Popular Posts

Saturday, May 12, 2018

የእግዚአብሔር ሶስቱ የምሪት ደረጃዎች

አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ። መዝሙር 32፡8
የእግዚአብሄርን የተስፋ ቃል እንደማወቅ የሚያሳርፍና የሚያስደስት ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር የተስፋ ቃሎች ንፁህ ናቸው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል የነጠረ ነው፡፡
በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው። መዝሙር 12፡6
የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች፤ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው። ምሳሌ 30፡5-6
እግዚአብሄር በተስፋ ቃሉ እንዲህ ይላል፡፡
·         አስተምርሃለሁ
እግዚአብሄር የፈጠረን ለክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሄ የፈጠረን ለአላማው ነው፡፡ ከመፈጠራችን በፊት በምድር ላይ ይምንሰራው ስራ ነበር፡፡ የተፈጠረንው እኛ የምንሰራው ስራ ስልነበረ ነው፡፡ ያንን ስራ ሊያሳየን ሊያስተምረን እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡
በእግዚአብሄር ካልተማርንና ካለ እውቀት ከሆንን እንደምንጠፋ እግዚአብሄር ያውቃል፡፡ በእግዚአብሄር ካልተማርን የተፈጠረንበትን አላማ መፈፀም አንደማንችልና ሰላም እንደማይኖረን እግዚአብሄር ያውቃል፡፡
ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል። ኢሳያስ 54፡13
እኛ መማር ከምንፈልግው በላይ እግዚአብሄር እንድንማርለት ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር ይናገራል፡፡ እግዚአብሄር በመረጠው መንገድ ሃሳቡን ይገልጣል ይናገራል፡፡ እግዚአብሄር በተለያየ መንገድ ይናገራል፡፡ እግዚአብሄር ሲናገር እናውቃለን፡፡ እግዚአብሄ ይናገር እንጂ የማናውቅው የእገዚአብሄ ንግግር የለም፡፡ እግዚአብሄር ሲያስተምር ልባችን ያውቀዋል፡፡ እግዚአብሄር በእኛ ደረጃ ወርዶ በሚገባን ቋንቋ ያስተምረናል፡፡
እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል፤ ኢዮብ 33፡14
·         በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤
ያስተማረንን እንዴት እንደምንተገብረው ደግሞ ያሳየናል፡፡ አስተምሮን ብቻ ዘወር አይልም፡፡ ያስተማረንን እንዴት እንደምንለማመደው ያሳየናል፡፡ እግዚአብሄ ማስተማር ብቻ ሳይሆን እግዚአብሄር ይመራናል፡፡ ስንለማመድ አብሮን ይሆናል፡፡ ማስተማር ብቻ ሳይሆን መንገዱን ያሳየናል፡፡ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በተግባር ይመራናል፡፡ መንፈሱ የተማርነውን ያሳሳበናል፡፡ ያ በሃሳብ ደረጃ የተማራችሁት በተግባር ይህ ነው ይለናል፡፡  
አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል። ዮሃንስ 14፡26
·         ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ
እግዚአብሄ ማስተማርና መምራት ብቻ ሳይሆን እስከመጨረሻው መሄዳችንን ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሄር አይኑን ከእኛ ላይ አይነቅልም፡፡ እግዚአብሄር በመንገዳችን ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሄር ከመንገዱ አለመውጣታችንንና በመንገዱ ውስጥ መሆናችንን ይከታተለናል፡፡
ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ። መዝሙር 23፡6
እግዚአብሄር በቸርነቱና በምህረቱ በህይወታችን ዘመን ሁሉ ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሄር ስለእኛ አይተኛም አያንቀላፋም፡፡   
እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም። እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም። መዝሙር 121፡3-4
አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ። መዝሙር 328
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #አስተምርሃለሁ #መንገድ #እመራሃለሁ #ዓይኖቼን #አጠናለሁ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment