Popular Posts

Saturday, June 30, 2018

The Moral Lesson from Argentina Vs. France Match

I was watching the world cup final knock out stage match between Argentina and France. France went through by defeating Argentina 4 to 2.
Some of the most important France players picked up yellow cards. The yellow cards they pick were unreasonable. Sometimes you may be tempted to commit foul when an attacker is about to score goals and It is sometimes worth the yellow card warning.
But when you just pick a yellow card in the middle of the field or just starting a fight doesn’t worth it at all.
France is through to the quarter-final but with some yellow cards that prevent them from playing the next match. Some of the players miss the next match because it is their second consequent yellow cards.
Some of them picked a yellow card not believing that they will be through to the next stage. Others were not cautious.
The moral lesson I got from the match is live your life in such a very careful way that doesn’t spoil your next stage. Don’t lose your next game focusing only on winning the current one.
God prevented David from building his house saying “You are not to build a house for my Name, because you are a warrior and have shed blood"
But God said to me, 'You are not to build a house for my Name, because you are a warrior and have shed blood.' 1 Chronicles 28:3
It takes discipline not to go overboard to win the current game at the cost of the next one.
Abiy Wakuma Dinsa
For More Articles https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#Jesus #God #Trust #praise #livelife #betrayal #blessed #rejoice #faith #enjoylife #faithfulness #church #achievement #celebration #preaching #salvation #bible #countingthecost #Argentina # France #worldcup #discipline #morale #abiy #facebook #abiywakuma #abiywakumadinsa  

በህይወቴ የምጠላው

በህይወቴ የምፈራው ሞትን አይደለም፡፡ ሞት የተሸነፈ ጠላት ነው፡፡ ሞት የሚያስፈራው የጌታ ኢየሱስን አዳኝነት ላልተቀበለ ሰው ለዘላለም ከእግዚአብሄር መለያያ መንገድ ስለሆነ ያስፈራል፡፡ ሞት የሚያስፈራው ከሞት ፍርሃት ነፃ ላልወጣ ላልዳነ ሰው ነው፡፡   
እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። ወደ ዕብራውያን 2፡14-15
የስጋ ሞት ከምድራዊ ህይወት ወደ መንፈሳዊ ህይወት የምንሸጋገርበት መተላለፊያ በር ነው፡፡ በእውነት ካሰብነው እግዚአብሄር በሰማይ ያዘጋጀልንን ክብር ካየነው መሞት ያስደስታል እንጂ አያስፈራም፡፡ መሞት እንዲያውም እረፍትና ጥቅም ነው፡፡ በምድር የምንኖረው የእግዚአብሄርን መንግስት ለመስራት እንጂ ለእግዚአብሄር ስራ ባይሆን ኖሮ መሞት እረፍት ነው፡፡
ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነውና። ነገር ግን በስጋ መኖር ለእኔ የሥራ ፍሬ ቢሆን፥ ምን እንድመርጥ ኣላስታውቅም። በእነዚህም በሁለቱ እጨነቃለሁ፤ ልሄድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ፥ ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻል ነውና፤ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 1፡21-23
በህይወቴ የምፈራው ማጣትን አይደለም፡፡
ማጣት እንደማይገድል አይቸዋለሁ፡፡ ማጣት ሊፈራ የሚገባ እንዳይደለ አይቼዋለሁ፡፡ ማጣት ማንንም መንከስ እንደማይችል እንደታሰረ ውሻ ባዶ ጩኸት መሆኑን በህይወቴ አይቼዋለሁ፡፡ ማጣት የእግዚአብሄርን ፈቃድ መፈፀም እንደማያግድ አይቼቸዋለሁ፡፡ ዋናው ነገር ማጣት ወይም ማግኘትን ሳይሆን ሁሉንም የሚያስችለን ክርስቶስ በእኛ ውስጥ መሆኑ ነው፡፡ ክርስቶስ ካለ ተጨማሪ ነገር አያስፈልገንም፡፡ ክርስቶስ ካለ ማጣት አያቆመንም፡፡ የሚያስችለን ማግኘት ሳይሆን ክርስቶስ ነው፡፡ በክርስቶስ ሁሉን እንችላለን፡፡
ይህን ስል ስለ ጉድለት አልልም፤ የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል ማለትን ተምሬአለሁና። መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ። ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ። ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 4፡11-13
በህይወቴ የምፈራው ድካምን አይደለም፡፡
ስንደክም ስንዋረድ በድካምና በመዋረድ ውስጥ ክብር አለ፡፡ በራሳችን ስንደክም ያን ጊዜ በክርስቶስ ሃይል ሃይለኛ ነኝ፡፡ የእግዚአብሄር ጉልበት በድካሜ ስለሚታይበት በድካሜ ደስ ይለኛል፡፡
እርሱም፦ ጸጋዬ ይበቃሃል፥ ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና አለኝ። እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ። ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም በመንገላታትም በችግርም በስደትም በጭንቀትም ደስ ይለኛል፤ ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 12፡9-10
በህይወቴ የምፈራው ሃዘንን አይደለም
ሃዘንተኛን በማፅናናት የተካነ የመፅናናት አምላክ እግዚአብሄር አባቴ ነው፡፡ አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ ሰላም የሚሰጥ እገዚአብሄ አብሮን ነው፡፡
የርኅራኄ አባት የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፡3
በህይወቴ የምፈራው መከራን አይደለም
ፈተና እኛን አሻሽሎን አበርትቶን ከፊት ይልቅ አሳድጎን ነው የሚያልፈው፡፡ ከምንችለው በላይ እንድንፈትን የማይፈቅድ ታማኝ እግዚአብሄር ስላለ መከራን አያስፈራንም፡፡ መከራ የሚያገኘው በእኛ ላይ ያለን የማያስፈልግ ስጋዊነትነ ብቻ ነው፡፡ መከራ የሚያራግፈው ክርስቶስን የማይመስለውን የስጋ ምኞታችንን ብቻ ነው፡፡ ስጋዊነትን በሰዎች ህይወት ስናይ እንደሚቀፈን ሁሉ ለእግዚአብሄር የማይመቸው በመከራ የሚራገፈውን ስጋዊነትን ስናይ እግዚአብሄር ይመስገን ልንል ይገባል፡፡
ሰላም ለእናንተ ይሁን። ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት ትዕግሥትም ምንም የሚጎድላችሁ ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም። የያዕቆብ መልእክት 1፡2-4
መውጫውን ያዘጋጀው እግዚአብሄር ከእኛ ጋር ስላለ ፈተና አያስፈራም፡፡
ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10፡13
የሚያስፈራው የእግዚአብሄርን ሃሳብ መጣስ ነው፡፡ የሚያስፈራው የምድር ህይወታችንን ለጊዜያዊ ለግል ጥቅማችን ማሳለፍ ነው፡፡ የሚያስፈራው ዋጋቸውን በምድር ተቀብለዋል መባል ነው፡፡ የሚያስፈራው በህይወታችን ዘመን ሁሉ እግዚአብሄር ያላለንን ነገር ሲያደርጉ በመኖር ህይወትን ማባከን ነው፡፡ የሚያስፈራው እግዚአብሄር ያዘዘንን ትተን እግዚአብሄር ያላዘዘንን ነገር ማድረግ ነው፡፡ የሚያስፈራው እግዚአብሄር ያልጠራንን ነገር በማድረግ አንዱን ህይወታችንን ማባከን ነው፡፡ የሞያስፈራው እግዚአብሄር ሳያዘን አንድ እርምጃን መራመድ ነው፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ልብ #መዳን #እምነት #ማስተዋል #አላማ #ግብ #የምፈራው #የምጠላው #ማጣት #ሃዘን #ፈተና #ሞት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ፅናት #ማሰብ #መሪ

የጴጥሮስ ክህደት

ብዙ ጊዜ ስለክህደት ሲነሳ ስሙ የሚነሳው ይሁዳ ነው፡፡ እንዲያውም የክህደት ሌላ ስሙ እስኪመስል ድረስ ይሁዳ ከክህደት ጋር አብሮ ይነሳል፡፡
ኢየሱስን ከካዱት ሁለት ሰዎች መካከል ይሁዳና ጴጥሮስ በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ጴጥሮስም ይህን ሰው አላውቀውም ብሎ ክዶዋል፡፡
ጴጥሮስም ከቤት ውጭ በአጥሩ ግቢ ተቀምጦ ነበር፤ አንዲት ገረድም ወደ እርሱ ቀርባ፦ አንተ ደግሞ ከገሊላው ከኢየሱስ ጋር ነበርህ አለችው። እርሱ ግን፦ የምትዪውን አላውቀውም ብሎ በሁሉ ፊት ካደ። ወደ በሩም ሲወጣ ሌላይቱ አየችውና በዚያ ላሉት፦ ይህ ደግሞ ከናዝሬቱ ከኢየሱስ ጋር ነበረ አለች። ዳግመኛም ሲምል፦ ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ካደ። የማቴዎስ ወንጌል 26፡69-72
ኢየሱስ ሰውን ሊክደው እንደሚችል ያውቃል፡፡ ሰው ሊክደኝ አይችልም ማለት አደገኛ አመለካከት ነው፡፡ ሰው የሚክደን በራሱ ችግር እንጂ እኛ ስላጠፋንም አይደለም፡፡ ሃጢያት የሌለበት ኢየሱስ ተክዷል፡፡
ልካድ እችላለሁ ብሎ ልብን ማስፋት ብንካድ ጉልበት ሊሰጠን የሚችል ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ሰው ሊካድ ቢችልም ሰውን ማመን ታላቅ ልብ ነው፡፡ ሰው ሊክደኝ ይችላል በሚል ፍርሃት ሰውን ማመን የሚያቆም ሰው ብቻውን ይቀራል፡፡ ሊክድ የሚችል እንዳለ የታመነ የማይክድ ሰውም ደግሞ አለ፡፡ ሊክድ በሚችለው ፍርሃት የታመነውን ሰው ማጣት ጥበብ አይደለም፡፡  
ፍቅር . . . ሁሉን ይታገሣል፥ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡7
ይሁዳ ሊክደው እንደሚችል ኢየሱስ አውቆ ነበር፡፡ ኢየሱስ እንደሚክደው አውቆ ከይሁዳ ጋር አብሮት ኖሮዋል አብሮት አገልግሏል፡፡
ኢየሱስም፦ እኔ እናንተን አሥራ ሁለታችሁን የመረጥኋችሁ አይደለምን? ከእናንተም አንዱ ዲያብሎስ ነው ብሎ መለሰላቸው። ስለ ስምዖንም ልጅ ስለ አስቆሮቱ ይሁዳ ተናገረ፤ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ የሆነ እርሱ አሳልፎ ይሰጠው ዘንድ አለውና። የዮሐንስ ወንጌል 6፡70-71
ኢየሱስ ጴጥሮስ እንደሚክደውም ሁሉ አስቀድሞ አውቆዋል፡፡
እርሱም፦ ጌታ ሆይ፥ ወደ ወኅኒም ወደ ሞትም ከአንተ ጋር ለመሄድ የተዘጋጀሁ ነኝ አለው። እርሱ ግን፦ ጴጥሮስ ሆይ፥ እልሃለሁ፥ እንዳታውቀኝ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዛሬ ዶሮ አይጮኽም አለው። የሉቃስ ወንጌል 22፡33-34
ይሁዳ በክህደቱ አገልግሎቱንም ህይወቱንም አጣ፡፡
በመዝሙር መጽሐፍ፦ መኖሪያው ምድረ በዳ ትሁን የሚኖርባትም አይኑር፤ ደግሞም፦ ሹመቱን ሌላ ይውሰዳት ተብሎ ተጽፎአልና። የሐዋርያት ሥራ 1፡20
ማንም ሰው ሊወድቅ ይችላል፡፡ ሰው በክህደቱ ከቀጠለ ህይወቱንና አገልግሎቱን ያጣል፡፡ ሰው ግን በክህደቱ ካዘነና ከተመለሰ እንዳልወደቀ ሆኖ እግዚአብሄር እንደገና በሃይል ይጠቀምበታል፡፡
እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን ጸጸት የሌለበትን፥ ወደ መዳንም የሚያደርሰውን ንስሐ ያደርጋልና፤ የዓለም ኀዘን ግን ሞትን ያመጣል። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7፡10
ከይሁዳ የሚለየው ጴጥሮስ የሚመለስ ልብ ነበረው፡፡ አንዳንዴ ካልሆነ የጴጥሮስ ክህደት አይነሳም፡፡ የጴጥሮስ ክህደት ከመረሳቱ የተነሳ ጴጥሮስን የምናስታውስበት ብዙ መልካም ነገሮች አሉ፡፡ ኢየሱስ የጴጥሮስን ከውድቀቱ ባሻገር መነሳቱን አይቶ ነበር፡፡ ኢየሱስ ከክህደቱ ባሻገር የጴጥሮስን ጠቃሚነቱን አይቶ ነበር፡፡
ጴጥሮስ የሚሰበር በጥፋቱ የሚያዝን ልብ ስልነበረው እግዚአብሄር ሁለተኛ እድል ሰጠው፡፡ ኢየሱስ ጴጥሮስ ወደፊት የማይክድበትን መንገድ ቀየሰ፡፡ ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ እንዲሞላና እንዲክድ ያደረገውንና ያሸነፈውን የፍርሃት መንፈስን የሚያሸንፍበት መንፈስ ቅዱስ ተሞላ፡፡
ጴጥሮስ በንስሃ ከተመለሰ በኋላ መንፈስ ቅዱስን በመሞላት ያሸነፈውን የፍርሃትን መንፈስ አሸነፈው፡፡
ነገር ግን ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ፥ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ሲል ተናገራቸው፦ አይሁድ በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፥ ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፥ ቃሎቼንም አድምጡ። የሐዋርያት ሥራ 2፡14
ጴጥሮስ ሲመለስ እግዚአብሄር በመንፈስ ቅዱስ ሙላት የሃይል የፍቅር ራስን የመግዛት መንፈስ ሰጠው፡፡
እግዚአብሔር የኃይልና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሃት መንፈስ አልሰጠንምና። 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1፡7
ማንም ሰው በክህደት ሊወድቅ ይችላል፡፡ የሚነሳውና እንደገና የእግዚአብሄር መጠቀሚያ የሚሆነው ሰው ግን በንስሃ በእግዚአብሄር ፊት የሚመለሰው ሰው ብቻ ነው፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መካድ #መታለል #ታማኝነት #ክህደት #ንስሃ #ሃዘን #መመለስ መጣል #መሰደድ #መገፋት #መውደቅ #አለመመረጥ #ተቀባይነትማጣት #ዋጋአሰጣጥ #አእምሮ #ልብ #ኢየሱስ #ጌታ #መፅሃፍቅዱስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አምልኮ #እምነት #መከተል 

Friday, June 29, 2018

በሰው የሚታመን

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹንም ክንዱ የሚያደርግ ልቡም ከእግዚአብሔር የሚመለስ ሰው ርጉም ነው። በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ ይሆናል፥ መልካምም በመጣ ጊዜ አያይም፤ ሰውም በሌለበት፥ ጨው ባለበት ምድር በምድረ በዳ በደርቅ ስፍራ ይቀመጣል። ትንቢተ ኤርምያስ 17፡5-6
እግዚአብሄር የፈጠረን በእርሱ እንድንደገፍ ነው፡፡ በእርሱ ስንደገፍ እግዚአብሄር ደስ ያሰኘዋል፡፡
ነገር ግን በእግዚአብሄር መታመን ትተን በሰዎች መታመን ስንጀምር እግዚአብሄር ያዝናል፡፡ የተፈጠርነው በእግዚአብሄር እንድንደገፍ ስለሆነ በሰው ስንደገፍ አይሳካልንም፡፡
እንኳን ለሌላ ሰው መገደፊያ ሊሆን ይቅርና ሰው ራሱ በእግዚአብሄር ላይ መገደፍ አለበት፡፡ ሰው ለሌላ ለማንም ሰው መደፊያ ሊሆን አይችልም፡፡
ብዙ ሰዎች በእግዚአብሄር መታመን ይጀምራሉ፡፡ በእግዚአብሄር በመታመን እንድንጀምር ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሄር በመታመን እንድንጨርስ እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡
በአስቸጋሪ ጊዜ እምነቱን ከእግዚአብሄር ላይ የማያነሳ ሰው ምስጉን ነው፡፡ በክፉ ጊዜ እምነቱን ከእግዚአብሄር ላይ የሚያነሳ ሰው እርጉም ነው፡፡
በመከራ ቀን ብትላላ ጉልበትህ ጥቂት ነው። መጽሐፈ ምሳሌ 24፡10
አስቸጋሪ ጊዜ አልፎ ደግሞ መልካም ዘመን ሲመጣ እምነቱ ከእግዚአብሄር ላይ ያነሳውና በሰው ላየ ያደረገው ሰው ይፀፀታል፡፡ መልካም ጊዜ መጥቶ የማይለወጥ የሚመስለው ነገር ሲለወጥ እምነቱን ከእግዚአብሄር ላይ እንስቶ ወደሰው ላይ ያደረገው ሰው ለሚያልፍ ነገር ምነው በእግዚአብሄር በታመንኩኝ ኖሮ ብሎ ይቆጫል፡፡ በአስቸጋሪ ጊዜ እምነቱን እግዚአብሄርን በሰው የለወጠ ሰው የእምነትን ገድል ደስታ አያገኘውም፡፡ በአስቸጋሪ ጊዜ እምነቱን ከእግዚአብሄር ላይ እንስቶ በሰው ላይ ያደረገ ሰው ለማይረባ ነገር እግዚአብሄርን ስለለወጠው ያፍራል፡፡
በአስቸጋሪ ጊዜ ሁሉ ከእግዚአብሄር ጋር የሙጥኝ ያለ ሰው በእግዚአብሄር በመታመኑና በማለፉ ብቻ እምነቱ ይጨምራል፡፡ በአስቸጋሪ ጊዜ እግዚአብሄርና ያመነና የጠበቀ ሰው እምነቱ ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ጠርቶና ከብሮ ይወጣል፡፡ በአስቸጋሪ ጊዜ እምነቱን በሰው ያልለወጠው ሰው ደስታው ይበዛል፡፡
በዚህም እጅግ ደስ ይላችኋል፥ ነገር ግን በእሳት ምንም ቢፈተን ከሚጠፋው ወርቅ ይልቅ አብልጦ የሚከብር የተፈተነ እምነታችሁ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ፥ ለምስጋናና ለክብር ለውዳሴም ይገኝ ዘንድ አሁን ለጥቂት ጊዜ ቢያስፈልግ በልዩ ልዩ ፈተና አዝናችኋል። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1፡6-7
እምነቱን ሲፈተን የወደቀ ሰው መልካም በመጣ ጊዜ አያይም፡፡ በሰው መደገፍን ያልናቀ ሰው በእግዚአብሄር በመደገፍ ያለውን ደስታ አያይም፡፡ በሰው በመደገፍ ክፉን ጊዜ ያሳለፈ ሰው ላነሰ ጥቅም ራሱን ስለሰጠ እውነተኛውን የእግዚአብሄርን በረከት አያየውም፡
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹንም ክንዱ የሚያደርግ ልቡም ከእግዚአብሔር የሚመለስ ሰው ርጉም ነው። በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ ይሆናል፥ መልካምም በመጣ ጊዜ አያይም፤ ሰውም በሌለበት፥ ጨው ባለበት ምድር በምድረ በዳ በደርቅ ስፍራ ይቀመጣል። ትንቢተ ኤርምያስ 17፡5-6
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ስጋለባሽ #መታመን #መደገፍ #ልብ #የሚመልስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ክንዱ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መታመን #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

Thursday, June 28, 2018

የእግዚአብሔር ቃል ሙላት

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤ በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ፤ በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ ወደ ቆላስይስ ሰዎች 3፡16
እግዚአብሄርን የምናውቀው በቃሉ ነው፡፡ እግዚአብሄርን የምንሰማው በቃሉ ነው፡፡ ከእግዚአብሄር ጋር የምንራመደው በቃሉ ነው፡፡ እምነት የሚመጣው በቃሉ ነው፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡17
ካለ እምነት እግዚአብሄርን ደስ ማሰኘት አይቻልም፡፡ እምነት የሚመጣበት ቃሉ በሙላት ሲኖርብን እምነታችን ይሞላል፡፡ ቃሉ በህይታችን ሲጎድል እምነታችን ይጎድላል፡፡
ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ወደ ዕብራውያን 11፡6
ፍሬ የምናፈራው በቃሉ ነው፡፡ ቃሉ በህይወታችን ከጎደለ ፍሬያችን ይጎድላል፡፡ ቃሉ በሙላት ሲኖርብን ፍሬያችን ሙሉ ይሆናል፡፡
አእምሮዋችን የሚታደሰው በቃሉ ነው፡፡ ቃሉ በህይወታችን ሲጎድል የአእምሮዋችን አዲስነት ይጎድላል፡፡ ቃሉ በሙላት ሲኖርብን አእምሮዋችን በሙላት ይታደሳል፡፡
የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ወደ ሮሜ ሰዎች 12፡2
የእግዚአብሄር ቃል እውቀት በህይወታችን ሲጎድል የእግዚአብሄር ፀጋ በህይወታችን ይጎድላል፡፡ የእግዚአብሄር ቃል በህይወታችን ሲበዛ የእግዚአብሄር ፀጋ በህይወታችን ይበዛል፡፡
የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። 2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1፡2-3
የእግዚአብሄር ቃል ከህይወታችን ሲጎድል ነፃነታችን ይጎድላል፡፡ የእግዚአብሄር ቃል በህይወታችን ሲበዛ ነፃነታችን ይበዛል፡፡
ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ፦ እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። የዮሐንስ ወንጌል 8፡31-32
የእግዚአብሄር ቃል በህይወታችን ሲጎድል ህይወታችን ሙላትን ያጣል፡፡ የእግዚአብሄር ቃል በሙላት ሲኖርብን ህይወታችን ሙሉ ይሆናል፡፡
ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው፤ ሥጋ ምንም አይጠቅምም፤ እኔ የነገርኋችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወትም ነው። የዮሐንስ ወንጌል 6፡63
ስለዚህ ነው ለእግዚአብሄር ቃል በህይወታችን የመጀመሪያውን ስፍራ በመስጠት ፣ መፈለግ ፣ ማንበብና መስማት ማሰላሰል ያለብን፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እውቀት #ጥበብ #ሙላት #መዳን #ኢየሱስ #ጌታ #እግዚአብሔር #ቃል #መልካም #መታዘዝ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ነፃነት #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፀጋ #ሰላም #ልጅ

በእምነትም ያልሆነ ሁሉ

የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 14፡23
ሰው የተፈጠረው ለእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡ እግዚአብሄርን የምናከብረው ቃሉን በመጠበቅና በቃሉ በመኖር ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሄርን የምናከብረውና የምናስደስተው በቃሉ በመኖር ፍሬ በማፍራት ብቻ ነው፡፡
በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል። ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራል። የዮሐንስ ወንጌል 15፡7-8
ካለ እምነት እግዚአብሄርን ደስ ማሰኘት አይቻልም፡፡
ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ወደ ዕብራውያን 11፡6
እግዚአብሄርን የምናስደስተው ከቃሉ በሆነ እምነት ኑሮ ብቻ ነው፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡17
ሰው የተፈጠረው ከቃሉ በሚገኝ እምነት እንዲኖር ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በእምነት ከእግዚአብሄር ጋር እንዲራመድ ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በእምነት በሚወስደው እርምጃ እግዚአብሄርን እንዲያስደስት ነው፡፡ ሰው በእምነት ሲኖር የተፈጠረበትን አላማ ግቡን ይመታል፡፡ ሰው ከእምነት ውጭ ሲኖር የተፈጠረበትን አላማ ይስተዋል፡፡ ከቃሉ በሚመጣ እምነት እንጂ በጥርጥር እግዚአብሄር አይከብርም፡፡ ጥርጥር የተፈጠሩበትን አላማን መሳት ነው፡፡ ጥርጥር አላማን መሳት ወይም ሃጢያት ነው፡፡
ስለዚህ ነው እምነት የሚገኝበትን የእግዚአብሄር ቃል ላይ የሙጥኝ ማለት ያለብንና በእምነት እርምጃን መውሰድ ያለብን፡፡
የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 14፡23
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ልብ #ማመን #ቃል #መናገር #ያለእምነት #ስሜት #ሁኔታ #አካባቢ #አላማ #መሳት #ሃጢያት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አለማመን #ጥርጥር #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Wednesday, June 27, 2018

ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና

አቤቱ፥ አንተ ኵላሊቴን ፈጥረሃልና፥ በእናቴም ሆድ ሰውረኸኛል። ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ፤ ሥራህ ድንቅ ነው፥ ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች። እኔ በስውር በተሠራሁ ጊዜ፥ አካሌም በምድር ታች በተሠራ ጊዜ፥ አጥንቶቼ ከአንተ አልተሰወሩም። ያልተሠራ አካሌን ዓይኖችህ አዩኝ፤ የተፈጠሩ ቀኖቼ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመጽሐፍህ ተጻፉ። መዝሙረ ዳዊት 139፡13-16
እግዚአብሄርን ከማወቅ ቀጥሎ ራስን ማወቅ እጅግ ወሳኝ ነገር ነው፡፡ እግዚአብሄርን አውቀን በመልኩና በአምሳሉ የሰራንን ራሳችንን ካላወቅን በእርሱና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት ሊሳካ አይችልም፡፡ ራሳችንን ካላወቅን ከእግዚአብሄር ጋርና ከሌላው ጋር ያለን ግንኙነት ትክክል ሊሆን አይችልም፡፡
በመድር ላይ ያሉ አብዛኛው ችግሮች መንስኤ የሰው እግዚአብሄርን ያለማወቅና ራስን ያለማወቅ ችግር ነው፡፡
ሰው ራሱን ካላወቀና እግዚአብሄር እንደሚያየው አድርጎ ካላየ ከእግዚአብሄር ጋርም ከሰውም ጋርም እንዴት እንደሚኖር ማወቅ አይችልም፡፡ ሰው እግዚአብሄር እንደሚያየው ራሱን ካላየ እግዚአብሄር በህይወቱ ያለውን አላማ ለመፈፀም አይችልም፡፡
እግዚአብሄር ግሩምና ድንቅ አድርጎ ፈጥሮናል፡፡ እግዚአብሄር በመድር ላየ እንድንሰራ ለፈለገው ነገር በቂ ነገር በእኛ ውስጥ ፈጥሮአል፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ሊፈፅም ላሰበው ነገር የሚጎድለን ምንም እምቅ ሃይል የለም፡፡
የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። 2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1፡2-3
ሰይጣንም በመጀመሪያ የሰው ልጅን የተዋጋው ሰው ያለውን ማንነት በማበላሸትና ለራሱ ያለውን መረዳት በማሳሳት ነው፡፡
እባብም ለሴቲቱ አላት፦ ሞትን አትሞቱም፤ ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። ኦሪት ዘፍጥረት 3፡4-5
አሁንም ሰይጣን የሚጎድልህ ነገር አለ ፣ እግዚአብሄር የደበቀህ ነገር አለ ወይም እግዚአብሄር ከሚያስፈልግህ ነገር አጉድሎብሃል ብሎ በውሸት ካሳመነህ ትወድቃለህ፡፡ 
ነገር ግን ውብና ድንቅ አድርጎ ሰርቶኛል፡፡ እኔ የእርሱ የፈጠራ ውጤት ማሳያ ነኝ፡፡ እኔ የእግዚአብሄር የእጅ ስራ ነኝ፡፡ እኔ በህይወት ያለኝን አላማ ለመፈፀም ፍፁም ተደርጌ ተፈጥሬያለሁ ካልክ ታሸንፋለህ፡፡
እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፡10
እግዚአብሄር ውብና ድንቅ አድርጎ እንደሰራኝ ራሴን ከተቀበልኩ አሸንፋለሁ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር የፈጠረኝ አፈጣጠር ላይ የማወጣው አቃቂር ካለ የህይወት አላዬን መፈፀም ያቅተኛል እሸነፋለሁም፡፡
ራሱን ያልተቀበለ ሰው ሌላውን ሊቀበል አይችልም፡፡ ሌላውን ያለመቀበል ችግር ወደኋላ ቢጠና ራስን ያለመቀበል ችግር መንስአኤ ነው፡፡
ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ፤ ሥራህ ድንቅ ነው፥ ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች። መዝሙረ ዳዊት 139፡14
ምንም ሳላሻሽልና ሳልቀንስ ሳልጨምር ራሴን እቀበለዋለሁ፡፡ ማንም በፍጥረቴ ላይ ጥያቄ ቢኖረው ምንም ማድረግ አልችልም አዝናለሁ፡፡ እኔ ግን ፍጥረቴን እወደዋለሁ፡፡ እኔ ግን በፍጥረቴ ላይ ምንም የማወጣው እንከን የለም፡፡
እግዚአብሄር የፈጠረው የቆዳዬ ቀለም ፣ ቁመቴ ፣ ዘሬ ፣ መልኬ ፣ አስተዳደጌና ባህሪዬ ምንም አይወጣለትም፡፡ ስለ ቆዳዬ ቀለም ፣ ስለ ቁመቴ ፣ ስለ ዘሬ ፣ ስለ መልኬ ፣ ስለ አስተዳደጌና ስለ ባህሪዬ ማንንም ይቅርታ አልጠይቅም፡፡ ማንም በአፈጣጠሬ ላይ እንከን ያገኘበት ካለ ንስሃ ይግባና ይመለስ፡፡ ማንም ሰው አይኑ ተለቅ ቢል ኖሮ ጥሩ ነበር ቢል ይችላል፡፡ የእግዚአብሄርን የእጅ ስራ የማስተካክል እኔ ማነ ነኝ?
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ግሩም #ድንቅ #በክርስቶስ #መንፈስ #ማንነት #መልክ #አምሳል #የእግዚአብሄርልጅ #ክብር  #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ማየት #የእግዚአብሄርመንግስት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አዲስፍጥረት #ክርስቶስ #የእግዚአብሄርቤተሰብ #ማእረግ #ስልጣን #ከፍታ

እግዚአብሔርን የሚያስክደን ክፉና የማያምን ልብ 8 ምልክቶች

ወንድሞች ሆይ፥ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፤ ወደ ዕብራውያን 3፡12
አማኝ የነበረ ሰው ካልተጠነቀቀ በስተቀር አንድ ቀን ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክደው ክፉና የማያምን ልብ ሊኖረው ይችላል፡፡ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት አመልካች ምልክቶች ሰው በአፉ ምንም ቢልም እንኳን ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክደው ክፉና የማያምን ልብ እንዳለው ያመለክታል፡፡
1.      በህይወታችን ለቁሳቁስ የመጀመሪያውን ስፍራ ስንሰጥ
ሰው እግዚአብሄርን ተስፋ ካላደረገ ተስፋ የሚሆነውን ነገር ይፈልጋል፡፡ ሰው እግዚአብሄርን ማመን ሲያቆም በቁሳቁስ ማመን ይጀምራል፡፡ ሰው እግዚአብሄርን ማመን ሲያቆም በገንዘብ ማመን ይጀምራል፡፡ ሰው ለእግዚአብሄር መገዛት ሲያቆም ለገንዘብ ይገዛል፡፡ ሰው ገንዘብን ሲወስድ እግዚአብሄርን ይጠላል፡፡
ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም ይወዳል፤ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል፤ ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም። የማቴዎስ ወንጌል 6፡24
2.     ስለዘላለም ህይወት ማሰብ ስናቆም
ሰው የሚያሳስበው የምድር ህይወት ብቻ ከሆነ ልቡ እግዚአብሄርን አስክዶታል ማለት ነው፡፡ ሰው በአፉ ምንም ቢናገር ነገር ግን ለዘላለም ህይወት አክብሮት ካጣ በእግዚአብሄር የፍርድ ወንበር ፊት እንደሚቀርብ ማሰብ ከተወ እግዚአብሄርን እንደካደ የሚያሳይ ጥሩ ምልክት ነው፡፡  
እንደ ሰው በኤፌሶን ከአውሬ ጋር ከታገልሁ፥ ሙታንስ የማይነሡ ከሆነ፥ ምን ይጠቅመኛል? ነገ እንሞታለንና እንብላና እንጠጣ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፡32
3.     ስለ እግዚአብሄር ፈቃድ ግድ ሳይኖረን ሲቀር
እግዚአብሄርን የሚያምን ሰው ምልክቱ ለእግዚአብሄር ክብር መኖር ነው፡፡ እግዚአብሄርን የሚያምን ሰው የመጀመሪያው ፍላጎቱ እግዚአብሄር በህይወቱ ያለውን አላማ ለመፈፀም የእግዚአብሄርን ፈቃድ መፈለግ ነው፡፡ ሰው ግን የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለመፈለግ ፍላጎቱን ካጣና ለእግዚአብሄር ፈቃድ ግድ ከሌለው እግዚአብሄርን እንደካደ አመልካች ነው፡፡
ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር። የሉቃስ ወንጌል 22፡42
4.     ለቤተክርስትያን የቤተሰብነት ስሜት ስናጣ
ሰው እግዚአብሄርን ሲያምን በምድር ላይ ያለው የእግዚአብሄር ቤተሰብ አባል እንደሆነ የቤተሰብነት ስሜት ይሰማዋል፡፡ ሰው ግን ለቤተክርስትያን የቤተሰብነት ስሜት ካጣ በቤተክርስትያን ላይ እንደፈለገ የሚናገርና የሚያደርግ ከሆነ እግዚአብሄርን እንደካደ አመልካች ነው፡፡
አንድም ብልት ቢሣቀይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ይሣቀያሉ፤ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል። እናንተም የክርስቶስ አካል ናችሁ እያንዳንዳችሁም ብልቶች ናችሁ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 12፡26-27
5.     ለእግዚአብሄር ቃል የነበረንን ክብደት ስናጣ
ሰው ለእግዚአብሄር ቃል ያለውን የመጀመሪያ ስፍራ ካጣ እና የእግዚአብሄርን ቃል እንደሰው ቃል ማየት ከጀመረ በአፉ ምንም ይበል ምን እግዚአብሄርን እየካደ እንደሆነ ያመለክታል፡፡ ሰው ሃሳቡን እንደ እግዚአብሄር ቃል መመዘኛ መመርመር ካቆመ እግዚአብሄርን እየካደ ነው፡፡
ስምዖን ጴጥሮስ፦ ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤ የዮሐንስ ወንጌል 6፡68
6.     እግዚአብሄርን መፍራት ስናቆም
ሰው እግዚአብሄርን መፍራት ካቆመና እግዚአብሄር እንደሚያይ እንደሚሰማና በሁላችን ላይ ዳኛ እንደሆነ ከረሳ እግዚአብሄርን  ክዶዋል፡፡ ሰው የዘራወን ያንኑ ደግሞ እንደሚያጭድ ካላወቀ እግዚአብሄርን የሚያስክድ ክፉ ልብ አለው ማለት ነው፡፡
አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤ ወደ ገላትያ ሰዎች 6፡7
7.     መፀለይ ስናቆም
እግዚአብሄርን የሚያምን ሰው እግዚአብሄርን በመፈለግና በመፀለይ ይታወቃል፡፡ ሰው ግን መፀለይን ካቆመና ሁሉንም ነገር በራሱ ጉልበት ለመፍታት ከፈለገ እግዚአብሄርን የሚያስክድ ክፉና የማያምን ልብ እንዳለው ራሱን ይመርምር፡፡
በእናንተ ዘንድ ጦርና ጠብ ከወዴት ይመጣሉ? በብልቶቻችሁ ውስጥ ከሚዋጉ ከእነዚህ ከምቾቶቻችሁ አይደሉምን? ትመኛላችሁ ለእናንተም አይሆንም፤ ትገድላላችሁ በብርቱም ትፈልጋላችሁ፥ ልታገኙም አትችሉም፤ ትጣላላችሁ ትዋጉማላችሁ ነገር ግን አትለምኑምና ለእናንተ አይሆንም፤የያዕቆብ መልእክት 4፡1-2
8.     እግዚአብሄርን መከተልና ማገልገል ከንቱ ነው ብለን ስናስንብ
ሰው በአፉ ላይናገረው ይችላል ነገር ግን እግዚአብሄርን ማገልገል ከንቱ ነው ብሎ ካሰበ እግዚአብሄርን የሚያስክድ ክፉና የማያምን ልብ እንዳለው አውቆ በንስሃ ይመለስ ፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ  Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ልብ #ማመን #ቃል #መናገር #ስሜት #ሁኔታ #አካባቢ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አለማመን #ጥርጥር #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #የሚያስክድ #ክፉልብ #የማያምን #ትግስት #መሪ