I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል። ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸ...
-
Faith is an Adventure Faith is an exciting adventure. The faith walk is a real and worthwhile adventure. There is nothing more adventuro...
-
It is very wise to seize any opportunity set-aside to give thanks to the Lord. But thanks-giving isn’t a once a year activity to be ...
-
መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 2፡1-10 ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች፦ ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል። ...
-
Who is the real Jesus? Two thousand years ago a man set foot on our planet who claimed to be from a place beyond space and time. Althoug...
-
እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በውስጡ ቅሚያና ስስት ሞልቶ ሳለ የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ስለምታጠሩ፥ ወዮላችሁ። አንተ ዕውር ፈሪሳዊ፥ ውጭው ደግሞ ጥሩ እንዲሆን አስቀድመህ የጽዋውንና የወጭቱን ውስጡን አጥራ። ...
-
እግዚአብሔርን ሰውን ሲፈጥረው ከሰው ጋር በደንብ መነጋገር እንዲችል በመልኩና በአምሳሉ ነው የፈጠረው፡፡ እግዚአብሔር በመልኩና በአምሳሉ ለፈጠረው ለሰው ይናገራል፡፡ የእግዚአብሔርና የሰው ግንኙነት በሃጢያት ምክኒያት...
-
የእግዚአብሄር መንግስት የመንፈስ መንግስት ነው፡፡ እግዚአብሄር መንፈስ ነው፡፡ ከእግዚአብሄር ጋር የምናደርገውን ማንኛውንም ነገር የምናደርገው በእምነት እንጂ በማየት አይደለም፡፡ ለክርስትና ህይወት እምነት ወሳኝ ነው፡...
-
ለእውነት እንጂ በእውነት ላይ ምንም ለማድረግ አንችልምና። 2ኛ ቆሮንቶስ 13፡8 በእግዚአብሄርና ለእግዚአብሄር ክብር ተፈጥረናል፡፡ ከእግዚአብሄር ጋር የምንኖረው በእግዚአብሄር ህግ በእግዚአብሄር ቅድመ ሁኔ...
Sunday, July 31, 2022
Saturday, July 30, 2022
Thursday, July 28, 2022
Monday, July 25, 2022
ባለ ጠጋም በውርደቱ ይመካ
የተዋረደው ወንድም ግን በከፍታው፥ ባለ ጠጋም በውርደቱ ይመካ፤ እንደ ሣር አበባ ያልፋልና። ፀሐይ ከትኵሳት ጋር ይወጣልና፥ ሣርንም ያጠወልጋልና፥ አበባውም ይረግፋልና፥ የመልኩም ውበት ይጠፋልና፤ እንዲሁ ደግሞ ባለ ጠጋው በመንገዱ ይዝላል። የያዕቆብ መልእክት 1:9-11
ሁላችንም
በህይወታችን
ከእኛ
የሚበልጥ
የሚያስመካ
ሃያል
ነገርን
እንፈልጋለን፡፡
ነገር
ግን
ያስመካል
ብለን
የምናስበው
ነገር
ሁሉ
የሚያስመካ
አይደለም፡፡
መፅሃፍ
ቅዱስ
በሚታይ
ነገር
የተዋረደ
ወንድም
ሊዋረድ
እንደማይገባው
ያስተምረናል፡፡
በምድራዊ
ነገር
ብዙ
ነገር
የሌለው
ሰው
በውርደቱ
እንዳይዋረድ
መፅሃፍ
ቅዱስ
ያስጠነቅቃል፡፡
በምድራዊ
ህይወት
ደረጃው
ዝቅተኛ
የሆነ
ሰው
ውርደቱን
በሚሸፍን
በእግዚአብሄር
እንዲመካ
ያስተምራል፡፡
በምድራዊ
ነገር
ባለጠጋ
መሆን
ለመመካት
ብቁ
ያልሆነ
ነገር
በመሆኑ
በምድራዊ
ነገር
ባለጠጋ
የሆነ
ሰው
በባለጠግነቱ
እንዳይመካ
መፅሃፍ
ቅዱስ
ይመክራል፡፡
ባለጠጋ
መመካት
ያለበት
የሚያስፈልገውን
በማያጎድልበት
በእግዚአብሄር
ብቻ
ነው፡፡
የእግዚአብሄር
ነገር
ብቻ
እንጂ
በምድር
ላይ
ምንም
የሚያስተማምን
ምንም
ቋሚ
ነገር
የለም፡፡
ብላቴኖች
ይደክማሉ
ይታክቱማል፥
ጐበዛዝቱም
ፈጽሞ
ይወድቃሉ፤
እግዚአብሔርን
በመተማመን
የሚጠባበቁ
ግን
ኃይላቸውን
ያድሳሉ፤
እንደ
ንስር
በክንፍ
ይወጣሉ፤
ይሮጣሉ፥
አይታክቱም፤
ይሄዳሉ፥
አይደክሙም።
ኢሳያስ
40፡30-31
Saturday, July 23, 2022
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት
ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥየለም። 1 ኛ ዮሀንስ 3:15-16
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት ከህፃንነት የሚመነጭ የስጋዊነት ሀጢያት ነው::
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት የእግዚአብሔርን ፍቅር በአግባቡ ካለመረዳት የሚመጣ አለመብሰል እንጭጭነትነው::
ሰው በእግዚአብሐር የተወደደበትን ጥልቅ ፍቅር ሲረዳ የገንዘብን ትንሽነት እና ውስንነት ስለሚረዳ በገንዘብውይም በኑሮ ከመመካት የስጋዊነት ሀጢያት ይድናል::
ከክፉ የሚጠብቀውን የሚያኖረውን የእግዚአብሔርን ፍቅር በሚገባ የተረዳ ሰው ስለገንዘብ መመካትያሳፍረዋል::
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናውአይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው። ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔንበማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር። ኤርሚያስ 9:23-24
ሰው በሚበላው ምግብ ውድነት ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው በሚነዳው መኪና ውድነት ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው እንጂ መንፈሳዊ ሰው አይደለም::
ሰው ባለመማሩ ካዘነ እና ከተዋረደ መንፈሳዊ ስው አይደለም ማለት ነው::
ሰው ባለው እውቀት ከተመካ ከአለማዊ አስተሳሰብ ያልዳነ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው ባለው ሀብት ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው ባለው ዘመድ ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው በሚለብሰው ልብስ ውድነት ከተመካ መንፈሳዊ ሰው አይደለም::
ሰው በእግዚአብሔር ሳይሆን በውበቱ ከተመካ እን ደስ ድስ ከተሰኘ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው በድህነቱ ካዘነ እና ከተዋረደ መንፈሳዊ ስው አይደለም ማለት ነው::
በሚኖርበት ቤት ትልቅነት እና ውድነት የሚመካ ሰው መንፈሳዊ አይደለም ማለት ነው::






