I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
Live soberly and be vigilant, for the devil, who is not your partner, prowls around like a roaring lion looking for someone to devour. Re...
-
የህይወት ስኬት የሚመጣው ለእግዚአብሄር ቃል የመጀመሪያውን ስፍራ በመስጠትና በቃሉ ከባቢ ውስጥ ለመኖር በመወሰን ነው፡፡ ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ...
-
ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ማቴዎስ 5፡10 አለም በክፉ ተይዞአል፡፡ ሰው እግዚአብሄርን ሲያመልክና ሲከተል ከብዙ ሰዎች መካከል ተለይቶ ይወጣል፡፡ በክርስትና ለጌታ ብ...
-
“ አስቀድማችሁ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ፥ እርሱም ግብዝነት ነው። ” የሉቃስ ወንጌል 12 ፡ 1 የፈሪሳዊያን ትምህርት ተጠበቁ ሲባል አንድን የህብረተሰብ ክፍል ወይም አንድን ሃይማኖት የሚመለከት በፍ...
-
A group of alumni, highly established in their careers, got together to visit their old university professor. Conversation soon turned in...
-
ስለ እግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት አይደለም ከማርያምና ከእኅትዋ ከማርታ መንደር ከቢታንያ የሆነ አልዓዛር የሚባል አንድ ሰው ታሞ ነበር። ማርያምም ጌታን ሽቱ የቀባችው እግሩንም በጠጕርዋ ያበሰችው ነበረች፤ ወንድም...
-
የዲያቢሎስ አላማ አንድና አንድ ነው፡፡ ዲያቢሎስ ከመጣ ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ለሌላ ነገር አይመጣም፡፡ ዲያቢሎስንብ የመጋዣው መንገድ ደግሞ በእግዚአብሄር ላይ ማመፅ ወደ እግዚአብሄር...
-
We are created to be free moral beings. Man thinks before he decided to do something. He only does what he decided to do. For as he ...
Wednesday, October 30, 2024
የአሜሪካ የፕሬዝዳንታዊነት ምርጫ
Tuesday, October 29, 2024
ሀሎዊን ክፍል 2
ሃሎዊን Halloween የሚባለው በአል በኦክቶበር ወር መጨረሻ ላይ በተለያየ መልኩ ይከበራል፤ ባብዛኛው ህዝብ ዘንድ እንደ አንድ ባህል የሚከብረው ይህ የሃሎዊን በአል ሰዎች ቢገባቸውም ባይገባቸውም መንፈሳዊ እንደምታ የለውም ማለት ግን አይቻልም።
ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ እንጂ ስለሌላ አይመጣም የተባለው ጠላት ዲያቢሎስ ባገኘው አጋጣሚ የሰዎችን ህይወት ይሰርቃል ያርዳል ያጠፋል።
ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። የዮሐንስ ወንጌል 10፣10
ሰይጣን በእግዚአብሄር ይፈጠር የእግዚአብሄር መላክ የነበር ሳጥናኤል ነበር። ሳጥናኤል ሰይጣን የሆነው እና እርሱን ከተከተሉት የወደቁት መላእክት ጋር ከእግዚአብሄር ፊት ወደ ምድር የተጣለው በትእቢት እንደ እግዚአብሄር ሊሆን ስለፈለገ ነበር።
መኖሪያቸውንም የተዉትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁትን መላእክት በዘላለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ቀን ፍርድ ድረስ ጠብቆአቸዋል። የይሁዳ መልእክት 1:6
ሰይጣን ዲያብሎስ የእሳት ባህር ቅጣት ተዘጋጅቶልታል።
እስክዚያ ግን የቻለውን ያህል ሰው አታልሎ ብዙ ሰዎችን ወደ እሳት ባህር መሄድ ይፈልጋል። የእሳት ባህር ለሰው ያልተዘጋጀ ቢሆንም እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ ያልተቀበሉ ሁሉ ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር ይጣላሉ።
እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ የተቀብሉ ብቻ ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም አይለያዩም ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር አይጣሉ።
በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ። የማቴዎስ ወንጌል 25:11
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
#ሰይጣን #ሀሎዊን #ሃሎዊን #ጠላት #ዲያቢሎስ #አቢይዋቁማ #ኢየሱስጌታ #ኢየሱስ
.jpeg)
