I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
እነሆ፥ እኔና እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች ለእስራኤል በጽዮን ተራራ ከሚኖረው ከሠራዊት ጌታ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምልክትና ተአምራት ነን። ኢሳያስ 8፡18 ለእግዚአብሄር ክብር ተፈጥረናል፡፡ የእ...
-
እኛ የተፈጠርነው ለእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡ የተፈጠርነው ሌሎችን ለማገልገል ነው፡፡ ገንዘብን መስጠት ገንዘብን እንደመስራት በጣም ወሳኝ የሆነ ልምምድ ነው፡፡ እግዚአብሄር የሚሰጠን ገንዘብ የምንበላውና የምንዘራው ...
-
አዲሱን አመት በእውነት አዲስ የሚያደርገው በአዲሱ የእግዚአብሔር በተሰብ ውስጥ መሆናችን ነው። ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ አዳኝ ካልተቀበልን በስተቀር የእግዚአብሔር ልጆች መሆን በፍጹም አንችልም። እውነት ነው ሰይጣን የፈጠር...
-
ምስክርነት በህይወታችን የቀመስነውን የኢየሱስ ክርስቶስን ነፃነት ለሌሎች የምናካፍልበት መንገድ ነው፡፡ ምስክርነት እጅግ ታላቅ ሃይል ያለው ስራ ነው፡፡ ምስክርነት ወይም ወንጌልን መስበክ ምን እንደሆነ ከመፅሃፍ ቅዱስ ...
-
እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ። 1ኛ ጢሞቴዎስ 3፡16...
-
የተፈጠርነውና በምድር ያለነው ለእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡ በምድር ያለነው ያለንበት ዋነኛው ምክኒያት ለመብላት ለመጠጣትና ለመልበስ አይደለም፡፡ በምድር ያለነው የእግዚአብሄርን ስራ ለመስራት ነው ፡፡ በምድር ያለነው ስ...
-
የሆነው ነገር እርሱ የሚሆን ነው፥ የተደረገውም ነገር እርሱ የሚደረግ ነው፤ ከፀሐይም በታች አዲስ ነገር የለም። መክብብ 1፡9 በምድር ላይ ቢሆንልኝ ብለን እጅግ ስንመኘው የነበረ ስናገኘው ለ...
-
ሰይጣን ከመጀመሪያ ጀምሮ የሰው ልጆችን የሚያጠቃው በውሸት ነው፡፡ ሰይጣን ወደሄዋን መጥቶ ያታለላት እግዚአብሄር ከበላችሁ ትሞታላችሁ ያለውን አትሞቱም ብሎ በመዋሸት ነበር፡፡ ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን...
Wednesday, October 30, 2024
የአሜሪካ የፕሬዝዳንታዊነት ምርጫ
Tuesday, October 29, 2024
ሀሎዊን ክፍል 2
ሃሎዊን Halloween የሚባለው በአል በኦክቶበር ወር መጨረሻ ላይ በተለያየ መልኩ ይከበራል፤ ባብዛኛው ህዝብ ዘንድ እንደ አንድ ባህል የሚከብረው ይህ የሃሎዊን በአል ሰዎች ቢገባቸውም ባይገባቸውም መንፈሳዊ እንደምታ የለውም ማለት ግን አይቻልም።
ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ እንጂ ስለሌላ አይመጣም የተባለው ጠላት ዲያቢሎስ ባገኘው አጋጣሚ የሰዎችን ህይወት ይሰርቃል ያርዳል ያጠፋል።
ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። የዮሐንስ ወንጌል 10፣10
ሰይጣን በእግዚአብሄር ይፈጠር የእግዚአብሄር መላክ የነበር ሳጥናኤል ነበር። ሳጥናኤል ሰይጣን የሆነው እና እርሱን ከተከተሉት የወደቁት መላእክት ጋር ከእግዚአብሄር ፊት ወደ ምድር የተጣለው በትእቢት እንደ እግዚአብሄር ሊሆን ስለፈለገ ነበር።
መኖሪያቸውንም የተዉትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁትን መላእክት በዘላለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ቀን ፍርድ ድረስ ጠብቆአቸዋል። የይሁዳ መልእክት 1:6
ሰይጣን ዲያብሎስ የእሳት ባህር ቅጣት ተዘጋጅቶልታል።
እስክዚያ ግን የቻለውን ያህል ሰው አታልሎ ብዙ ሰዎችን ወደ እሳት ባህር መሄድ ይፈልጋል። የእሳት ባህር ለሰው ያልተዘጋጀ ቢሆንም እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ ያልተቀበሉ ሁሉ ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር ይጣላሉ።
እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ የተቀብሉ ብቻ ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም አይለያዩም ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር አይጣሉ።
በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ። የማቴዎስ ወንጌል 25:11
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
#ሰይጣን #ሀሎዊን #ሃሎዊን #ጠላት #ዲያቢሎስ #አቢይዋቁማ #ኢየሱስጌታ #ኢየሱስ
.jpeg)
