እግዚአብሔር
እንዲህ ይላል፦ በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹንም ክንዱ የሚያደርግ ልቡም ከእግዚአብሔር የሚመለስ ሰው ርጉም ነው። በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ ይሆናል፥ መልካምም በመጣ ጊዜ አያይም፤ ሰውም በሌለበት፥ ጨው ባለበት ምድር በምድረ በዳ በደርቅ ስፍራ ይቀመጣል። ትንቢተ ኤርምያስ 17፡5-6
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና . . . ማቴዎስ 28፡18 በመጀመሪያ ሰው ከሙሉ ስልጣን ጋር ተፈጥሮ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ ...
-
ኢየሱስ ወደምድር የመጣው በስጋ ነው፡፡ ኢየሱስ የመጣው ከሰው ልጅ ተወልዶ ሰው ሆኖ ነው፡፡ ኢየሱስ ሰው ሆኖ የመጣው በሰው የተሰራውን ሃጢያት በሰውነት ለመክፈል ነው፡፡ እንግዲህ በአንድ በደል ምክንያት ፍ...
-
የፈጠረን እግዚአብሄር ሁለንተናችንን ያውቃል፡፡ እግዚአብሄር በውጫዊ ነገራችን አይወሰድም፡፡ እግዚአብሄር ፊትን አያየም፡፡ እግዚአብሄር የፊትን መልክ አይቶ አይሳብም፡፡ እግዚአብሄር ቁመናችንን አይቶ አይደነቅም፡፡...
-
የማቴዎስ ወንጌል 22:1-14 1 ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ፦ 2 መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች። 3 የታደሙትንም ወደ ሰር...
-
People are devoted to get the right recipe for success. They study life and people diligently. They come up with many tactics and strat...
-
ከከንቱ ኑሮአችንም የተገዛነው እና የተዋጀነው በክርስቶስ ደም ነው፡፡ ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክ...
-
ብዙ ሰዎች አንደኛ መሆን ይፈልጋሉ፡፡ አንደኛ መሆን ምንም ጥፋተኛ የለበትም፡፡ ኢየሱስ ፊተኛ መሆን የሚፈልግህ ንስሃ ይግባ አይደለም ያለው፡፡ ፊተኛ የሚሆንበትን መንገዱን ነው እንጂ ያሳየው በፍፁም አልገሰፀም፡፡ አን...
-
ዕብራውያን 11 ፡ 1-40 እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው። ለሽማግሌዎች የተመሰከረላቸው በዚህ ነውና። ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እ...
-
እንዲሁም፥ እናንተ ሚስቶች ሆይ፥ ከባሎቻችሁ አንዳንዱ ለትምህርት የማይታዘዙ ቢኖሩ፥ በፍርሃት ያለውን ንጹሑን ኑሮአችሁን እየተመለከቱ ያለ ትምህርት በሚስቶቻቸው ኑሮ እንዲገኙ ተገዙላቸው። ...
Sunday, January 6, 2019
Friday, January 4, 2019
የወርቅ ቀለበት በእርያ አፍንጫ እንደ ሆነ፥ ከጥበብ የተለየች ቆንጆ ሴትም እንዲሁ ናት። መጽሐፈ ምሳሌ 11፡22 ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች። መጽሐፈ ምሳሌ 31፡30
የወርቅ
ቀለበት በእርያ አፍንጫ እንደ ሆነ፥ ከጥበብ የተለየች ቆንጆ ሴትም እንዲሁ ናት። መጽሐፈ ምሳሌ 11፡22
ውበት
ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች። መጽሐፈ ምሳሌ 31፡30
Wednesday, January 2, 2019
ንስሃ ያለመግባት አራቱ አደጋዎች
ንስሃ ማለት በአስተሳሰቡ በንግግሩና በአካሄዱ ከእግዚአብሄር ቃል የወጣ ሰው የሚያደርገው የሃሳብ ወይም የመንገድ ለውጥ ማለት ነው፡፡ እንደ እግዚአብሄር ቃል ያልኖረ ሰው ከቃሉ ሲወጣ መንገዱን ማስተካከል አለበት፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር መንገድ ተቃራኒ እየሄደ ካለ ቀኝ ኋላ ዙር ብሎ መመለስ አለበት፡፡
ሰው ግን ንስሃ ካልገባ እነዚህ አምስት አደጋዎች ከፊቱ እንደሚጋረጡ የእግዚአብሄር ቃል ያስትምራል፡፡
1. ሰው በአመፁ ንስሃ ካልገባ በስተቀር በአመፁ መቀጠሉ የማይቀር ነው፡፡
ንስሃ መግባት ሃጢያትን ከህይወት ነቅሎ እንደመጣል ነው፡፡ ሰው ከሃጢያት መንገዱ ካልተመለሰ በስተቀር ስንፍናውን ለመሸፈን ስንፍናውን መድገሙ የማይቀር ነው፡፡ ሰው ከሃጢያቱ ቶሎ ካልተመለሰ አመፃው የሰራለት ስለሚመስለው በሌላው ሰው ላይ ይደግመዋል፡፡ ሰው ሃጢያት ባሰራው በስጋው ላይ ካልጨከነ በስተቀር ሃጢያቱ ለስጋው ስለሚጥመው ደግሞ በሌላ ሰው ላይ ያሰራዋል፡፡
ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡27
ሰው በሃጢያተኛ ባህሪው በስጋው ላይ ካልጠነከረበት በስተቀር ስጋ የሃጢያት ፍላጎቱ ይበልጥ ስለሚከፈት ይበልጥ ሃጢያትን መስራት ይፈልጋል፡፡ ሰው በሃጢያቱ ንስሃ ካለገባ ሃጢያቱ በሃጢያቱ ላይ እየተከመረ ይሄዳል፡፡
ወደ ቤቶች ሾልከው እየገቡ፥ ኃጢአታቸው የተከመረባቸውን በልዩ ልዩ ምኞትም የሚወሰዱትን ሁልጊዜም እየተማሩ እውነትን ወደ ማወቅ ሊደርሱ ከቶ የማይችሉትን ሞኞችን ሴቶች የሚማርኩ፥ ከእነዚህ ዘንድ ናቸውና። 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3፡6-7
2. ሰው በሃጢያቱ ንስሃ ካልገባ ራሱን ያታልላል፡፡
እግዚአብሄር በሃጢያቱ ቢቀጣውም ባይቀጣውም ሰው በሃጢያቱ ንስሃ እንዲገባ እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡ ሰው ግን በሃጢያቱ ንስሃ ካልገባና በአመፃ ከተሳካለት እየተታለለ ይሄዳል፡፡ ሰው ንስሃ ካልገባ ክፋት የማይሰሩ ሰዎች ሞኞች እንደሆኑ እያሰበ ይመጣል፡፡ ሰው በአመጹ ንስሃ ካልገባ ክፋት የማይሰሩ ሰዎች እንዳልገባቸው እና እንደተሸወዱ እርሱ ግን ጥበበኛ እንደሆነ ስለሚመስለው በእግዚአብሄር ጥበብ የሚኖሩትን ሰዎች ሞኝ ያደርጋል ይንቃል፡፡
ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮ ሆኑ፥ ወደ ሮሜ ሰዎች 1፡22
ሰው ንስሃ ካልገባ ለራሱ ጥበበኛ የሆነ ይመስለዋል ነገር ግን በምድር በስጋና በአጋንንት ጥበብ ስለሚኖር ሞኝ እየሆነ ነው፡፡
ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም፤ ነገር ግን የምድር ነው፥ የሥጋም ነው፥ የአጋንንትም ነው፤ ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ስራ ሁሉ አሉና። የያዕቆብ መልእክት 3፡15-16
3. ሰው በሃጢያቱ ንስሃ ካልገባ በዙሪያው ላሉት ሰዎች አመፅና ክፋት ትክክልኛ እንደሆነ በድርጊቱ ምሳሌ ይሆናቸዋል፡፡
ወደድንም ጠላንም የሚያዩንና ድርጊታችንን አውቀውም ይሁን ሳውቁት የሚከተሉ ሰዎች አሉ፡፡ ንስሃ የማይገባ ሰው ለሚያዩትና ለሚሰሙት መጥፎ ምሳሌ ይሰጣቸዋል፡፡ ንስሃ የማይገባና በአመፁ የሚቀጥል ሰው በአካባቢው ሰዎች በድርጊቱ አመፅ ትክክል ነው ብሎ ያስተምራቸዋል፡፡ ንስሃ የማይገባና በክፋቱ የሚቀጥል ሰው ለወንድም ለእህቶቹ ፣ ለሚስቱ ፣ ለልጆቹና ለሚመጣው ትውልድ መልካሙን እንዳይከተሉ መጥፎ ምሳሌ ይተውላቸዋል፡፡
አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፡33
4. ሰው በሃጢያቱ ንስሃ ካልገባ ከመንፈስ ወቀሳና ከእግዚአብሄር ህልውና እየራቀ ይሄዳል፡፡
እንደሳተ ሲያውቅ በፍጥነት ንስሃ የማይገባ ሰው ህሊናው እየደነዘዘ አመፅ ማድረግ ይበልጥ እየቀለለው ይሄዳል፡፡
መንፈስ ግን በግልጥ፦ በኋለኞች ዘመናት አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በውሸተኞች ግብዝነት የተሰጠውን የአጋንንትን ትምህርት እያደመጡ፥ ሃይማኖትን ይክዳሉ ይላል፤ በገዛ ሕሊናቸው እንደሚቃጠሉ ደንዝዘው፥ 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4፡1-2
ሰው ንስሃ ካልገባ የመዳንን ደስታ እያጣው ይሄዳል፡፡ ሰው ንስሃ ካልገባ በእግዚአብሄር ህልውና ውስጥ የሚገኘውን ደስታ እያጣው ይሄዳል፡፡
አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ። ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ። የማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ። መዝሙረ ዳዊት 51፡10-12
ሰው በአመፃው ሲቀጥል በእግዚአብሄር ፊት ያለውን ድፍረት እያጣው ይሄዳል፡፡ ሰው በአመፃ ሲቀጥል በእምነት ኑሮያለውን ገድልና ደስታ እያጣው በሰው ሰራሽ ነገር እየተካው ይሄዳል፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ጌታ #ኢየሱስ #ሃሳብ #ቃል #እግዚአብሄር #መንፈስቅዱስ #ንስሃ #መለወጥ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #አእምሮ #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
Subscribe to:
Posts (Atom)