I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና . . . ማቴዎስ 28፡18 በመጀመሪያ ሰው ከሙሉ ስልጣን ጋር ተፈጥሮ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ ...
-
ኢየሱስ ወደምድር የመጣው በስጋ ነው፡፡ ኢየሱስ የመጣው ከሰው ልጅ ተወልዶ ሰው ሆኖ ነው፡፡ ኢየሱስ ሰው ሆኖ የመጣው በሰው የተሰራውን ሃጢያት በሰውነት ለመክፈል ነው፡፡ እንግዲህ በአንድ በደል ምክንያት ፍ...
-
የፈጠረን እግዚአብሄር ሁለንተናችንን ያውቃል፡፡ እግዚአብሄር በውጫዊ ነገራችን አይወሰድም፡፡ እግዚአብሄር ፊትን አያየም፡፡ እግዚአብሄር የፊትን መልክ አይቶ አይሳብም፡፡ እግዚአብሄር ቁመናችንን አይቶ አይደነቅም፡፡...
-
የማቴዎስ ወንጌል 22:1-14 1 ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ፦ 2 መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች። 3 የታደሙትንም ወደ ሰር...
-
People are devoted to get the right recipe for success. They study life and people diligently. They come up with many tactics and strat...
-
ከከንቱ ኑሮአችንም የተገዛነው እና የተዋጀነው በክርስቶስ ደም ነው፡፡ ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክ...
-
ብዙ ሰዎች አንደኛ መሆን ይፈልጋሉ፡፡ አንደኛ መሆን ምንም ጥፋተኛ የለበትም፡፡ ኢየሱስ ፊተኛ መሆን የሚፈልግህ ንስሃ ይግባ አይደለም ያለው፡፡ ፊተኛ የሚሆንበትን መንገዱን ነው እንጂ ያሳየው በፍፁም አልገሰፀም፡፡ አን...
-
ዕብራውያን 11 ፡ 1-40 እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው። ለሽማግሌዎች የተመሰከረላቸው በዚህ ነውና። ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እ...
-
እንዲሁም፥ እናንተ ሚስቶች ሆይ፥ ከባሎቻችሁ አንዳንዱ ለትምህርት የማይታዘዙ ቢኖሩ፥ በፍርሃት ያለውን ንጹሑን ኑሮአችሁን እየተመለከቱ ያለ ትምህርት በሚስቶቻቸው ኑሮ እንዲገኙ ተገዙላቸው። ...
Monday, February 28, 2022
Saturday, February 26, 2022
Tuesday, February 22, 2022
Friday, February 18, 2022
Sunday, February 13, 2022
የፍቅር ምንጭ
ስለ ፍቅር ብዙ ይዘከራል ይወራል፡፡
ሁሉም
ሰው ይህ የሚዘመርለትንና የሚሰበክለትን ፍቅር ማወቅ ፣ መኖር እና ማጣጣም ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን ወደ ተግባር ሲመጣ ፍቅር በተግባር
ሊተረጎም የማይችል ረቂቅ ነገር ብቻ ይሆንበታል፡፡
ሰው
ደግሞ እውነተኛውን ፍቅርን ካልተረዳ ተመሳሳዩን ምኞትን እንደፍቅር ይዞት ባነሰ ነገር ረክቶ ይኖራል፡፡
ፍቅር
ግን ምኞት አይደለም፡፡ ፍቅር ስሜት አይደለም፡፡ ፍቅር ከፍ ያለ የህይወት ደረጃ ነው፡፡
ስለፍቅር
የሚናገሩትን መፅሃፍት በማንበብ ፍቅር አይመጣም፡፡ ፍቅር ከሰው አይመጣም፡፡ ሰው ራሱ ፍቅርን የተራበ እና ፍቅር የሚያስፈልገው
ፍጥረት ስለሆነ ፍቅርን በራሱ ሊሰጥ አይችልም፡፡
ፍቅር
የሚመጣው ፍቅር ከሆነው ከእግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሔር
ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል። 1ኛ ዮሐንስ 4፡16
ፍቅርን
ሊያውቅ በፍቅር ሊኖር የሚችለው በእግዚአብሄር የሚኖር ሰው እግዚአብሄርም በእርሱ የሚኖርበት ሰው ብቻ ነው፡፡
ሰው
ፍቅርን ከእግዚአብሄር ካላገኘ ምኞትን እንጂ ፍቅርን በፍፁም ሊያውቀው አይችልም፡፡
ሰው
ከእግዚአብሄር ፍቅርን ካልተቀበለ ፍቅርን ተቀብሎ አያውቅም፡፡ ሰው በእግዚአብሄር ፍቅር ጉልበት ካላገኘ በእውነተኛ ፍቅር ሌላውን
የሚወድበት አቅም አይኖረውም፡፡
ሰው
ምክኒያታዊ ያልሆነውን እውነተኛውን ፍቅርን መማር የሚችለው ፍቅር ከሆነው ከእግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን
ፍቅር የቀመሰ ሰው ብቻ እውነተኛውን ፍቅር ያውቃል፡፡
የእግዚአብሄርን
ፍቅር የቀመሰ ሰው ብቻ የተቀበለውን ፍቅር ለሌላው መስጠት ይችላል፡፡
በተሰጠንም
በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም። ሮሜ 5፡5
በእግዚአብሄር
ፍቅር የረካ ሰው ብቻ ሌላውን ሰው በፍቅር ሊያረካ ይችላል፡፡
ሰው
የእግዚአብሄርን ፍቅር በተቀበለ መጠን የእንካ በእንካ ያልሆነውን ፍቅር ለሌላው መስጠት ይችላል፡፡
Abiy Wakuma Dinsa አቢይ ዋቁማ
ዲንሳ
ለተጨማሪ
ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ
መልእክቶች
https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ
#ጌታ #እምነት #ፍቅር #ስር #መሰረት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #ከቅዱሳንሁሉጋር #መታበይ #መመካት #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ