Popular Posts

Tuesday, May 29, 2018

የችግሩ ስርና መሰረት

ወንድሞች ሆይ፥ እርስ በርሳችሁ አትተማሙ። ወንድሙን የሚያማ በወንድሙም የሚፈርድ ሕግን ያማል በሕግም ይፈርዳል፤ በሕግም ብትፈርድ ፈራጅ ነህ እንጂ ሕግን አድራጊ አይደለህም። ያዕቆብ 4፡11
ወንድሙን የሚያማ ሰው ችግሩ ወንድሙ ይመስለዋል፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው ዋናው ችግሩ ወንድሙ አይደለም፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው የችግሩ ስርና መሰረት ቢጠና ወንድሙ ሳይሆን ወንደሙን የሚያማ ሰው ችግሩ ህጉ ራሱ ነው፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው እውነተኛ ችግሩ ከወንድሙ ጋረ ሳይሆን ከህጉ ጋረ ነው፡፡  
ወንደሙን የሚያማ ሰው ህጉን ያማል፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው በቀጥታ ወንደሙን በተዘዋዋሪ ህጉን ያማል፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው ህጉ አስቸጋሪ እንደሆነ ፣ ህጉ ቀላል እንዳይደለና ህጉ ለመፈፀም እንደሚከብድ ህጉን እያማው ነው፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው በህጉ ላይ ያለውን ተቀባይነት እያማ ነው፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው ህጉ ችግር አለበት እያለ ነው፡፡   
ወንድሙን የሚያማ ሰው ህጉን ስለሚያማ ዛሬ ህጉን በተዘዋዋሪ እንደተቃወመው ሁሉ ነገ ደግሞ ህጉን ላይ በቀጥታ ይቃወመዋል፡፡ ወንድሙን የሚያማ በተዘዋዋሪ ህጉን ስለሚያማ እና በተዘዋዋሪ ወንድሙን ስለሚደግፍ ነገ ህጉን ለመቃወም ለራሱ እያመቻቸ ነው፡፡ ዛሬ ወንድሙን የሚያማ ውስጥ ሰው ውስጡን ህጉን ስለሚያማ ህጉን ለመፈፀም አቅም እያጣ ይሄዳል፡፡
በጣም ሰውን የሚያሙ ሰዎችን ስትመለከቱ ብዙ ጊዜ በሚያሙበት በዚያው ነገር ውስጥ ወድቀው ይገኛሉ፡፡ ምክኒያቱም ሰውን የሚያሙ ሰዎች ያን ወንድም ሃጢያት ያሰራው ያው ስጋ በእነርሱ እንደሚኖር አይረዱትም፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው ወንድሙን የሚያማው በትምክት ነው፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው ወንድሙን የሚያማው እኔ እበልጣለሁ ከሚል የትምክት ስሜት ነው፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው ወንድሙን የሚያማው በጭካኔ ነው፡፡ በርህራሄ ወንድሙን የሚያማ ሰው የለም፡፡ በትህትና ወንድሙን የሚደግፍ የሚያነሳ የሚረዳ እንጂ ወንድሙን እንደ ባዕድ የሚያማ ሰው የለም፡፡  
ወንድሞች ሆይ፥ ሰው በማናቸውም በደል ስንኳ ቢገኝ፥ መንፈሳውያን የሆናችሁ እናንተ እንደዚህ ያለውን ሰው በየውሃት መንፈስ አቅኑት፤ ከእናንተ እያንዳንዱ የአንዱን ሸክም ይሸከም እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ። ገላትያ ሰዎች 6፡1-2
ወንድሙን የሚያማ ሰው ወንድሙ ህጉን እንዲጠብቅ የሚያደረገው ምንም አስተዋፅኦ የለም፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው የቤተሰብነት ስሜት የጠፋበት ሰው ነው፡፡ ወንደሙን የሚያማ ሰው ለቤተሰቡ ህጉን መጠበቅ የሚያደርገው አስተዋፅኦ የለም፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው ወንድሙ ህጉን እንዲጠብቅ የሚረዳው ምንም ነገር የለም፡፡
ነገር ግን በፍቅር እርስ በርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ። ሕግ ሁሉ በአንድ ቃል ይፈጸማልና፥ እርሱም፦ ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የሚል ነው። ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱና ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ።  ገላትያ ሰዎች 5፡13-15
ወንድሙን የሚያማ ሰው ቤተሰቡን እንደ እንግዳ እያየው ነው፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው የወንድሜ ገመና የእኔ ገመና ነው አይልም፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው ከራሱ የቤተሰብ አባል ጋር ከንቱ ፉክክር ውስጥ ገብቶዋል፡፡
አንድም ብልት ቢሣቀይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ይሣቀያሉ፤ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል። 1ኛ ቆሮንቶስ 12፡26
ወንድሙን የሚያማ ሰው ላይላዩን በወንድሙ መውደቅ የተናደደ ይመስላል እንጂ ውስጥ ውስጡን በወንድሙ መውደቅ ደስ ብሎታል፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው በወንድሙ መውደቅ ራሱን ከፍ ሊያደርግ እየሞከረ ነው፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው የወንድሙ መውደቅ የእርሱ መክበር ይመስለዋል፡፡ ወንድሙን የሚያማ ሰው በወንድሙ መውደቅ አብሮ እንደወደቀ አያስበውም፡፡
አንዱ ምንም ሳይሆን ምንም የሆነ ቢመስለው ራሱን ያታልላልና። ነገር ግን እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሥራ ይፈትን፥ ከዚያም በኋላ ስለ ሌላው ሰው ያልሆነ ስለ ራሱ ብቻ የሚመካበትን ያገኛል፤ ገላትያ 6፡3-4
የሃሜት አላማ ሌላውን ማንሳት ፣ ሌላውን መጥቀም እና ሌላውን መርዳት አይደለም፡፡ የሃሜት ብቸኛው አላማ ሌላውን ማዋረድ ራስን ማክበር ስለሆነ በእግዚአብሄር ፊት አስፀጸያፊ ነው፡፡  
ወንድሞች ሆይ፥ እርስ በርሳችሁ አትተማሙ። ወንድሙን የሚያማ በወንድሙም የሚፈርድ ሕግን ያማል በሕግም ይፈርዳል፤ በሕግም ብትፈርድ ፈራጅ ነህ እንጂ ሕግን አድራጊ አይደለህም። ያዕቆብ 4፡11
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ህይወት #የሚፈርድ #የሚያማ #ወንጌል #መውደድ #ፍቅር #የህይወትምስክርነት #መታዘዝ #ማገልገል #መውደድ #እውነት #ትህትና #ትንሳኤ #ህይወት #ወንጌል #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ  #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment