Popular Posts

Saturday, September 5, 2026

የጩኸት ህይወት

መዝሙር 19:1 ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል።

መዝሙር 19:2 ቀን ለቀን ነገርን ታወጣለች፥ ሌሊትም ለሌሊት እውቀትን ትናገራለች።

መዝሙር 19:3 ነገር የለም መናገርም የለም፥ ድምፃቸውም አይሰማም።

መዝሙር 19:4 ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ፥ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ።

ተፈጥሮ በስራው ካለቃል እና ንግግር በስራው ብቻ ስለእግዚአብሔር ክብር ይናገራሉ። 

አንድ አባባል አለ። ወንጌልን ስበክ አስፈላጊ ከሆነ ቃልን ተጠቀም። 

በቀዳሚነት ወንጌልን የሚሰብው ህይወታችን ነው። 

እግዚአብሔርን የመፍራት ህይወት ሲኖረን በህይወታችን ብቻ ሌሎች እግዚአብሔርን እንዲፈሩ እናስገድዳለን እናስፈራራለን። 

መልካም ስራችን ስለእግዚአብሔር መልካምነት በጩኸት ይናገራል። 

ማቴዎስ 5:16 መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።

የሚያስችለው ሀይል የእግዚአብሔር ፀጋ በህይወታችን ሲገለጥ ሰዎችን የሚቀሰቅስ ሀያል ጩኸት ነው። 

ንፁህ ህይወት ከሩቅ የሚሰማ ጬኸት ነው። 

1 ጴጥሮስ 3:1-2 እንዲሁም፥ እናንተ ሚስቶች ሆይ፥ ከባሎቻችሁ አንዳንዱ ለትምህርት የማይታዘዙ ቢኖሩ፥ በፍርሃት ያለውን ንጹሑን ኑሮአችሁን እየተመለከቱ ያለ ትምህርት በሚስቶቻቸው ኑሮ እንዲገኙ ተገዙላቸው።

1 ጴጥሮስ 3:3 ለእናንተም ጠጕርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጎናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ፥

1 ጴጥሮስ 3:4 ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ።

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

Wednesday, July 29, 2026

በፊቱም ልባችንን እናሳርፋለን፥ እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነውና ሁሉንም ያውቃል። 1ኛዮሐንስ 3:19-20

 በፊቱም ልባችንን እናሳርፋለን፥ እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነውና ሁሉንም ያውቃል።

1ኛዮሐንስ 3:19-20 


Sunday, May 17, 2026

የምንሞትለት እንጂ የምንገድልለት አምላክም ሆነ ሀይማኖት የለንም!

 የምንሞትለት እንጂ የምንገድልለት አምላክም ሆነ ሀይማኖት የለንም! 


አምላክ ሀያል ነው የእኛ እርዳታ አይፈልግም። እንዲገድሉለት የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት እውነተኛ ሀይማኖት አይደለም። የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት ሀሰተኛ ሀይማኖት ነው። የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት ከሰይጣን ነው። 

ብዙ ሀይማኖቶች በምድር ላይ ቢኖሩም በአጠቃላይ ምድር ላይ ያሉት ሁለት አይነት ሀይማኖቶች ብቻ ናቸው። በምድር ላይ እውነተኛ እና ሀሰተኛ ሀይማኖት አለ። እግዚአብሔር አንድ ነው። ከአንድ በላይ እውነተኛ ሀይማኖት ሊኖር አይችልም። በአለም ላይ ከአንድ በላይ  ሀሰተኛ ሀይማኖት ሊኖር ግን ይችላል። 

ታዲያ ሀይማኖት መያዙ ሳይሆን እውነተኛውን አምላክ መያዛችንን እርግጠኛ እንሁን። እኔን በተመለከተ ፍለጋ አቁሜያለው እውነተኛውን አምላክ አግኝቻለሁ።

እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። ዮሐንስ 17:3 ሁሉም ሀይማኖት ወደ አንድ ፈጣሪ ያደርሳል የሚሉ በሰይጣን የተታለሉ ናቸው። 

ኢየሱስም አለው፡— እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። ዮሐንስ 14:6 

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa 

Sunday, April 12, 2026

ከእርሱ ጋር አስነሣን !



ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፣6 7

ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው ስለእኛ ነው። ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው እኛ በሃጢያታችን ምክኒያት ቅዱስ ከሆነው ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላላም እንዳንለያይ ነው።

ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና። ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፣21 22

ክርስቶስ ኢየሱስ የሞተው እኛ በሃጢያታችን መሞት የነበረበንን ሞት ነው። ክርስቶስ የሞተው በእኛ ምትክ ነው። ክርስቶስ የሞተው ለእኛ ነው።

በመጀመሪያ ሰው የተፈጠረው ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላላም እንዲኖር ነበር። በእግዚአብሔር የተፈጠረው ሃጢያትን የማያውቅ  ፍጹም ሰው ነበር።

ሰው ከእግዚአብሔር የተለየው ሃጢያት በሰራ ጊዜ ነበር።

እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤ ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና። ዘፍጥረት 2፣16  17

ክርስቶስ የመጣው እኛ ወደፊት እንዳንሞት ከእግዚአብሔርም ጋር ለዘላላም እንዳንለያይ ነው።

ክርስቶስ ሃጢያት ያልተገኘበት ፍጹም ነው። ክርስቶስ መሞት አይገባውም  ነበር። ክርስቶስ የሞተው እኛ ሞት ሰለሚገባን ነበር። ክርስቶስ የሞተው እኛን ከሞት ሊያስነሳን በእኛ ምትክ ነው።  

ክርስቶስ የሞተው ለእኛ ትንሳኤን ሊሰጠን ነው።

እኛ ከክርስቶስ ጋር አብረነው ካልተነሳን ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።

የክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ "ከእለታት አንድ ቀን ክርስቶስ ከሞት ተነሳ" ብለን ብቻ የምናስታውሰው የክርስቶስ ታሪክ አይደለም። የክርስቶስ ትንሳኤ የእኛም ከሙታን የመነሳት ልምምድ ነው። በክርስቶስ ሞትና ተንሳኤ የምናምን ሁላችን ከሞት ተነስተናል።

ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥ በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፣5-7

የትንሳኤ በአል የክርስቶስ ብቻ ሳይሆን የእኛም የትንሳኤ በአል ነው።

መልካም የትንሳኤ በአል

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

Friday, November 28, 2025

የብልጽግና ወንጌል ምሥጢር ሲገለጥ


የብልጽግና ወንጌል ምሥጢር ሲገለጥ  

በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና። ወደ ሮሜ ሰዎች 1፡16

ወንጌል በሃጢያታቸው ምክኒያት  ለዘላለም ከእግዚአብሔር የተለያዩትን የሰው ልጆች  ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም እንዲኖሩ የሚያስችል ታላቅ የምስራች ነው። 

አሁን ግን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ ታይቶአል። እርሱ ሞትን ሽሮአልና እኔ ሰባኪና ሐዋርያ አሕዛብንም አስተማሪ እንድሆን በተሾምሁበት በወንጌል ሕይወትንና አለመጥፋትን ወደ ብርሃን አውጥቶአል። 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1:10-11

ወንጌል ጠላቶች የነበሩትን የሰው ልጆች በማስታረቅ የእግዚአብሔር ወንድና ሴት ልጆች አድርጎ መቀበል የሚያስችል ታላቅ የምስራች ነው።

ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ የዮሃንስ ወንጌል 1:12

ወንጌል በሃጢያት ምክኒያት ከሰይጣን የባርነት እስራት ወስጥ ሲሰቃዩ የነበሩትን የሰው ልጆች በሰይጣን ላይ ስልጣን የሚሰጥ የእግዚአብሔር ታላቅ የማዳኛ ሃይል ነው፡፡

እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። ወደ ዕብራውያን 2:14

#የብልጽግናወንጌል #ወንጌል #ኢየሱስ #የምስራች #እግዚአብሔር #የበለጸገ #መልካምዜና

Tuesday, January 28, 2025

Name it claim it Take it!

 



Name it claim it Take it!

“So Jesus answered and said to them, “Have faith in God. For assuredly, I say to you, whoever says to this mountain, ‘Be removed and be cast into the sea,’ and does not doubt in his heart, but believes that those things he says will be done, he will have whatever he says.”

‭‭Mark‬ ‭11‬:‭22‬-‭23‬ ‭NKJV‬‬

Jesus taught that we can speak to our mountains and have them removed. Jesus encouraged us to believe in God for the removal of our mountain by the word of our mouth.

Whoever believes in God will identify his need, look for a solution from the word, call it to be changed, and have the situation changed.

We look for the word to see the will of God for our lives. 

We have to believe God for it. Faith comes by hearing, and it comes by hearing the word of God. 

“So then faith comes by hearing, and hearing by the word of God.”

‭‭Romans‬ ‭10‬:‭17‬ ‭NKJV‬‬

Faith comes as soon as we know the will of God for our lives.

Once we know the will, we don’t stop thinking it will go away by itself.  We have actively claimed the desired result. Our confession must be aligned with our faith in our heart. We can't just believe and not confess thinking the work is done.

Once we confess what we believe from the word of God, we will have it.

It may take a while to manifest in the physical world, but in the spiritual, we have it already. We have to claim what we know the will of God for our lives is; we have to confess and call it into existence. And we will have it.

Name it claim it Take it!

Abiy Wakuma Dinsa

Thursday, January 2, 2025

ጸሎት እንዲመለስ የሚያደርገው

 

ጸሎት ከእግዚአብሄር ጋር መነጋገር ነው። ጸሎት ሊደረግ የሚችለው ከእግዚአብሄር ጋር በመግባባት ብቻ ነው። ጸሎት የሚሰምረው እንደ እግዚአብሄር አሳብ ስንጸልይ ብቻ ነው።

በአጠቃላይ ለእግዚአብሄር ያለን አመለካከት የጸሎታችንን ውጤታማነት ይወስናል።

ጸሎት ፍሬያማ የሚሆነው ለእግዚአብሄር የአምላክነት ስልጣን እውቅና በሰጠን መጠን ብቻ ነው። ጸሎት የሚሰምረው ከምስጋና ልብ ሲወጣ ብቻ ነው።

ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና። 1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 5፡17-18

ወደ እግዚአብሄር በጸሎት የመቅረብ አንደኛው ደንብ ወይም አሰራር ምስጋና ነው።

ልመናና ጸሎት ምልጃም መቅረብ ያለበት በምስጋና ብቻ ነው።

እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:1-2

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ  Abiy Wakuma Dinsa        

#እግዚአብሔርንመምሰል #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #አበሻ #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አዲስአመት #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፀሎት #ሀበሻ #ምስጋና