apostle Abiy Wakuma Dinsa
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
በፊቱም ልባችንን እናሳርፋለን፥ እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነውና ሁሉንም ያውቃል። 1ኛዮሐንስ 3:19-20
-
ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2 ፣6 7 ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው ስለእኛ ነው። ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው እኛ በሃጢያታችን...
-
Kanaafis Waaqayyo ofii isaatii milikkita isiniif in kenna; kunoo, durbi in ulfoofti, ilmas in deessi, maqaa isaas Amaanu'el jettee in mo...
-
Name it claim it Take it! “So Jesus answered and said to them, “Have faith in God. For assuredly, I say to you, whoever says to this mount...
-
የብልጽግና ወንጌል ምሥጢር ሲገለጥ በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና። ወደ ሮሜ ሰዎች 1፡16 ወንጌል በሃጢያታቸው ምክኒያት ለዘላለም ከእ...
-
ጸሎት ከእግዚአብሄር ጋር መነጋገር ነው። ጸሎት ሊደረግ የሚችለው ከእግዚአብሄር ጋር በመግባባት ብቻ ነው። ጸሎት የሚሰምረው እንደ እግዚአብሄር አሳብ ስንጸልይ ብቻ ነው። በአጠቃላይ ለእግዚአብሄር ያለን አመለካከት ...
-
የምንሞትለት እንጂ የምንገድልለት አምላክም ሆነ ሀይማኖት የለንም! አምላክ ሀያል ነው የእኛ እርዳታ አይፈልግም። እንዲገድሉለት የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት እውነተኛ ሀይማኖት አይደለም። የሰውን እርዳታ የሚፈልግ...
-
እግዚአብሄር - አባት የሁልጊዜ ነው፡፡ አባት ስሜቱን ዋጥ ያደርጋል፡፡ አባት ተለዋዋጭ ስሜቱን አይከተልም፡፡ አባት በመርህ ይመራል፡፡ ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በ...
-
ብዙ ጊዜ የምናተኩረው በክርስቶስ ስለተደረገልን ነገር ነው፡፡ በክርስቶስ የተደረገልን ነገር ሁሉ ያልለፋንበት ስጦታ ነው፡፡ በክርስቶስ ይህ ሁሉ ነገር ተፈደርጎልንም ለሃላፊነት የማንበቃ ህፃናት ልንሆን እንችላለን፡፡ ...
-
God created man in his image, after his likeness. One of the most important characters God wants to see in us in gentleness. Gentleness c...
Wednesday, September 9, 2026
እውነተኛው የዘመን አቆጣጠር
ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ፤ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችሁ። ኦሪት ዘጸአት 12:2
እውነተኛው አዲስ አመት የሚባለው ቃሉን ሰምተን ነጻ የምንወጣበትን ጊዜ ነው። እውነተኛው ዘመን መለወጫ የሚባለው ቃሉን ሰምተን በቃሉ የዳንንበት ቀን ነው።
ዘጸአት ምዕራፍ 12 በአጠቃላይ እግዚአብሔር ለእስራኤል ከግብፅ ነፃ በወጡበት ወቅት አዲስ ጅምር ያደረገበት ምዕራፍ ነው።
ዘጸአት 12፡2 — እግዚአብሔር ለሙሴና ለአሮን እንዲህ አላቸው፦ «ይህ ወር ለእናንተ የወሮች መጀመሪያ፣ የዓመቱም የመጀመሪያ ወር ይሁንላችሁ።»
እስራኤላዊያን ሊያድናቸው የመጣውን የእግዚአብሄር ቃል ሰምተው ከግብጽ ባርነት ነጻ የወጡበትን ቀን የወሩ መጀመሪያ ወሩን ደግሞ የአመቱ መጀምሪያ እንዲሆን ተነገራቸው።
ቀናቸውን እና ወራቸውን አንድ ብለው የጀመሩት ከነጻነታቸው ቀን ጀምረው ነው።
ዘጸአት 13፡3–4 ደግሞ ይህንን አዲስ ቀን እና አዲስ ወር ከግብፅ ነፃ ከመውጣታቸው ጋር ይገናኛል።
በመጽሐፍ ቅዱስ እይታ፣ «አዲሱ ዓመት» የሚቀርበው እንደ ቀላል የቀን መቁጠሪያ ለውጥ ብቻ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ቤዛነትና ነፃ ማውጣት የተፈጠረ አዲስ ጅምር እንደሆነ ነው።
ዛሬም እውነተኛ ነጻነት የእግዚአብሄርን ቃል ሰምተን ነጻ የምንወጣበት ነጻነት ነው።
ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ፦ እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። የዮሃንስ ወንጌል 8፡31፣ 32
አዲስ ዘመንም የእግዚአብሄርን ቃል ሰምተን ነጻ የወጣንበትን ቀን ነው።
እውነተኛው ዘመን መለወጫ ደግሞ የዘመን መቁጠሪያ ካላንደር ሳይሆን በእግዚአብሄር ቃል ነጻ የምትወጡበት ቀን ነው።
ነገር ግን ነጻ የሚያወጣውን ፍጹሙን ሕግ ተመልክቶ የሚጸናበት፥ የያዕቆብ መልእክት 1:25
በቃሉ ነጻ ለወጣ ሰው ጷጉሜ 5 የዘመን መለዋጫ ነው። የእግዚአብሄርን ቃል ሰምቶ ነጻ ለማይወጣበት ሰው ግን በመስከረም 1 እንኳን ዘመኑን አይለወጥም።
ስለዚህ ጥያቄው የእግዚአብሄርን ቃል በመስማት እና በማድረግ ዘመናችሁን ለመለወጥ ተዘጋጅታችኋል ወይስ ዘመኑ በራሱ ህይወቴን ይለወጣል ብላችሁ በከንቱ ተስፋ እያደረጋችሁ ነው ?
ህይወትን የሚለወጥ የእግዚአብሁሄር ቃል ብቻ ነው። ቀን ያው የተለመደው ተመሳሳይ ሰኞ ማክሰኞ ሮብ ሃሙስ አርብ ቅዳሜ እሁድ ነው። የእግዚአብሄር ቃል ህይወታችንን ካልለወጠ ቀን ህይወትን ሊለውጥ አይችልም።
አዲስ አመት ህይወታችን በእግዚአብሄር ቃል እንዲለወጥ የመንፈቅድበት አዲስ እድል እንጂ በራሱ የህይወት ለወጥ አይደለም።
መልካም አዲስ አመት መልካም አዲስ ህይወት
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
Sunday, September 6, 2026
ከፀሎት በላይ
የጻድቅ ሰው ጸሎት ብዙ ነገር የመስራት እና የመለወጥ አቅም አለው።
ያዕቆብ 5:16 … የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።
ነገር ግን የእግዚአብሔር ሀይል በፀሎታችን አይወሰንም። እግዚአብሔር ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ይችላል።
ኤፌሶን 3:20 እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው፥
የእግዚአብሔር ለሚፀልዩት ብቻ ሳይሆን በሁሉም ፍጥረቱ ላይ ያለው አላማ የፍቅር ነው።
መዝሙር 145:9 እግዚአብሔር ለሚታገሡት ቸር ነው። ምሕረቱም በሥራው ሁሉ ላይ ነው።
1 ጢሞቴዎስ 6:17 … ደስም እንዲለን ሁሉን አትርፎ በሚሰጠን በሕያው እግዚአብሔር እንጂ….
እግዚአብሔር የሚያስፈልገንን ከእኛ በላይ ስለሚያውቅ ለእኛም የሚያደርግልን በምንፀልየው ላይ ብቻ ተወስኖ ሳይሆን ከምንለምነው ሁሉ በላይ ነው።
ማቴዎስ 6:8 … ሳትለምኑት አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ያውቃልና።
እግዚአብሔር ከአፋችን ቃል በላይ የልባችንን ጩኸት ሰምቶ ይመልሳል። እግዚአብሔር አውቀን ከፀለይነው በላይ የማናውቀውን ታላቅና ኃይለኛ ነገርን ያሳየናል።
ኤርምያስ 33:3 ወደ እኔ ጩኽ፥ እኔም እመልስልሃለሁ፤ አንተም የማታውቀውን ታላቅና ኃይለኛ ነገርን አሳይሃለሁ።
1 ቆሮንቶስ 2:9 ነገር ግን፦ “ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው፡” ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።
እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው በሰውም ልብ ያልታሰበውን ጭምር ነው።
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma
Wednesday, July 29, 2026
Sunday, May 17, 2026
የምንሞትለት እንጂ የምንገድልለት አምላክም ሆነ ሀይማኖት የለንም!
የምንሞትለት እንጂ የምንገድልለት አምላክም ሆነ ሀይማኖት የለንም!
አምላክ ሀያል ነው የእኛ እርዳታ አይፈልግም። እንዲገድሉለት የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት እውነተኛ ሀይማኖት አይደለም። የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት ሀሰተኛ ሀይማኖት ነው። የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት ከሰይጣን ነው።
ብዙ ሀይማኖቶች በምድር ላይ ቢኖሩም በአጠቃላይ ምድር ላይ ያሉት ሁለት አይነት ሀይማኖቶች ብቻ ናቸው። በምድር ላይ እውነተኛ እና ሀሰተኛ ሀይማኖት አለ። እግዚአብሔር አንድ ነው። ከአንድ በላይ እውነተኛ ሀይማኖት ሊኖር አይችልም። በአለም ላይ ከአንድ በላይ ሀሰተኛ ሀይማኖት ሊኖር ግን ይችላል።
ታዲያ ሀይማኖት መያዙ ሳይሆን እውነተኛውን አምላክ መያዛችንን እርግጠኛ እንሁን። እኔን በተመለከተ ፍለጋ አቁሜያለው እውነተኛውን አምላክ አግኝቻለሁ።
እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። ዮሐንስ 17:3 ሁሉም ሀይማኖት ወደ አንድ ፈጣሪ ያደርሳል የሚሉ በሰይጣን የተታለሉ ናቸው።
ኢየሱስም አለው፡— እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። ዮሐንስ 14:6
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
Sunday, April 12, 2026
ከእርሱ ጋር አስነሣን !
ከእርሱ
ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፣6 7
ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው ስለእኛ ነው። ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው እኛ በሃጢያታችን
ምክኒያት ቅዱስ ከሆነው ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላላም እንዳንለያይ ነው።
ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና። ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ
እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፣21 22
ክርስቶስ ኢየሱስ የሞተው እኛ በሃጢያታችን መሞት የነበረበንን ሞት ነው። ክርስቶስ
የሞተው በእኛ ምትክ ነው። ክርስቶስ የሞተው ለእኛ ነው።
በመጀመሪያ ሰው የተፈጠረው ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላላም እንዲኖር ነበር። በእግዚአብሔር
የተፈጠረው ሃጢያትን የማያውቅ ፍጹም ሰው ነበር።
ሰው ከእግዚአብሔር የተለየው ሃጢያት በሰራ ጊዜ ነበር።
እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤ ነገር
ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና። ዘፍጥረት 2፣16 17
ክርስቶስ የመጣው እኛ ወደፊት እንዳንሞት ከእግዚአብሔርም ጋር ለዘላላም እንዳንለያይ
ነው።
ክርስቶስ ሃጢያት ያልተገኘበት ፍጹም ነው። ክርስቶስ መሞት አይገባውም ነበር። ክርስቶስ የሞተው እኛ ሞት ሰለሚገባን ነበር። ክርስቶስ የሞተው እኛን
ከሞት ሊያስነሳን በእኛ ምትክ ነው።
ክርስቶስ የሞተው ለእኛ ትንሳኤን ሊሰጠን ነው።
እኛ ከክርስቶስ ጋር አብረነው ካልተነሳን ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።
የክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ "ከእለታት አንድ ቀን ክርስቶስ ከሞት ተነሳ"
ብለን ብቻ የምናስታውሰው የክርስቶስ ታሪክ አይደለም። የክርስቶስ ትንሳኤ የእኛም ከሙታን የመነሳት ልምምድ ነው። በክርስቶስ ሞትና
ተንሳኤ የምናምን ሁላችን ከሞት ተነስተናል።
ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር
ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥ በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት
ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፣5-7
የትንሳኤ በአል የክርስቶስ ብቻ ሳይሆን የእኛም የትንሳኤ በአል ነው።
መልካም የትንሳኤ በአል
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
Friday, November 28, 2025
የብልጽግና ወንጌል ምሥጢር ሲገለጥ
የብልጽግና ወንጌል ምሥጢር ሲገለጥ
በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና። ወደ ሮሜ ሰዎች 1፡16
ወንጌል በሃጢያታቸው ምክኒያት ለዘላለም ከእግዚአብሔር የተለያዩትን የሰው ልጆች ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም እንዲኖሩ የሚያስችል ታላቅ የምስራች ነው።
አሁን ግን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ ታይቶአል። እርሱ ሞትን ሽሮአልና እኔ ሰባኪና ሐዋርያ አሕዛብንም አስተማሪ እንድሆን በተሾምሁበት በወንጌል ሕይወትንና አለመጥፋትን ወደ ብርሃን አውጥቶአል። 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1:10-11
ወንጌል ጠላቶች የነበሩትን የሰው ልጆች በማስታረቅ የእግዚአብሔር ወንድና ሴት ልጆች አድርጎ መቀበል የሚያስችል ታላቅ የምስራች ነው።
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ የዮሃንስ ወንጌል 1:12
ወንጌል በሃጢያት ምክኒያት ከሰይጣን የባርነት እስራት ወስጥ ሲሰቃዩ የነበሩትን የሰው ልጆች በሰይጣን ላይ ስልጣን የሚሰጥ የእግዚአብሔር ታላቅ የማዳኛ ሃይል ነው፡፡
እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። ወደ ዕብራውያን 2:14
#የብልጽግናወንጌል #ወንጌል #ኢየሱስ #የምስራች #እግዚአብሔር #የበለጸገ #መልካምዜና
Tuesday, January 28, 2025
Name it claim it Take it!
Name it claim it Take it!
“So Jesus answered and said to them, “Have faith in God. For assuredly, I say to you, whoever says to this mountain, ‘Be removed and be cast into the sea,’ and does not doubt in his heart, but believes that those things he says will be done, he will have whatever he says.”
Mark 11:22-23 NKJV
Jesus taught that we can speak to our mountains and have them removed. Jesus encouraged us to believe in God for the removal of our mountain by the word of our mouth.
Whoever believes in God will identify his need, look for a solution from the word, call it to be changed, and have the situation changed.
We look for the word to see the will of God for our lives.
We have to believe God for it. Faith comes by hearing, and it comes by hearing the word of God.
“So then faith comes by hearing, and hearing by the word of God.”
Romans 10:17 NKJV
Faith comes as soon as we know the will of God for our lives.
Once we know the will, we don’t stop thinking it will go away by itself. We have actively claimed the desired result. Our confession must be aligned with our faith in our heart. We can't just believe and not confess thinking the work is done.
Once we confess what we believe from the word of God, we will have it.
It may take a while to manifest in the physical world, but in the spiritual, we have it already. We have to claim what we know the will of God for our lives is; we have to confess and call it into existence. And we will have it.
Name it claim it Take it!
Abiy Wakuma Dinsa




