የጻድቅ ሰው ጸሎት ብዙ ነገር የመስራት እና የመለወጥ አቅም አለው።
ያዕቆብ 5:16 … የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።
ነገር ግን የእግዚአብሔር ሀይል በፀሎታችን አይወሰንም። እግዚአብሔር ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ይችላል።
ኤፌሶን 3:20 እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው፥
የእግዚአብሔር ለሚፀልዩት ብቻ ሳይሆን በሁሉም ፍጥረቱ ላይ ያለው አላማ የፍቅር ነው።
መዝሙር 145:9 እግዚአብሔር ለሚታገሡት ቸር ነው። ምሕረቱም በሥራው ሁሉ ላይ ነው።
1 ጢሞቴዎስ 6:17 … ደስም እንዲለን ሁሉን አትርፎ በሚሰጠን በሕያው እግዚአብሔር እንጂ….
እግዚአብሔር የሚያስፈልገንን ከእኛ በላይ ስለሚያውቅ ለእኛም የሚያደርግልን በምንፀልየው ላይ ብቻ ተወስኖ ሳይሆን ከምንለምነው ሁሉ በላይ ነው።
ማቴዎስ 6:8 … ሳትለምኑት አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ያውቃልና።
እግዚአብሔር ከአፋችን ቃል በላይ የልባችንን ጩኸት ሰምቶ ይመልሳል። እግዚአብሔር አውቀን ከፀለይነው በላይ የማናውቀውን ታላቅና ኃይለኛ ነገርን ያሳየናል።
ኤርምያስ 33:3 ወደ እኔ ጩኽ፥ እኔም እመልስልሃለሁ፤ አንተም የማታውቀውን ታላቅና ኃይለኛ ነገርን አሳይሃለሁ።
1 ቆሮንቶስ 2:9 ነገር ግን፦ “ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው፡” ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።
እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው በሰውም ልብ ያልታሰበውን ጭምር ነው።
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma





