Popular Posts

Sunday, September 30, 2018

የሰርግ ጥሪ


የማቴዎስ ወንጌል 22:1-14
1 ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ፦
2 መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች።
3 የታደሙትንም ወደ ሰርጉ ይጠሩ ዘንድ ባሮቹን ላከ ሊመጡም አልወደዱም።
4 ደግሞ ሌሎችን ባሮች ልኮ፦ የታደሙትን፦ እነሆ፥ ድግሴን አዘጋጀሁ፥ ኮርማዎቼና የሰቡት ከብቶቼ ታርደዋል፥ ሁሉም ተዘጋጅቶአል፤ ወደ ሰርጉ በሉአቸው አለ።
5 እነርሱ ግን ቸል ብለው አንዱ ወደ እርሻው፥ ሌላውም ወደ ንግዱ ሄደ፤
6 የቀሩትም ባሮቹን ይዘው አንገላቱአቸው ገደሉአቸውም።
7 ንጉሡም ተቈጣ፥ ጭፍሮቹንም ልኮ እነዚያን ገዳዮች አጠፋ፤ ከተማቸውንም አቃጠለ።
8 በዚያን ጊዜ ባሮቹን፦ ሰርጉስ ተዘጋጅቶአል፥ ነገር ግን የታደሙት የማይገባቸው ሆኑ፤
9 እንግዲህ ወደ መንገድ መተላለፊያ ሄዳችሁ ያገኛችሁትን ሁሉ ወደ ሰርጉ ጥሩ አለ።
10 እነዚያም ባሮች ወደ መንገድ ወጥተው ያገኙትን ሁሉ ክፉዎችንም በጎዎችንም ሰበሰቡ፤ የሰርጉንም ቤት ተቀማጮች ሞሉት።
11 ንጉሡም የተቀመጡትን ለማየት በገባ ጊዜ በዚያ የሰርግ ልብስ ያለበሰ አንድ ሰው አየና፦ ወዳጄ ሆይ፥
12 የሰርግ ልብስ ሳትለብስ እንዴት ወደዚህ ገባህ? አለው እርሱም ዝም አለ።
13 በዚያን ጊዜ ንጉሡ አገልጋዮቹን፦ እጁንና እግሩን አስራችሁ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል አለ።
14 የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና።
አሁን ኢየሱስን ለመቀበል ከወሰንክ ይህንን ፀሎት ከልብህ ወደ እግዚአብሔር ፀልይ
እግዚአብሄር ሆይ የመዳንን እውቀት ስለላክልኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ ሃጢያተኛ እንደሆንኩ አውቃለሁ፡፡ በሃጢያቴ ካንተ እንደተለሁ አውቃለሁ፡፡ ኢየሱስ ስለሃጢያቴ በመስቀል ላይ በመሞት የሃጢያቴን ዋጋ ሁሉ እንደከፈለ አውቄያለሁ፡፡ ኢየሱስ በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ አምናለሁ፡፡ ኢየሱስ ጌታ ነው፡፡ ልጅህ አድርገህ ወደ ቤተሰብህ ስለተቀበልከኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ በኢየሱስ ስም፡፡ አሜን፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ልጅነት #ደህንነት #መልካምስራ #መልካምምግባር #ሞት #አላማመሳት #ሐጢያት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ቃል #ፍጥረት #ልጅነት #ስራ #እምነት #አምባሳደር #ብርሃን #ጨው #ልጅነት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ

ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። ወደ ሮሜ ሰዎች 109-10
ኢየሱስ እኛን ከሃጢያት ባርነት ለማዳን ነፍሱን ሰጥቷል፡፡ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በመሞት በእግዚአብሄርና በእኛ መካከል ያለውን ጠላትነት አስወግዷል፡፡
መዳን ታላቅ ዋጋ ቢከፈልበትም እኛ ግን ለመዳን ምንም ዋጋ መክፈል የለብንም፡፡ ማድረግ ያለብን አንድ ነገር ይህን የመዳን ስጦታ አምነን መቀበል ብቻ ነው፡፡
ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፡8-9
ማንም ሰው ላለመዳን በቂ ምክኒያት ሊኖረው እስከማይችል ድረስ  እግዚአብሄር መዳንን ቀላል አድርጎታል፡፡
ከእምነት የሆነ ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል፦ በልብህ፦ ማን ወደ ሰማይ ይወጣል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤ ወይም፦ በልብህ፦ ወደ ጥልቁ ማን ይወርዳል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡6-7
መዳን ሩቅ አይደለም፡፡ መዳን ለሚፈልግ ሰው መዳን እጅግ ቅርብ ነው፡፡
ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡8
ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡9-10
አሁን ኢየሱስን ለመቀበል ከወሰንክ ይህንን ፀሎት ከልብህ ወደ እግዚአብሔር ፀልይ
እግዚአብሄር ሆይ የመዳንን እውቀት ስለላክልኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ ሃጢያተኛ እንደሆንኩ አውቃለሁ፡፡ በሃጢያቴ ካንተ እንደተለሁ አውቃለሁ፡፡ ኢየሱስ ስለሃጢያቴ በመስቀል ላይ በመሞት የሃጢያቴን ዋጋ ሁሉ እንደከፈለ አውቄያለሁ፡፡ ኢየሱስ በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ አምናለሁ፡፡ ኢየሱስ ጌታ ነው፡፡ ልጅህ አድርገህ ወደ ቤተሰብህ ስለተቀበልከኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ በኢየሱስ ስም፡፡ አሜን፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ልጅነት #ደህንነት #መልካምስራ #መልካምምግባር #ሞት #አላማመሳት #ሐጢያት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ቃል #ፍጥረት #ልጅነት #ስራ #እምነት #አምባሳደር #ብርሃን #ጨው #ልጅነት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Thursday, September 27, 2018

የሚድነው ሁሉም ሰው ያልሆነው ለምንድነው ?


እግዘኢአብሄር ለሰው ልጆች መዳን የሚያስፈልገውን የሃጢያት እዳ ሁሉ በኢየሱስ በኩል እንዲከፈል ቢያደርግም እውነታው ግን ሁሉም ሰው አይድንም፡፡
ሁሉም ሰው ይድናል ብሎ እየተጠባበቀ ያለ ሰው ካለ ተሞኝቷል፡፡ ሁሉም ሰው አይድንም፡፡
የሚድነው እግዚአብሄር ያዘጋጀለትን የመዳኛ መንገድ ኢየሱስን የተቀበለ ሰው ብቻ ነው፡፡ ኢየሱስን ያልተቀበለ ሰው መዳን አይችልም፡፡
የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ የዮሐንስ ወንጌል 1፡12-13
ሰው ሁሉ ኢየሱስን ተቀብሎ መዳን ቢችልም ኢየሱሰን የማይቀበለ ሰው ግን አይድንም፡፡
በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም። የዮሐንስ ወንጌል 3፡36
ኢየሱስን ያልተቀበለ ሰው ሃጢያቱ ለዘላለም ከእግዚአብሄር ይለየዋል፡፡ ኢየሱስን ያልተቀበለ ሰው ለሃጢያቱ የተከፈለውን እዳ ለእኔ ነው ብሎ ስላለተቀበለ እስከ እዳው ይኖራል፡፡
ለእግዚአብሄር ፍቅር ምላሽ ያለሰጠ ሰው ከዚህ ወዲያ መስዋእት አይቀርለትም፡፡
ብዙ የመዳኛ መንገዶች የሉም፡፡ መንገዱ አንድ ነው፡፡
ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። የዮሐንስ ወንጌል 14፡6
በኢየሱስ ያልዳነ በማንም ሊድን አይችልም፡፡
መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና። የሐዋርያት ሥራ 412
አሁን ኢየሱስን ለመቀበል ከወሰንክ ይህንን ፀሎት ከልብህ ወደ እግዚአብሔር ፀልይ
እግዚአብሄር ሆይ የመዳንን እውቀት ስለላክልኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ ሃጢያተኛ እንደሆንኩ አውቃለሁ፡፡ በሃጢያቴ ካንተ እንደተለሁ አውቃለሁ፡፡ ኢየሱስ ስለሃጢያቴ በመስቀል ላይ በመሞት የሃጢያቴን ዋጋ ሁሉ እንደከፈለ አውቄያለሁ፡፡ ኢየሱስ በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ አምናለሁ፡፡ ኢየሱስ ጌታ ነው፡፡ ልጅህ አድርገህ ወደ ቤተሰብህ ስለተቀበልከኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ በኢየሱስ ስም፡፡ አሜን፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ልጅነት #ደህንነት #መልካምስራ #መልካምምግባር #ሞት #አላማመሳት #ሐጢያት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ቃል #ፍጥረት #ልጅነት #ስራ #እምነት #አምባሳደር #ብርሃን #ጨው #ልጅነት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

እድን ዘንድ ምን ማድረግ ይገባኛል?


ወደ ውጭም አውጥቶ፦ ጌቶች ሆይ፥ እድን ዘንድ ምን ማድረግ ይገባኛል? ኣላቸው። የሐዋርያት ሥራ 16:30
ይህ የብዙ ሰው የልብ ጨኸት ነው፡፡
ይህ በህይወት ዘመን ሊመለስ የሚገባው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡
ይህ የእውቀት ጥያቄ አይደለም፡፡ ይህ የጥበብ ጥያቄ አይደለም፡፡ የህ የህግይወትና የሞት ጥያቄ ነው፡፡
ይህን ጥያቄ በትክክል መመለሳችን ወይም አለመመለሳችን ለዘላለም ከእግዚአብሄር እንድንለይ ወይም ከእግዚአብሄር ጋር እንድንኖር ያስችለናል፡፡
ይህን ጥያቄ በትክክል መመለሳችን የተፈጠረንበትን አላማ እንድናገኝ እና የተፈጠርንበትን አላማ ባለመሳት ከንቱ እንዳንሆን ያደርገናል፡፡
ለመዳን መልሱ አጭርና ግልጭ ነው፡፡
እነርሱም፦ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አንተና ቤተ ሰዎችህ ትድናላችሁ አሉት። የሐዋርያት ሥራ 16:31
ምክኒያቱም ከክርስቶስ ውጭ መዳን በሌላ በማንም የለም፡፡
መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና። የሐዋርያት ሥራ 4፡12
አሁን ኢየሱስን ለመቀበል ከወሰንክ ይህንን ፀሎት ከልብህ ወደ እግዚአብሔር ፀልይ
እግዚአብሄር ሆይ የመዳንን እውቀት ስለላክልኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ ሃጢያተኛ እንደሆንኩ አውቃለሁ፡፡ በሃጢያቴ ካንተ እንደተለሁ አውቃለሁ፡፡ ኢየሱስ ስለሃጢያቴ በመስቀል ላይ በመሞት የሃጢያቴን ዋጋ ሁሉ እንደከፈለ አውቄያለሁ፡፡ ኢየሱስ በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ አምናለሁ፡፡ ኢየሱስ ጌታ ነው፡፡ ልጅህ አድርገህ ወደ ቤተሰብህ ስለተቀበልከኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ በኢየሱስ ስም፡፡ አሜን፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ልጅነት #ደህንነት #መልካምስራ #መልካምምግባር #ሞት #አላማመሳት #ሐጢያት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ቃል #ፍጥረት #ልጅነት #ስራ #እምነት #አምባሳደር #ብርሃን #ጨው #ልጅነት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Wednesday, September 26, 2018

የመታዘዝ ስልጣን


ሰው የተፈጠረው እንዲገዛ ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው እግዚአብሄርን ወክሎ ምድርን እንዲያስተዳደር ነው፡፡
ሰው በእግዚአብሄር መልክና አምሳል የተፈጠረው ከሙሉ ስልጣን ጋር ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በስልጣን ነው፡፡
ሰው እግዚአብሄርን መታዘዝ ሲያቆም ስልጣኑን አጣው፡፡ ሰው እግዚአብሄር ላይ ሲያምፅ ክብሩን አጣው፡፡ ሰው እግዚአብሄር ላይ ሲያምፅ ንግስናውን አጣው፡፡  ለእግዚአብሄር የማዘዝ ስልጣን እምቢ ሲል ሰው የራሱን ስልጣኑን አጣው፡፡ ሰው በአመፅ ስልጣኑን አሳልፎ ሰጠ፡፡
ሰው እግዚአብሄርን ሲታዝዝ የሚታዘዙለት ነገሮች ሁሉ በእግዚአብሄር ላይ ሲያምፅ አመፁበት፡፡ ሰው ሲያምፅ እግዚአብሄን ሲታዝዝ የነበረውን ስልጣን አጣው፡፡
እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው፦ ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥ ግዙአትም፤ የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ግዙአቸው። ኦሪት ዘፍጥረት 1፡27-28
መታዝዝ ያነግሳል፡፡ መታዘዝ ያከብራል፡፡ መታዘዝ ስልጣንን ይሰጣል፡፡
ማመፅ ስልጣንን ይሽራል፡፡ አለመታዘዝ ያዋርዳል፡፡ አለመታዘዝ ያስንቃል፡፡
ለእግዚአብሄር ስርአት መታዘዝ ክብር እንጂ ውርደት አይደለም፡፡ ለእግዚአብሄር ስልጣን መታዝዝ ሃይል እንጂ ድካም እይደለም፡፡ እግዚአብሄር ላስቀመጣቸው ባለስልጣናት መታዘዝ ድል እንጂ ሽንፈት አይደለም፡፡
ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ሥልጣኖች ይገዛ። ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለ ሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው። ስለዚህ ባለ ሥልጣንን የሚቃወም የእግዚአብሔርን ሥርዓት ይቃወማል፤ ወደ ሮሜ ሰዎች 13፡1-2
ሰው ስልጣኑን የሚያገኘው በትህትና ነው፡፡ ሰው ሃይሉን የሚያገኘው በመታዝዝ ነው፡፡
እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ የያዕቆብ መልእክት 4፡7
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መታዝዝ #ስልጣን #ትህትና #ክብር #ውርደት #አመፅ #ሃይል #ተገዙ #ተቃወሙት #አለመታዘዝ #ታማኝ #ትጉህ #መክሊት #ትውልድ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ሃሳብ #ገንዘብ #ጊዜ #ትግስት #መሪ

Monday, September 24, 2018

ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም

ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም። መጽሐፈ መክብብ 11፡4
የተለያዩ እድሎች በየጊዜው ይመጣሉ፡፡ በህይወታችን እድሎች መምጣታቸው አይቀርም፡፡ የሚመጣው እድል ተጠቃሚ የሚሆነው ሰው ግን እድሉ ሳይመጣ ለእድሉ የተዘጋጀ ሰው ብቻ ነው፡፡ ውጤት ማግኘት ከተፈለገ እድሉ ይመጣል ብሎ አምኖ አስቀድሞ መዘጋጀት መስራትና መትጋትን ይጠይቃል፡፡
እምነት የሚያስፈልገው ሳያዩ በፊት ነው፡፡ ለወደፊት መዘጋጀት ሳያዩ ነው፡፡ ለአዩት ነገር መዘጋጀት አይቻልም፡፡ የአሁትን ነገር ማስተናገድ እንጂ ለአዩት ነገር መዘጋጀት ከንቱ ነው፡፡ ካላየሁ አላምንም የሚል ሰው ሲያይ ቢያምን ዋጋ የለውም፡፡ እስከሚያይ የማያምን ሰው ሲያይ ቢያምን ረፍዶበታል፡፡
ነፋስን ሳይጠባባቅ የሚዘራ ሰው የተባረከ ነው፡፡ ደመናን ሳይመለከት የሚዘራ ሰው ሰው በጊዜው ያጭዳል፡፡
ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም። መጽሐፈ መክብብ 11፡4
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ነፋስ #የሚጠባበቅ #አይዘራም #ደመና #አያጭድም #የጌታፈቃድ #ይቀጣል #በብዙ #በጥቂት ##ታማኝ #ትጉህ #መክሊት #ትውልድ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ሃሳብ #ገንዘብ #ጊዜ #ትግስት #መሪ

Saturday, September 22, 2018

ጥቂት ቃልን የሚናገር አዋቂ ነው

ጥቂት ቃልን የሚናገር አዋቂ ነው፥ መንፈሱም ቀዝቃዛ የሆነ አስተዋይ ነው። ሰነፍ ዝም ቢል ጠቢብ ሆኖ ይቈጠራል፥ ከንፈሩንም የሚቈልፍ፦ ባለ አእምሮ ነው ይባላል። መጽሐፈ ምሳሌ 17፡27-28
ዐዋቂ ሰው ንግግሩ ቊጥብ ነው፤ አስተዋይም መንፈሱ የረጋ ነው። አላዋቂ እንኳ ዝም ቢል ጠቢብ፣ አንደበቱንም ቢገዛ አስተዋይ ይመስላል። መጽሐፈ ምሳሌ 17፡27-28 (መደበኛ ትርጉም)

በቃል ብዛት ውስጥ ኃጢአት ሳይኖር አይቀርም፤ ከንፈሩን የሚገታ ግን አስተዋይ ነው። መጽሐፈ ምሳሌ 10፡19

Friday, September 21, 2018

እግዚአብሄር የሚቀጣባቸው ሁለቱ መመዘኛዎች

እግዚአብሄር ሰውን ለክብሩ ፈጥሮታል፡፡ እግዚአብሄር ሰውን በመልኩና በአምሳሉ ፈጥሮታል፡፡ እግዚአብሄር ሰውን ይወዳል፡፡ እግዚአብሄር በሰው ላይ ይፈርዳል፡፡ እግዚአብሄር እውነተኛ ዳኛ ነው፡፡
እግዚአብሄር ሰውን ሲፈጠረው እንዲያደርግለት የሚፈልገውን ነገር ነግሮት ነበር፡፡ እግዚአብሄር የሚፈልገውን ነገር ሰው ካላደረገ እግዚአብሄር እንደሚቀጣው ነግሮት ነበር፡፡ እግዚአብሄር የሰዎችን አካሄድ በሚገባ በትጋት ይከታተላል ያስተካክላል፡፡
እግዚአብሄር ሁለት አይነት ሰዎችን ይቀጣል፡፡
የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ባሪያ እጅግ ይገረፋል፤ ያላወቀ ግን መገረፍ የሚገባውንም ያደረገ ጥቂት ይገረፋል። የሉቃስ ወንጌል 12፡47-48
የጌታውን ፈቃድ አውቆ ያላደረገ ሰው
ሰው የተፈጠረው እንዲታዘዝ ነው፡፡ እግዚአብሄር አመፀኛን ሰው ይቀጣል፡፡ እግዚአብሄር የማይታዘዝን ሰው ይቀጣል፡፡ አለመታዘዝ አመፅ ነው፡፡ የጌታን ፈቃድ ያወቀ ሰወ ፈቃዱን ማድረግ እንጂ ሌላ ምንም አማራጭ የለውም፡፡ የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ያ ባሪያ እጅግ ይገረፋል፡፡
የጌታውን ፈቃድ ማወቅ ሲገባው ያላወቀ
የጌታን ፈቃድ ያላወቀ ሰው ሊቀጣ ይችላል፡፡ የጌታን ፈቃድ ያላወቀ ሰው ሁሉ ግን አይቀጣም፡፡ የጌታን ፈቃድ ያላወቀ ሰው ላይቀጣ ይችላል፡፡ የጌታ ፈቃድን ያላወቀ ሰው መቀጣቱና አለመቀጣቱ የሚወሰነው በደረጃው ነው፡፡ ሰው ባልደረሰበት ደረጃ አይቀጣም፡፡ ነገር ግን ከጊዜው የተነሳ እዚያ ደረጃ ላይ ባለመድረሱ በዚያ ይቀጣል፡፡ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ያላወቀ ግን መገረፍ የሚገባውንም ያደረገ ጥቂት ይገረፋል፡፡
ከጊዜው የተነሳ አስተማሪዎች ልትሆኑ ሲገባችሁ፥ አንድ ሰው ስለ እግዚአብሔር ቃላት መጀመሪያ ያለውን የሕፃንነትን ትምህርት እንዲያስተምራችሁ እንደ ገና ያስፈልጋችኋልና፤ የሚያስፈልጋችሁም ወተት ነው እንጂ ጠንካራ ምግብ አይደለም። ወደ ዕብራውያን 5፡12
አንድ ሰው ማድረግ ሲገባው  በህይወቱ የሚያሳድጉትን ነገሮች ባለማድረጉ በስንፍናው ይቀጣል፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የጌታፈቃድ #ይቀጣል #በብዙ #በጥቂት ##ታማኝ #ትጉህ #መክሊት #ትውልድ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ሃሳብ #ገንዘብ #ጊዜ #ትግስት #መሪ

Monday, September 17, 2018

አጥብቀህ


አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፥ የሕይወት መውጫ ከእርሱ ነውና። መጽሐፈ ምሳሌ 4፡23
ህይወት የሚወጣው ከልብ ነው፡፡ የሰው አካሄድ የሚወጣው ከልቡ ነው፡፡ የሰው አካሄድ የሚጀምረው በልቡ ነው፡፡ ሰው የሚኖረው የልቡን ሃሳብ ነው፡፡ ሰው የሚመስለው ልቡን ነው፡፡
እርሱም አለ፦ ከሰው የሚወጣው ሰውን የሚያረክስ ነው። ከውስጥ ከሰው ልብ የሚወጣ ክፉ አሳብ፥ ዝሙት፥ መስረቅ፥ መግደል፥ ምንዝርነት፥ መጐምጀት፥ ክፋት፥ ተንኰል፥ መዳራት፥ ምቀኝነት፥ ስድብ፥ ትዕቢት፥ ስንፍና ናቸውና፤ ይህ ክፉው ሁሉ ከውስጥ ይወጣል ሰውን ያረክሰዋል። የማርቆስ ወንጌል 7፡19-23
ልብህ ከወደቀ ትወድቃለህ
ዳዊትም በአጠገቡ ለቆሙት ሰዎች፦ ይህን ፍልስጥኤማዊ ለሚገድል፥ ከእስራኤልም ተግዳሮትን ለሚያርቅ ሰው ምን ይደረግለታል? የሕያውን አምላክ ጭፍሮች የሚገዳደር ይህ ያልተገረዘ ፍልስጥኤማዊ ማን ነው? ብሎ ተናገራቸው። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 17፡26
ልብህ ከቆሸሸ ትቆሽሻለህ
ልብሳችንና ቤታችን እንዳይቆሽሽ በንፅህና እንደምንጠብቀው ሁሉ ልባችንን መጠበቅ አለብን፡፡ ቤታችንና ልብሳችን ሲቆሽሽ እንደሚያሳፍረን ሁሉ ከልብስና ከቤት መቆሸሸ በላይ ህይወታችንን ሊገድልና ሊያድን የሚችለውን የልባችንን መቆሸሽ ሊያሳፍረን ይገባል፡፡ ለሰው የሚታየው የቤታችንና የልብሳችን መቆሸሽ ከሚያሳፍረን በላይ ውሎ አድሮ በተግባር የሚታይው የልባችን መቆሸሽ ሊያሳፍርን ይገባል፡፡ ቤታችንንና ልብሳችንን ለማፅዳት ጊዜያችንን ገንዘባችንን ጉልበታችንን ከምናፈሰው በላይ የህይወት መውጫ የሆነውን ልባችንን ለማንፃት ሁለንተናችንን መስጠይት ይገባናል፡፡    
አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ። መዝሙረ ዳዊት 51፡10
ልቡን የሚመረምርና ልቡን ለማጥራት የሚተጋ ሰው ከክፋት ያርፋል በህይወቱንም ፍሬያማ ይሆናል፡፡
ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ። ያዕቆብ 4፡8
የሰው ሃሳብ ሰውን እንሚያረክሰው የሚበላው ምግብ ሰውን አያረክሰውም፡፡ ለምንበላው ምግብ ከምንጠነቀው በላይ ለልባችን ንፁህነት መጠንቀቅ ህይወታችንን ያድነዋል፡፡
ልብህ ከበረታ ትበረታለህ
ሰው የሚበረታውምን የሚደክመውም በልቡ ነው፡፡ ሰው በልቡ ከበረታ ይብረታል፡፡ ሰው በልቡ ከደከመ ይደክማል፡፡
ሰው ህይወቱን የሚያስተካክለው በልቡ ነው፡፡ ሰው ልቡን ሳይጠብቅ ህይወቱን መጠበቅ አይችልም፡፡ ሰወ ልቡን ከተጠበቀ ህይወቱ የማይጠበቅበት ምንም ምክኒያት የለም፡፡
በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና፤ ብላ ጠጣ ይልሃል፥ ልቡ ግን ካንተ ጋር አይደለም። መጽሐፈ ምሳሌ 23፡7
በነጋውም የጠጁ ስካር ከናባል ባለፈ ጊዜ ሚስቱ ይህን ነገር ነገረችው፤ ልቡም በውስጡ ሞተ፥ እንደ ድንጋይም ሆነ፤ መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 25፡37
ልቡን በእግዚአብሄር ቃል ለመቃኘት ራሱን የሰጠ ሰው ህይወቱ ይቃኛል፡፡   
የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ወደ ሮሜ ሰዎች 12፡2
ልቡን ለመጠበቅ ቸልተኛ የሆነ ሰው ለህይወቱ ግድ የሌለው ሰው ብቻ ነው፡፡ ህይወቱን መጠበቅ የሚፈልግ ሰው አጥብቆ ልቡን መጠበቅ አለበት፡፡
አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፥ የሕይወት መውጫ ከእርሱ ነውና። መጽሐፈ ምሳሌ 4፡23
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ሃሳብ #መነሻሃሳብ #ልብ #ንፁህ #ማየት #ምኞት #ንፁህ #አጥሩ #ልብ #አለማየት #ቃል #የእምነትተጋድሎ #የእግዚአብሄርቃል #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ