Popular Posts

Friday, June 28, 2019

ወንድሙንም ደንቆሮ የሚለውም ሁሉ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይገባዋል



እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል፤ ወንድሙንም ጨርቃም የሚለው ሁሉ የሸንጎ ፍርድ ይገባዋል፤ ደንቆሮ የሚለውም ሁሉ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይገባዋል። የማቴዎስ ወንጌል 5፡22
እግዚአብሄር አንድ ላይ እንድንኖር ማህበራዊ ፍጥረቶች አድርጎ ፈጥሮናል፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ያለው ፍላጎት የሚያሟላው አጠገባችን ባለው ሰው ስጦታ ተጠቅሞ ነው፡፡ በምድር ላይ ያለነው በስጦታችን የሌላውን ሰው ፍላጎት ለማሟላት ነው፡፡
እግዚአብሄር ሲፈጥረን የተለያን አድርጎ ፈጥሮናል፡፡ ሁላችንም የተለያየ አስተሳሰብ ፣ አመለካከት ፣ ስጦታ ፣ ዝንባሌና  ፍላጎት ያለን ሰዎች ነን፡፡  ስላለን ትክክል ነው ብለን ስለምናምነው አስተሳሰብ ፣ አመለካከት ፣ ስጦታ ፣ ዝንባሌና  ፍላጎት ንስሃ እንደማንገባ ሁሉ ሌላውም ሰው ማንንም ይቅርታ ባይጠይቅ መገረም የለብንም፡፡ እኔ እስከ ልዩነቴ ሰዎች እንዲቀበሉኝ ወይም እንዲታገሱኝ እንደምፈልገው ሁሉ ሌላውም ሰው እንድንታገሰው ይፈልጋል፡፡
ሰዎችም ሊያደርጉላችሁ እንደምትወዱ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው። የሉቃስ ወንጌል 6፡31
በምድር ላይ ስኬታማ ለመሆን ልዩነታችንን መገንዘብ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ እንዲያውም በምድር ላይ ፍሬያማ ለመሆን ልዩነታችንን ተረድቶ እንደ ልዩነታችን መኖር ግዴታ ነው፡፡ እግዚአብሄር እንኳን ያላደረገውን ሁሉንም ሰው አንድ አይነት ለማድረግ በሞከር ህይወትን ከማባከን የሰውን ልዩነት ለመቀበል ልብን ማስፋት ጥቅም አለው፡፡ የሰዎችን ልዩነት የማይረዳ ሰው በህይወቱ ስኬትንና ፍሬያማነትን ሳያይ ያልፋል፡፡
ከእኛ የተለዩ ብዙ ሰዎች ባሉበት ምድር ውስጥ መኖር ትህትናን ይጠይቃል፡፡ በፍፁም የማንረዳቸው ሰዎች ባሉበት ምድር ውስጥ ለመኖር ራስን ማዋረድ ይጠይቃል፡፡ በፍፁም የማይረዱን ሰዎች ባሉበት ምድር ውስጥ በሰላም መኖር መረዳትን ይጠይቃል፡፡ በፍጩም የማንረዳቸው ሰዎች ባሉነት መድር ወስጥ መኖር ራሰን መግዛት ይጠይቃል፡፡
ማናችንም ራሳችንን አልፈጠረንም፡፡ ሁላችንም እግዚአብሄር ለራሱ የፈጠረን የእግዚአብሄር ባሪያዎች ነን፡፡ የፈጠራቸው እግዚአብሄር አለ እንጂ ማናችንም ሌላውን ሰው አልፈጠርንም፡፡ ሰውም በመጨረሻ ተጠሪነቱ ለፈጠረው ለእግዚአብሄር እንጂ ለእርስ በእርሳችን አይደለም፡፡  
እኛ የእግዚአብሄር ፍጥረት እንደሆንን ሁሉ ወደድንም ጠላንም የማይመቸን ሰው የእግዚአብሄር ፍጥረት ነው፡፡ እኛን እግዚአብሄር እንደሚወደን ሁሉ ወደድንም ጠላንም በፍጹም የማይረዳንን ሰው ወዶታል፡፡ የእኛ ድርሻ እግዚአብሄር ከፈጠራቸው ሰዎች ጋር በትህትና መኖር ነው፡፡ ከእግዚአብሄር ጋረ በትህትና መሄዳችን የሚታየው ከፈጠራቸው ጋር በትህትና በመኖር ነው፡፡  
ሰው ሆይ፥ መልካሙን ነግሮሃል፤ እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ፥ ምሕረትንም ትወድድ ዘንድ፥ ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሄድ ዘንድ አይደለምን? ትንቢተ ሚክያስ 6፡8
ሌላውን መጣል የራስን አንድ የሰውነት ክፍል እንደመጣል ይቆጠራል፡፡ ሌላውን መጣል አንዱን በረከታችንን እንደመጣል ይቆጠራል፡፡ ሌላው ላይ መፍረድ ትእቢት ነው፡፡ ሌላው ላይ መፍረድ የእግዚአብሄርን ቦታ መውሰድ ነው፡፡ ሌላው ላይ መፍረድ ከእግዚአብሄር በላይ አውቃለሁ ማለት ነው፡፡ ሌላው ላይ መፍረድ አለም የምትተዳረው እንደ እግዚአብሄር ሳይሆን እንደ እኔ ህግ ነው ማለት ነው፡፡ ሌላው ላይ መፍረድ ማለት አለም ሰው መተዳደር ያለበት እንደእኔ መረዳት እንጂ እንደ እግዚአብሄር መረዳት አይደለም ማለት ነው፡፡  
በመፅሃፍ ቅዱስ ሌላውን መጣል እንደሚያስፈርድ የሚያስተምረው ስለዚህ ነው፡፡  
እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል፤ ወንድሙንም ጨርቃም የሚለው ሁሉ የሸንጎ ፍርድ ይገባዋል፤ ደንቆሮ የሚለውም ሁሉ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይገባዋል። የማቴዎስ ወንጌል 5፡22
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ህይወት #የሚፈርድ #የሚያማ #ወንጌል #መውደድ #ፍቅር #ደንቆሮ #የሚቆጣ #ፍርድ #ጨርቃም #ትህትና #መታዘዝ #ማገልገል #መውደድ #እውነት #ትህትና #ትንሳኤ #ህይወት #ወንጌል #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ  #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ 

Sunday, June 23, 2019

ቸሩ እግዚአብሔር



እግዚአብሄር አይለወጥም የእግዚአብሄር መልካምነት አይለወጥም
እግዚአብሄር ሁሌ መልካም ነው፡፡ የእግዚአብሄር መልካምነት ባህሪው ነው፡፡ እግዚአብሄርን ብታገላብጡት መልካም እንጂ ክፉ ሊሆን አይችልም፡፡
የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ አትሳቱ። በጎ ስጦታ ሁሉ ፍጹምም በረከት ሁሉ ከላይ ናቸው፥ መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ በመዞርም የተደረገ ጥላ በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ።  የያዕቆብ መልእክት 1፡16-17
እግዚአብሄር ከምድር አባት ሁሉ የሚበልጥ ልዩ አባት ነው
አብልጦ መልካም ነገርን ይሰጣል፡፡
ይህ ከምድር ኣበቶች ሁሉ በአባትነቱ መልካምነት የሚበልጠው እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ አዳኝነት ላመንን ሁላችን አባታችን ሆኖዋል፡፡  
ወይስ ከእናንተ፥ ልጁ እንጀራ ቢለምነው፥ ድንጋይን የሚሰጠው ከእናንተ ማን ሰው ነው? ዓሣስ ቢለምነው እባብን ይሰጠዋልን? እንኪያስ እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን ካወቃችሁ፥ በሰማያት ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን ይሰጣቸው? የማቴዎስ ወንጌል 7፡9-11
እግዚአብሄር የመልካምነት ማጣቀሻ ነው፡፡
ስለአንድ መልካምነት ክርክር ከተነሳ ውሳኔውን የሚሰጥ እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡ መልካም የሚባለው እግዚአብሄር መልካም ካለው ነው፡፡ ክፉ የሚባለው እግዚአብሄር  በቃሉ ክፉ ካለው ብቻ ነው፡፡ የመልካምነት ደረጃ መዳቢ እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡  
የእግዚአብሄር መልካምነት በወሳኝ ጊዜ ይታያል
ብዙ መልካም ሊያደርጉልን የሚፈልጉ በመካከላችን አሉ፡፡ ነገር ግን ሁሉም በማይችሉበት ጊዜ ምላምን ከሊያደርግልን የሚችል እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል። ትንቢተ ናሆም 1፡7
የትኛውም መልካምነት የሚመነጨው ከእግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
እናንትም ምንም መልካም ማድረግ ብትፈልጉ እግዚአብሄር ካልተጠቀመባችሁ ለማንም አትጠቅሙም፡፡
እግዚአብሔርን፦ አንተ ጌታዬ ነህ አልሁ፤ ከአንተ በቀር በጎነት የለኝም። መዝሙረ ዳዊት 16፡2
ሰው ምንም ቢያዝናችሁ ሃዘናችሁን ይካፈላል እንጂ እግዚአብሄር ካልተጠቀመበት ምንም መልካምነት ሊያደርግላችሁ አይችልም፡፡  
ኢየሱስም፦ ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም። የሉቃስ ወንጌል 18፡19
እግዚአብሄር ለእኛ የሚያስብ ፍፁም አሳብ ያለው መልካም አባት ነው፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ትንቢተ ኤርምያስ 29፡11
ስለዚህ እግዚአብሄርን ማመስገን መልካም ነው፡፡ እግዚአብሄርን ባለማመስገን እንጂ እግዚአብሄርን አመስግኖ የሚሳሳት ሰው የለም፡፡ እግዚአብሄር መልካም ነው፡፡
ሃሌ ሉያ። ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ መዝሙረ ዳዊት 107፡1
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #አመስግኑ #መልካም #እምነት #ቃልኪዳን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ቸር #መንፈስ #መንፈስቅዱስ

Friday, June 21, 2019

እግዚአብሄር ያሳፍራል



ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁን ተመልከቱ፤ እንደ ሰው ጥበብ ጥበበኞች የሆኑ ብዙዎች፥ ኀያላን የሆኑ ብዙዎች፥ ባላባቶች የሆኑ ብዙዎች አልተጠሩም። ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን እንዲያሳፍር የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ፤ ብርቱንም ነገር እንዲያሳፍር እግዚአብሔር የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ፤ እግዚአብሔርም የሆነውን ነገር እንዲያጠፋ የዓለምን ምናምንቴ ነገር የተናቀውንም ነገር ያልሆነውንም ነገር መረጠ፥ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት እንዳይመካ። ነገር ግን፡የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ፡ ተብሎ እንደ ተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው። 1 ቆሮንቶስ 1:26-31
v  ጥበበኞችን እንዲያሳፍር የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ፤
እግዚአብሔር ጥበበኛን ቢመርጥ የሚረዳው ፈልጎ ነው ይባላል:: እግዚአብሔር እኛን ይረዳል እንጂ በማናችንም አይረዳም :: እግዚአብሔር ክብሩን ለማንም ስለማይሰጥ ሞኝን ነገር መረጠ:: እግዚአብሔር ሞኝን ጠቢብ ቢያደርግ ይህ የእግዚአብሔር ጣት ነው ይባላል::
ጴጥሮስና ዮሐንስም በግልጥ እንደ ተናገሩ ባዩ ጊዜ፥ መጽሐፍን የማያውቁና ያልተማሩ ሰዎች እንደ ሆኑ አስተውለው አደነቁ፥ ከኢየሱስም ጋር እንደ ነበሩ አወቁአቸው፤ የሐዋርያት ሥራ 4:13
v  ብርቱንም ነገር እንዲያሳፍር እግዚአብሔር የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ፤
እግዚአብሄር ከሰው ጋር አይወዳደርም:: እግዝአብሄር እኛን የሚያዋርደው ያንሰኛል እበልጠዋለሁ በምንለው ሰው ነው:: እግዚአብሔር ደካማውን ያበረታና የምንመካበት የእኛ ብርታት ምንም እንዳይደለ ያሳየናል::
እርሱም፡ጸጋዬ ይበቃሃል፥ ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና፡ አለኝ። እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ። . . . ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና። 2 ቆሮንቶስ 12:9-10
v  እግዚአብሔርም የሆነውን ነገር እንዲያጠፋ የዓለምን ምናምንቴ ነገር የተናቀውንም ነገር ያልሆነውንም ነገር መረጠ፥
እግዚአብሔር ይህ የትም አይደርስም የተባለውን አስነስቶ እርሱ ብቻ ክብሩን መውሰድ ይፈልጋል::
ከሕዝቡ መኳንንት ጋር ያስቀምጣቸው ዘንድ፥ የክብርንም ዙፋን ያወርሳቸው ዘንድ፥ ችግረኛውን ከመሬት ያስነሣል፥ ምስኪኑንም ከጉድፍ ያስነሣል፤ የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና፥ በእነርሱ ላይም ዓለምን አደረገ። 1 ሳሙኤል 2:8
እግዚአብሄር በተናቀው ተጠቅሞ የናቀውን ትእቢተኛውን ያስቀናል::
ነገር ግን፡እስራኤል ባያውቁ ነው ወይ? እላለሁ። ሙሴ አስቀድሞ፡እኔ ሕዝብ በማይሆነው አስቀናችኋለሁ በማያስተውልም ሕዝብ አስቆጣችኋለሁ፥ ብሎአል። ወደ ሮሜ 10:19
ሰው በእግዚአብሔር ፊት የሚያስመካው አንዳች ነገር የለም:: ምንም እንድንበልጥ ያደረገን ነገር ቢኖረን ከእርሱ የተቀበልነው ብቻ ነው፡፡
አንተ እንድትበልጥ ማን አድርጎሃል? ያልተቀበልኸውስ ምን አለህ? የተቀበልህ ከሆንህ ግን እንዳልተቀበልህ የምትመካ ስለ ምንድር ነው? 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 4፡7
ሰው መመካት የሚችለውና የሚገባው እስትንፋሳችንን በእጁ በያዘው በጌታ ብቻ ነው::
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ትህትና #መዋረድ #ባህሪ #ዝቅታ #ትዕቢት #ትምክህት #መመካት #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

''ተጠማሁ'' Solomon Yirga New Gospel 2019



ተጠማው

እልውናህን
መገኘትህን
ጌታ
ድምጽህን መዓዛ ግርማህን

አልፈልግም
ኖረ ኖረ ኖረ ሞተ
አልፈልግም
መሆን በምድር የታመነ
መንፈስክን
ይዞ ይዞ ሚገሰግስ
ለተጠማው
ደርሶ የልብህን የሚያደርስ
ንፋስክህን
በላዬ በላዬ አንፍስ
የሞተውን
ደርሶ ተነስ ተነስ ብሎ ሚቀሰቅስ

ውረድ
በላዬ ላይ መንፈስ ቅዱስ ልክ እንደ ዝናብ
አትምቀኝ
በመንፈስ እንደገና እውስጥ አስገባኝ
መለኪያ
የሌለው ያንተ ማንነትህ
ውዴ
ይምጣ በኔ እይወቴ
ጌታ
ሆይ ድንቅህ ታምራትህ

እያየሁ
እየሰማሁ እየያዝኩህ
እየዳሰስኩ
እንዳመልክህ እፈልጋልሁ
መንፈስ
ቅዱስ ተጠምቻልሁ

እሱ
አባት ነው እሱ አይጥልም
እሱ
ያደርሳል እሱ ይረዳል
እሱ
ይሰማል እሱ ይመልሳል
እሱ
ልዩ ነው ከሁሉም ይበልጣል
ተጠማው
ተጠማው ተጠምቻለው

Wednesday, June 19, 2019

ሰውን ወይስ እግዚአብሔርን አሁን እሺ አሰኛለሁን?



ሰውን ወይስ እግዚአብሔርን አሁን እሺ አሰኛለሁን? ወይም ሰውን ደስ ላሰኝ እፈልጋለሁን? አሁን ሰውን ደስ ባሰኝ የክርስቶስ ባሪያ ባልሆንሁም። ወደ ገላትያ 1:10
ብዙ የሰውና የእግዚአብሔር ፍላጎት ጊዜ ይለያያሉ::
እርሱ ግን ዘወር ብሎ ጴጥሮስን፦ ወደ ኋላዬ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን፤ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ዕንቅፋት ሆነህብኛል አለው። የማቴዎስ ወንጌል 16፡23
በሰው ወርቅ የሆነው ሃሳብ በእግዚአብሄር ግን የተሳሳተ ሃሳብ ሊሆን ይችላል፡፡
ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔር ፍላጎት ጥቁርና ነጭን ቀለም እንደ መለየት ቀላል ይመስለናል:: አንዳንድ ጊዜ በእግዚአብሄር አሰራር የምናዝነው ወይም የምንሰናከለው እንደጠበቅነው ስለማይሆ ነው፡፡ እግዚአብሔር መልካምን ነገር እንዳገኝ ይፈልጋል እንላለን ነገር ግን  ከማን አንፃር መልካም የሆነውን እግዚአብሄር እንደሚፈልግ አንርዳውም::
ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔር ፍላጎት ምንድነው ብለን ከመጠየቅና ከመፈለግ ይልቅ እግዚአብሔር ይህ እንዲሆንልኝ ሳይፈልግ አይቀርም ብለን በግምት በስንፍና እግዚአብሔርን በራሳችን ትንሽ አእሮምሮ ልንወስነው እንፈልጋለን::
ክርስትና የሚጀምረው የአንተ እና የእኔ ሀሳብ የተለያየ ነው ብሎ ከማመን ነው:: ክርስትና ፍሬያማ የሚሆነው በትህትናና በየዋህነት የራሳችንን ሀሳብ እየጣልን የእርሱን ሃሳብ በተቀበልን መጠን ብቻ ነው:: ክርስትና የሚደመደመው ብእርሱ ሀስብ እርሱን ስንመስለው ነው:: ክርስትና የሚጣፍጠው አእምሮዋችንን በእግዚአብሄር ቃል አና በእግዚአብሄር ሀሳብ ካደስን ብቻ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ወደ ሮሜ ሰዎች 12፡2
የእግዚአብሄርን ሃሳብ ለመቀበልና ለመተግበር የራሳችንንና የሌላውን ሰው ሀሳብ መተው ይጠይቃል::
ከምንስበው በላይ ብዙ ጊዜ የሰው ሃሳብና የእግዚአብሔር ሃሳብ በፊታችን እንደምርጫ ይቀርብልናል:: ክርስቶስን በመከተል ፍሬያማ ለመሆን ለእግዚአብሄር ቃል አዎ ለሰው ሃሳብ ደግሞ አይ ማለትን መማር አለብን፡፡
ከምናስበው በላይ ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔርና የሰው ህሳብ ይራራቃሉ:: የሰውንና የእግዚአብሄርን ሀሳብ አንድ ላይ ማስኬድ ደግሞ በፍፁም አይቻልም::
ክፉ ሰው መንገዱን በደለኛም አሳቡን ይተው፤ ወደ እግዚአብሔርም ይመለስ እርሱም ይምረዋል፥ ይቅርታውም ብዙ ነውና ወደ አምላካችን ይመለስ። አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው። ትንቢተ ኢሳይያስ 55፡7-9
ብዙ ጊዜ ሰውን ደስ ማሰኘት የእግዚአብሔርን ሃሳብ መጣል ይጠይቃል:: ብዙ ጊዜ እግዚአብሄርን ደስ ለማሰኘት የሰውን ሃሳብ መተው  ይጠይቃል::
ሰው ሊከበር ይገባዋል፡፡ ሰው ግን እንደ እግዚአብሄር ሊፈራ አይገባውም፡፡ ሰውን መፍራት ወጥመድ ያመጣል፡፡
ሰውን መፍራት ወጥመድ ያመጣል፤ በእግዚአብሔር የሚታመን ግን እርሱ ይጠበቃል። መጽሐፈ ምሳሌ 2925
አንዳንደ ጊዜ የእግዚአብሄርን ሃሳብ መርጠን የሰውን ቅያሜ ለመቀበል መዘጋጀት አለብን፡፡ የሰውን አስተያየት ሳንፈራ የእግዚአብሄርን ሃሳብ ለማድረግ ግንባራችንን የቡላድ ድንጋይ ማድረግ አለብን፡፡
ከቡላድ ድንጋይ ይልቅ እንዳለ አልማዝ ግምባርህን አጠንክሬአለሁ፤ እነርሱ ዓመፀኛ ቤት ቢሆኑ አትፍራቸው፤ ከፊታቸውም የተነሣ አትደንግጥ። ትንቢተ ሕዝቅኤል 39
የእግዚአብሄርን ሃሳብ ለማድረግ ሰዎች ነውር ነው የሚሉትን ነገር እንኳን ለማድረግ መዘጋጀት አለብን፡፡ እንደ ኢየሱስ እንደ ወንበዴ ተይዞ መሰቀል በብዙዎች ሰዎች ዘንድ ነውር ነው፡፡ ብዙዎች እንደወንበዴ ተይዘው ከሚሰቀሉ በእግዚአብሄር ሃሳብ ላይ ቢያመቻምቹ ይሻላቸዋል፡፡ ምሳሌያችን ኢየሱስ ግን ነውርን ናቀው እንጂ ከእግዚአብሄር ፈቃድ በላይ ነውርን አላከበረውም፡፡
እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና። ወደ ዕብራውያን 12፡2
የብዛት ጉዳይ አይደለም፡፡ ከእግዚአብሄር ፈቃድ ጋር አብሮ የሚቆም አንድ ሰው አብላጫ ነው፡፡  
ይህ ሕዝብ፦ ዱለት ነው በሚሉት ሁሉ፦ ዱለት ነው አትበሉ፤ መፈራታቸውንም አትፍሩ፥ አትደንግጡ። ትንቢተ ኢሳይያስ 8፡12
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ጌታ #ኢየሱስ #ፍቅር #ፍርሃት #ሃይል #ራስንመግዛት #አላማ #መዳን #ነፃነት #ቅድስና #ሰላም #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ብርሃን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  #የዋህነት #ንፁህ

Sunday, June 16, 2019

ስምንቱ የአባቶች ቀን ውሳኔዎች


1.      ልጆቼን ልመክርና ልገስፅ ግን ላላቆጣ እወስናለሁ
እናንተም አባቶች ሆይ፥ ልጆቻችሁን በጌታ ምክርና በተግሣጽ አሳድጉአቸው እንጂ አታስቆጡአቸው። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡4
2.     ለልጆቼ በእግዚአብሄር ቃል ምሳሌ ለመሆን እወስናለሁ
ባገኘሁት ጊዜ ሁሉ የስጋ ልጆቼ ላልሆኑት የአባትነትን ምክርና እንክብካቤ እሰጣለሁ፡፡
3.     ልጆቼን የእግዚአብሄርን መንገድ ለማሳየት ለማስተማር እወስናለሁ፡፡
ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም። መጽሐፈ ምሳሌ 22፡6
4.     ለቤተሰቤ የሚያስፈልገውን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳልል በመትጋት ለማቅረብ  እወስናለሁ፡፡
ነገር ግን ለእርሱ ስለ ሆኑት ይልቁንም ስለ ቤተ ሰዎቹ የማያስብ ማንም ቢሆን፥ ሃይማኖትን የካደ ከማያምንም ሰው ይልቅ የሚከፋ ነው። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 5፡8
5.     አባት ለሌለው ለድሃ አደጉ የመፍረድና የመከራከር መልካም ስራ በትጋት ለመስራት እወስናለሁ፡፡
መልካም መሥራትን ተማሩ፥ ፍርድን ፈልጉ፥ የተገፋውን አድኑ፥ ለድሀ አደጉ ፍረዱለት ስለ መበለቲቱም ተምዋገቱ። ትንቢተ ኢሳይያስ 1፡17
6.     የቤተሰቡን ችግር ከፊት ሆኜ ልጋፈጥ ችግሩ ወደ ቤተሰቤ እንዳይመጣ ቤተሰቤን ልከላከልና ጥላ ልሆናቸው እውስናለሁ፡፡
አባት ለልጆቹ እንደሚራራ እንዲሁ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ይራራል፤ መዝሙረ ዳዊት 103፡13
7.     በማንኛውም ሁኔታ ቤተሰቤን ላፅናና እና ላበረታታ እወስናለሁ፡፡
የርኅራኄ አባት የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፡3
8.     በስጋ ልጄ ላልሆነ በተለይ ይህ የአባትነት እድል ለማያገኘው በየትም ስፍራ ለማገኘው ልጅ በቻልኩት መጠን ሁሉ የአባትነት ተምሳሌ ልሆነው በህይወቱ ላይ አንድ የማበረታቻ ቃል አንኳን ቢሆን የአባትነትን አስተዋፅኦ ለማድረግ እወስናለሁ፡፡   
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
መልካም የአባቶች ቀን!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ወላጅ #ፍቅር #አባት #እርማት #ጥንካሬ #ራእይ #ደረጃመስጠት #ጥላ #ማበረታታት #አባትነት #ተግሳፅ  #መሪ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ