Popular Posts

Friday, March 29, 2019

ሆድ አምላኩ


እንዲህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና፥ በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ። ወደ ሮሜ ሰዎች 1618

መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው። ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 319 

Thursday, March 28, 2019

ትንፋሽህንና መንገድህን ሁሉ በእጁ የያዘውን አምላክ


የፈጠረን እግዚአብሄር ነው፡፡ ህይወትንና ትንፋሽን የሰጠን እግዚአብሄር ነው፡፡
አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፥ ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ። መጽሐፈ መክብብ 12፡7
የእያንዳንዳችንን ትንፋሽ የያዘው እግዚአብሄር ነው፡፡
ምድርን አደራ የሰጠው ማን ነው? ዓለምንስ ሁሉ በእርሱ ላይ ያኖረ ማን ነው? እርሱ ልቡን ወደ ራሱ ቢመልስ፥ መንፈሱንና እስትንፋሱን ወደ ራሱ ቢሰበስብ፥ ሥጋ ለባሽ ሁሉ በአንድነት ይጠፋል፥ ሰውም ወደ አፈር ይመለሳል።  መጽሐፈ ኢዮብ 34፡13-15
በመፅሃፍ ቅዱስ በትንቢተ ዳንኤል ምእራፍ 5 ከቁጥር 18 እስከ 23 የምንመለከተው ታሪክ የንጉስ አባት የናቡከደነፆር የልጁ የብልጣሶር ታሪክን ነው፡፡
ልጁ ብልጣሶር እግዚአብሄርን ስላልፈራና ስላላከበረ እግዚአብሄር የተናገረውን ንግግር እንመለከታለን፡፡
እግዚአብሄር ለአባቱ ለንጉስ ናቡከደነፆር እንዴት ታላቅ ክብርን እንደሰጠው መፅሃፍ ቅዱስ ይናገራል፡፡ ናቡከደነፆር በምድር ላይ የነበረው ታላቅነት ሁሉ ከእግዚአብሄር የተሰጠው ክብር ነበር፡፡  
ንጉሥ ሆይ፥ ልዑል አምላክ ለአባትህ ለናቡከደነፆር መንግሥትንና ታላቅነትን ክብርንና ግርማን ሰጠው። ስለ ሰጠው ታላቅነት ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ሁሉ በፊቱ ይንቀጠቀጡና ይፈሩ ነበር፤ የፈቀደውን ይገድል፥ የፈቀደውንም በሕይወት ያኖር ነበር፤ የፈቀደውንም ያነሣ፥ የፈቀደውንም ያዋርድ ነበር። ትንቢተ ዳንኤል 5፡18-19
አባቱ ግን በራሱ እንዴት እንደተመካና የማይገባውን ነገር እንዳደረገ እግዚአብሄርን እንደናቀው ያስታውሰዋል፡፡
ልቡ ግን በታበየ በኵራትም ያደርግ ዘንድ መንፈሱ በጠነከረ ጊዜ፥ ከመንግሥቱ ዙፋን ተዋረደ፥ ክብሩም ተለየው። ትንቢተ ዳንኤል 5፡20
በዚህ ምክኒያት ያ አለም ሁሉ ይገዛለትና ያከብረው ንጉስ እንዴት ከንጉስነት ደረጃ ወርዶ ከሰው በታች እንደተዋረደና ለእግዚአብሄር አምላክነት እውቅና እስሰጥ ድረስ እንደ እንስሳ ሳር እንደበላ ይናገረዋል፡፡
ልዑል አምላክም በሰዎች መንግሥት ላይ እንዲሠለጥን፥ የሚወድደውንም እንዲሾምበት እስኪያውቅ ድረስ ከሰው ልጆች ተይለቶ ተሰደደ፥ ልቡም እንደ አውሬ ልብ ሆነ፥ መኖሪያውም ከምድረ በዳ አህዮች ጋር ነበረ፤ እንደ በሬ ሣር በላ፥ አካሉም በሰማይ ጠል ረሰረሰ። ትንቢተ ዳንኤል 5፡21
ይህን ሁሉ የእግዚአብሄርን አሰራር ትእቢተኛን ማዋረዱን ያየው ልጁ ብልጣሶር ከዚያ እንዳልተማረ ፣ እግዚአብሄርን እንዳልፈራ እና እርሱም እንደታበየ ያስታውሰዋል፡፡
ብልጣሶር ሆይ፥ አንተ ልጁ ስትሆን ይህን ሁሉ እያወቅህ በሰማይ ጌታ ላይ ኰራህ እንጂ ልብህን አላዋረድህም። ትንቢተ ዳንኤል 5፡22
የመቅደሱንም ዕቃዎች በፊትህ አመጡ፥ አንተም መኳንንትህም ሚስቶችህም ቁባቶችህም የወይን ጠጅ ጠጣችሁባቸው ከብርና ከወርቅም ከናስና ከብረትም ከእንጨትና ከድንጋይም የተሠሩትን የማያዩትንም የማይሰሙትንም የማያውቁትንም አማልክት አመሰገንህ፤ ትንፋሽህንና መንገድህን ሁሉ በእጁ የያዘውን አምላክ አላከበርኸውም። ትንቢተ ዳንኤል 5፡23
መፅሃፍ ቅዱስ የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሄርን መፍራት ነው የሚለው ለዚህ ነው፡፡
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ። መጽሐፈ ምሳሌ 1፡7
ትንፋሹንና መንገዱን የያዘውን እግዚአብሄርን ከማያከብር ሰው በላይ ሞኝ የለም፡፡ እግዚአብሄር መኖርና አለመኖርህን ይወስናል፡፡ እግዚአብሄርን በምድር ላይ መንገድህን ይወስናል፡፡ መንገድህን በእጁ የያዘውን እግዚአብሄርን ከማክበር የበለጠ ጥበብ የለም፡፡
ትንፋሽህንና መንገድህን ሁሉ በእጁ የያዘውን አምላክ አላከበርኸውም ትንቢተ ዳንኤል 5፡23
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ትህትና #መዋረድ #ባህሪ #ዝቅታ #ትዕቢት #ትምክህት #መመካት #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Wednesday, March 27, 2019

እጅግ በጣም አስተማማኝ ቦታ


ሁሉም ሰው በህይወት እጅግ አስተማማኝ ቦታን ይፈልጋል፡፡ እጅግ አስተማማኝ ቦታ ደግሞ የልብ ሁኔታ እንጂ የተለየ ቦታ ፣ ከተማ ወይም አገር አይደለም፡፡ የልባችን ሁኔታ የቆምንበትን ቦታ አደገኛ ወይም አስተማማኝ ያደርገዋል፡፡ የልባችን ትእቢት ህይወታችንን አደጋ ላይ ሲጥለው የልባችን መዋረድና ትህትናችን ደግሞ የህይወታችንን ስኬታማነት አስተማማኝ ያደርገዋል፡፡
በህይወት ብዙ አደገኛ ቦታዎች ቢኖሩም እንደ ትእቢት እጅግ አደገኛ ቦታ የለም፡፡ በህይወት ብዙ አስተማማኝ ቦታአዎች ቢኖሩም እንደትህትና እጅግ በጣም አስተማማኝ ቦታ ግን የለም፡፡ ትእቢተኝነት ህይወታችንን አደጋ ላይ የሚጥል በእሳት እንደመጫወት አደገኛ ሁኔታ ነው፡፡ ራስን ማዋረድ ከማንኛውም ውድቀት የሚጠብቅ እጅግ አስተማማኝ ስፍራ ነው፡፡
ትህትና ስኬትን ሲቀድም ትእቢት ውድቀትን ይቀድማል፡፡  
ትዕቢት ጥፋትን፥ ኵሩ መንፈስም ውድቀትን ይቀድማል። መጽሐፈ ምሳሌ 16፡18
ትእቢት ለእግዚአብሄር ፣ ለራሳችንና ለሌሎች ሰዎች ያለንን አመለካከት ሲያዛባ ትህትና ግን ለእግዚአብሄር ፣ ለራሳችንና ለሌሎች ያለንን አመለካከት ያስተካክላል፡፡
ትእቢት በእኛ ላይ የእግዚአብሄርን ተቃውሞ ሲቀሰቅስ ትህትና የእግዚአብሄርን እርዳታ ያስገኝልናል፡፡ ትህትና አግዚአብሄር ከእኛ ጋር እንዲወግን ሲያደርገው ትእቢት እግዚአብሄር ከእኛ ጋር እንዲቃረነን ፣ የእኛ ተቃራኒ እንሆንና መንገዳችን ላይ እንዲቆም ያደርገዋል፡፡
ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ይላል። የያዕቆብ መልእክት 4፡6
ትህትናችን ለእግዚአብሄር ትክክለኛውን የአምላክነቱን ቦታ ሲሰጠው ትእቢታችን ግን የእግዚአብሄርን የአምላክነቱን እውቅና ይነፍገዋል፡፡
ትህትና የእግዚአብሄርንም አብሮነት ሲያመጣ ትእቢት የእግዚአብሄርን ቁጣ ይቀሰቅሳል፡፡ የልባችን ትህትና እግዚአብሄር ደስ ብሎት የሚያየውና የሚጎበኘው ሰው ሲያደርገን ትእቢት ደግሞ እግዚአብሄር ፊቱን እንዲመልስብን ያደርጋል፡፡
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሰማይ ዙፋኔ ነው፥ ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ የምትሠሩልኝ ቤት ምን ዓይነት ነው? የማርፍበትስ ስፍራ ምንድር ነው? እነዚህን ሁሉ እጄ ሠርታለችና እነዚህ ሁሉ የእኔ ናቸው፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን ወደዚህ ወደ ትሑት፥ መንፈሱም ወደ ተሰበረ፥ በቃሌም ወደሚንቀጠቀጥ ሰው እመለከታለሁ። ትንቢተ ኢሳይያስ 66፡1-2
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ትህትና #መዋረድ #ባህሪ #ዝቅታ #ትዕቢት #ትምክህት #መመካት #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Tuesday, March 26, 2019

በፍቅር ፍርሃት የለም


ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፥ ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም አይደለም። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፡18
ፍቅር ከእምነት ይመነጫል፡፡ ፍርሃት ደግሞ ከጥርጥር ይመነጫል፡፡
ፍቅር ሁሉን ያምናል፡፡
ፍቅር ሁሉን ያምናል፡፡ 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡7
ፍቅር እና ፍርሃት አብረው አይሄዱም፡፡ ፍቅር ካለ ፍርሃት ለቆ ይወጣል፡፡ ፍርሃት ካለ ደግሞ ፍቅር በሙላት የለም ማለት ነው፡፡ የፍርሃት መኖር የፍቅር መጉደል ትክክለኛ ማስረጃ ነው፡፡ ፍርሃት ካለ ፍቅር ሙሉ አይደለምና የፍቅር ችግር ሊፈተሽ ይገባዋል፡፡  
ፍቅር ነፃነት ነው፡፡ ፍርሃት ባርነት ነው፡፡ ነፃነትና ባርነት አብረው እንደማይኖሩ ሁሉ ፍቅርና ፍርሃት አብረው ሊኖሩ አይችሉም፡፡
ፍርሃት ራሱን ይሰስታል፡፡ ፍቅር ራሱን ይሰጣል፡፡  
በህይወታችሁ የምትፈሩት ነገር ካለ በዚያ አቅጣጫ ጥርጥር አለባችሁ ማለት ነው፡፡ በህይወታችሁ የምትፈሩት ነገር ካለ በዚያ አቅጣጫ እምነት ጎድሏችኋል ማለት ነው፡፡ በህይወታችሁ የምትፈሩት ነገር ካለ ስለዚያ ነገር እግዚአብሄርን አላመናችሁም ማለት ነው፡፡
በህይወታችሁ የምትፈሩት ነገር ካለ በዚያ አቅጣጫ የሚመራችሁ ፍቅር ሳይሆን ፍርሃት ነው ማለት ነው፡፡ በህይወታችሁ የምትፈሩት ነገር ካለ ቅጣትን ትፈራላችሁ ማለት ነው፡፡
ፍቅር ብርሃን ነው፡፡ በፍቅር የሚያስፈራ ምንም ነገር የለም፡፡ ፍቅር ንፁህ ነው፡፡ ንፅህና ድፍረትን ይሰጣል እንጂ አያሳቅቅም አያስፈራም፡፡ ፍቅር ሙሉ ነው፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ፍቅር #መንፈስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ፍርሃት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ትዕግስት #መንፈስቅዱስ #ምስክር #ልብ #መሪ

Saturday, March 23, 2019

አውቆ ነው

በህይወት በሰዎች በደል አለመሰናከልን የመሰለ ታላቅ ችሎታ የለም፡፡ ተበድሎም ማለፍን የመሰለ ነፃነት የለም፡፡ ሰው የሚያቆስል ንግግር ሲናገርህ ሰምተህ እንዳልሰማህ ማለፍና ህይወትህን መቀጠል ሀብት ነው፡፡  የናቀህን መልሰህ ለመናቅ የሚፈትንህን ፈተና በትግስት ማለፍና የናቀህን አለመናቅን የመሰለ በረከት የለም፡፡
ይቅር አለማለት የአንዳንድ ሰዎችን እምቅ ጉልበት በመብላት ህይወታቸውን ሽባ አድርጓል፡፡ በደልን አለመተው የአንዳንድ ሰውን ሩጫ ገቷል፡፡ በደልን መቁጠር ብዙ ሰዎችን ጠላልፎ ከህይወት መንገድ ጥሏል፡፡  
ይቅር አለማለት ጉልበትን ላልታለመለት አላማ በከንቱ ማባከን ነው፡፡
እግዚአብሄር ለእኛ ነው እግዚአብሔር በክፉ አይፈትነንም፡፡
እንዲያውም ከምንችለው በላይ እንድንፈተን አይፈቅድም፡፡ የበደለን ይቅር ማለት እንደምንችል ያውቃል፡፡ በህይወታችን ያለፈው ፈተና ሁሉ ያለፈው ፈተናውን ሁሉ ልናልፈው እንደምንችል እግዚአበሄር አውቆ ነው፡፡
ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10፡13
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #የሚረዳንን #ፀሎት #እውቀት #ምስጋና #ትህትና #ልብ #እምነት #ፀሎት #ማማጠን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

የሚበድል ሰው ይታዘንለታል እንጂ አይቀናበትም


የሚበድል ሰው ያልገባው ነገር አለ፡፡ የሚበድል ሰው የተሳሳተው ነገር አለ፡፡ የሚበድል ሰው የጎደለው እውቀት አለ፡፡ የሚበድል ሰው የጠፋበት መንገድ አለ፡፡ የሚበድል ሰው የሚያደርገውን ነገር በሚገባ አያውቀውም፡፡
አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ሉቃስ 2334
ስለዚህ የሚበድል ሰው የሚቀናበት ሰው አይደለም፡፡ የሚበድል ሰው ቢያንስ በበደለበት ነገር ሊከተሉት የሚገባ ጥሩ ሞዴል አይደለም፡፡ የሚበድል ሰው የሚፎካከሩት ጠንካራ ሰው አይደለም፡፡
የሚበድል ሰው የሚታዘንለት ሰው ነው፡፡ የሚበድል ሰው ድጋፍ የሚፈልግ የተቸገረ ሰው ነው፡፡ ሰው ካልቸገረውና መንገዱ ካልጠፋው በስተቀር ሰውን በመበደል መሳሳት አይፈልግም፡፡ የሚበድል ሰው ራሱን ማዋረድና ንስሃ መግባት የሚያስፈልጉት ብዙ ስራ የሚጠብቀው ሰው ነው፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ እናንተ ሰውን ከምትበድሉ እናንተ ብትበደሉ ይሻላችኋል ብሎ የሚመክረው ስለዚህ ነው፡፡
እንግዲህ ፈጽሞ የእርስ በርስ ሙግት እንዳለባችሁ በእናንተ ጉድለት ነው። ብትበደሉ አይሻልምን? ብትታለሉስ አይሻልምን? 1 ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 67
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እግዚአብሔር #ይቅርታ #ምህረት #ፍርድ #ጠላት #ዲያቢሎስ #ስፍራ #ኢየሱስ #ጥላቻ #ትእቢት #መራርነት #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Friday, March 22, 2019

የጥላቻን ዜና በማስፋፋት ለጊዜው የሚጠቀሙ የተሸነፉ ፖለቲከኞች ብቻ ናቸው



ፖለቲካ የህዝብ አስተዳደር ስርአት ነው፡፡ ፖለቲካ በራሱ ክፉ አይደለም፡፡ ማንኛውም ሙያ በክፉ ሰዎች እንደሚበላሽ ሁሉ ግን ፖለቲካም በክፉ ሰዎች ሊበላሽ አላማውንም ሊስት ይችላል፡፡
ይህ ደግሞ በመንግስት አካላት ያሉትን ፖለቲከኞች ብቻ ሳይሆን በህዝብ መገናኛ ዘዴዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች የራሳቸውን ትንተና የሚሰጡትንና አክቲቪስቶችን ሁሉ ያጠቃልላል፡፡
ፖለቲካ ወቅታዊውን የህዝብን ፍላጎት መረዳት መተንነተንና የተሻለ አማራጭን ማቅረብን ይጠይቃል፡፡ ፖለቲካ ህዝብን ወደ እረፍት ሰላም እና ብልፅግና የሚያደርስን የተሻለ ሃሳብን ማምጣት ይጠይቃል፡፡ እውነተኛ ፖለቲከኝነት ቀላል ስራ አይደለም፡፡ እውነተኛ ፖለቲከኝነት በጠለቀ እውቀት ፖሊሲ መቅረፅን በዚያ ዙሪያ ህዝብን ማንቃትና በአንድ አላማ ስር ማንቀሳስን ወደልማትና ብልፅግና መምራትን ይጠይቃል፡፡
ፖለቲከኛ ያለው ብቸኛ መሳሪያ የተሻለ ሃሳብ ነው፡፡ ፖለቲከኛ የተሻለ ሃሳብን ለማምጣት የሚተጋና በተሻለው ሃሳብ ዙሪያ ሰዎችን ለማንቀሳቀስ የሚያስተምር የሚያነቃና የሚሰራ ነው፡፡
እውነተኛም የፖለቲካ ስልጣን የሚገኘው አንድን የተሻለ ሃሳብ ከተቀበለ ህዝብ ነው፡፡ የፖለቲካ ስልጣን ሃሳብ በህዝብ ተቀባይነት በማግኘት ብቻ ይመጣል፡፡ የፖለቲካ ስልጣን በረብሻ አይመጣም፡፡ የፖለቲካ ስልጣን ሰዎችን ለብጥብጥ በማነሳሳት አይመጣም፡፡ የፖለቲካ ስልጣን ጥላቻን በመንዛት አይመጣም፡፡
አገራችን ኢትዮጲያ በብዙ እውነተኛ ፖለቲከኞች የተሞላች አገር ነች፡፡ ህዝባቸውን የሚወዱና ለህዝባቸው የሚሰሩ ብዙ ፖለቲከኞችን አፍርታለች፡፡
ነገር ግን የፖለቲከኝነትን ስራውን የማይፈልጉ ነገር ግን በአቋራጭ የፖለቲካ ስልጣንን የሚፈልጉ ፖለቲከኞችም አንዳንዴ ይታያሉ፡፡ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ሃሳብን ከማምጣት እና የህዝብን ልብ በተሻለ ሃሳብ ከማሸነፍ ይልቅ የሰውን አለማወቅ ተጠቅመው በውሸት ዜናዎች የራሳቸውን የግል አላማ ሊያሳኩ የሚጥሩ ፖለቲከኞችም አሉ፡፡
የአገሪቱን ሁኔታ በእውቀት በመረዳትና በመተንተን ሳይሆን የሰዎችን ችግር እየነካኩ በዚያም የፖለቲካ ነጥብ ሊያስመዘግቡ የሚፈልጉ ስነምግባር የጎደላቸው ፖለቲከኞች ከመንግስትም ከመገናኛ ብዙሃንም እንዲሁም ከአክትቪስቶችም አልጠፉም፡፡
የተሻለ ሃሳብ በማቅርብ በሃሳብ ውድድር ለማሸነፍ አቅቷቸው ጥላቻን በመዝራት የሰውን ስሜት የሚቀሰቅሱና በህዝቦች መካከል ጥርጣሬና አለመተማመን የሚፈጥሩ ይገኙበታል፡፡ የፖለቲካ እውቀታቸውን ለማሳደግ እና ለማስፋት በማንበብና በመመርመር ፋንታ ጊዜያቸውን ሁሉ ረብሻ ሊያስነሳ የሚችልን ወቅታዊ ወሬን የሚፈላለጉ የፖለቲካ ስነምግባር የጎደላቸው ይታያሉ፡፡
በተሻለ ሃሳብ የማሸነፍ አቅም ሲያጥራቸው ህብረተሰቡን ስጋቱን በማባባስ በችግረኛው ህብረተሰብ ላይ ተረማመደው የተሻለ ጥቅም ለማግኘት የሚፈልጉ የፖለቲካ ስነምግባር የማይገዳቸውንም ተመልክተናል፡፡
በተሻለ ሃሳብ ህዝቦችን ከማቀራረብና ለአንድ አገር ሰላም ልማትና አንድነት ከመስራት ይልቅ አገር በህዝቦች አለመተማመን ብትታመስ ምንም ደንታ የማይሰጣቸው የተሸነፉ ፖለቲከኞችም ይታዩባታል፡፡ የሚናገሩት የስድብ እና የንቀት ንግግር በህዝቦች መካከል ለሚያመጣው መቃቃር ግድ የሌላቸው ለጊዜያዊ ታዋቂነታቸው ብቻ የሚያስቡ ፖለቲከኞች አሉ፡፡ ህዝቡ በጥቃቅን ነገሮች ላይ ድንጋርይ መወራወሩት ትቶ ድህነትን በመዋጋት ወደልማትና ብልፅግና የሚሄድበትን መንገድ ለመፈለግ የሚያስችልን ከፍ ያለን ሃሳብ ማምጣት የማይችሉ ሰዎችን በማናቆር ብቻ ፖለቲከኞች እንደሆኑ የሚሰማቸው ይገኛሉ፡፡ ህዝቡ እርስ በእርሱ መፎካሩንና መወዳደሩን ትቶ ለአገር እንዲሰራ የሚያሳሙበት ሃሳብ ስለሚያጥራቸው በወቅታዊ ችግሮች ላይ ተጠምደው ጊዜያዊ ጥቅምን ያሳድዳሉ፡፡
ከራሳቸው ጥቅም በላይ የአገር እና የህዝብን ጥቅም የሚያስቀድሙ ፖለቲከኞች እንዳሉ መጠን ፖለቲካ እንደ ማንኛውም ሙያ ትምህርትና እውቀት የማይፈልግ የሚመስላቸው ይገኛሉ፡፡ እንወክለዋለን ከሚሉት ህዝብ ውጪ ላለውን ለሌላው ህዝብ የፍቅርና የርህራሄ ልብ የሌላቸው ከእነርሱ የተለየውን ህዝብ ሲሰድቡ እና የንቀትን ንግግር ሲናገሩ የሚውሉ ፖለቲከኞች ይገኛሉ፡፡   
በህዝቦች መካከል መቀራረብን መደራደርን የማይፈልጉ እና የማያበረታቱ የራሴ መንገድ ብቻ የሚሉ ፖለቲከኞች ያላቸው አንድ መሳሪያ ጥላቻን ማስፋፋት እና በህዝቦች መቃቃርና መናቆር በጊዜያዊነት ተጠቃሚ መሆን ብቻ ነው፡፡ በግልፅ በአደባባይ ሊሉት የማይፈልጉትን በማህበራዊ ሚዲያዎች ጀርባ እየተደበቁ ጥላቻን የሚያስፋፉ ስርአት አልበኛ ሰዎች አልታጡም፡፡
ለጊዜው የተሳካላቸው ይመስላችው ይሆናል እንጂ ሃሰተኛ ፖለቲከኞች መጋለጣቸው አይቀርም፡፡ ህዝብን የሚያቀራረብ ፍትሃዊ የሆነ የተሻለ ሃሳብን ማቅረብ እንጂ ጥላቻን በማስፋፋት የሚጎዳ እንጂ የሚጠቀም ማንም ሰው አይኖርም፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #በክርስቶስ #መንፈስ #ማንነት #መልክ #አምሳል #የእግዚአብሄርልጅ #ክብር #ብሔር #ቋንቋ #ወገን #ነገድ #አፍሪካ #ኢትዮጲያ #ነገድ #ቤተሰብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ዘረኝነት #የእግዚአብሄርመንግስት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አዲስፍጥረት #ክርስቶስ #የእግዚአብሄርቤተሰብ #ማእረግ #ስልጣን #ዘውግ

Thursday, March 21, 2019

ዘረኝነት ዘር የለውም



ዘረኝነት እጅግ ሊኮንን የሚገባ አፀያፊ አስተሳሰብና ድርጊት ነው፡፡ ዘረኝነት የሚለውን ቃል ብዙ ሰዎች ለብዙ ነገር ሲጠቀሙበት ይስተዋላል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ዘረኝነት በትክክል ተርጉመው ከሁኔታው ጋር አያየዝው ጥሩ የሆነ እውቀት ለሌሎች ሲያካፍሉ ይታያሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ዘረኝነት የሚለውን ቃል የሚጠቀሙበትን መንገድ ስንመለከት በእውነት ሃሳቡን ተረድተውታል ወይ ብለን እንድንጠይቅ ያስገድደናል፡፡  
አንዳንድ ሰዎች ዘረኝነት የሚለውን ቃል በትክክል ባለመረዳት በተለያየ ንግግራቸው እና ፅሁፋቸው ውስጥ ሲጠቀሙት እና ሰዎችን ከማስተማርና ከማንቃት ይልቅ ሲያደናግሩ እናያለን፡፡ ዘረፅነት የሚለውን ቃል የሚጠቀሙት ቃሉ ታዋቂ ስለሆነ ብቻ እንጂ ምን ማለት እንደሆነ ተረድተውት እንዳይደለ አነጋገራቸው በግልፅ ያሳያል፡፡ አንዳንድ ሰዎች የዘረኝነትን ቃሉን የሚጠቀሙት በቅጡ ተረድተውት ሳይሆን የራሳቸውን ሃሳብ ብቻ ለማስፈፀም ሲሉ ብቻ ነው፡፡
ዘረኝነት ብለው በብዛት የሚጮሁ አንዳንድ ሰዎች ዘረኛ ነው ብለው ከሚኮንኑት ወገን ይልቅ እነርሱ ራሳቸው ዘረኛ ሆነው ይገኛሉ፡፡
ሁላችንም እኩል ተደርገን ተፈጥረን ሳለ ዘረኝነት የሌላውን ዘር የመናቅ ፣ የመግፋትና የማንኳሰስ ክፉ በሽታ ነው፡፡ ከእኔ ዘር ያንሳል ብለህ የምታስብው ምንም ዘር ካለ ዘረኛ ለመፈለግ ሌላ ቦታ መሄድ አይጠበቅብህም አንተው ዘረኛ ነህ፡፡
ዘረኝነት በምንም መልኩ ሊበረታታ የማይገባው ክፉ ነው፡፡
ዘረኝነትን በሚገባ ካልተረዳነው መወገዝ የማይገባውን እያወገዝን መበረታታት የማይገባውን እያበረታታን የመፍትሄው አካል መሆን ሲገባን የችግሩ አካል ሆነን በከንቱ ጊዜያችንን እናባክናለን፡፡
ዘረኝነት ከበታችነት ስሜት ይመጣል፡፡
በራሱ መተማመን የሌለው ሰው የሰው ወይም የአንድ ወገን በራስ መተማን ያሰጋዋል፡፡ ዘረኝነት ከበታችነት ስሜት የተነሳ የበላይነት ስሜትን በማሳየት ይንፀባረቃል፡፡ ዘረኝነት ከተቻለ በሃይል ካልተቻለ ደግሞ በንግግር ሌላውን ወገን ዝቅ ዝቅ ማድረግና ራስን ከፍ በማድረግ ሌላውን ማጥቃት ነው፡፡ ዘረኛ የሆነ ሰው የራሱ ዘር ስኬት የሚደገፈው በሌላው ዘር ውድቀት ላይ ይመስለዋል፡፡ የአንተ ዘር እንዲሳካለት ሌላው ዘር መውደቅ የለበትም፡፡ ስግብግብነትና ንፉግነት ካልሆነ በስተቀር ለሁሉም ዘር የሚበቃ ስኬት አለ፡፡  
ሰው ክቡር ነው፡፡ ሰው ጠቃሚ ነው፡፡ ብዙ ዘር በሚኖርባት አገር ውስጥ እየኖርክ የምትቀበለው ያንተን ዘር ብቻ ከሆነ አንተ ራስህ ዘረኛ ነህ፡፡ ከአንተ የተለየ ዘር በራሱ ቋንቋ መናገር የሚያሳስብህ ከሆነ አንተው ዘረኛ ነህ፡፡
ሰውን እንደ ሀብት ሳይሆን እንደ እዳ ካየኸው መለወጥ ያለብህ የራስህን የሽንፈት አስተሳሰብህን ነው፡፡ በተለይ ከአንተ የተለየን ሰው እንደ ውበት ካላየኸው በስተቀር እያነስክ ትሄዳለህ እንጂ አትሰፋም፡፡
ኢትዮጲያ ውስጥ አንድ ዘርና እንድ ቋንቋ ብቻ ካልኖረ በስተቀር ሰላም አይኖርም ብለህ የምታስብ ከሆንክ ዘረኛው አንተው ነህ፡፡ የኢትዮጲያ ችግር የመጣው ብሄሮች በራሳቸው ቋንቋ መጠቀም ሲጀምሩ ነው ብለህ ካሰብክ ዘረኛው አንተው እንጂ በቋንቋቸው የሚማሩና ብሄሮች አይደሉም፡፡ ኢትዮጲያ ባለአንድ ቋንቋ ስትሆን ብቻ ነው ሰላም የሚመጣው ብለህ የምታስብ ከሆንክ ልብህ በዘረኝነት ክፉ በሽታ አለመያዙን መርምር፡፡ እያንዳንዱ ዘር ቋንቋውን አክብሮ ለኢትዮጲያ አንድነትና ብልፅግና መስራት አይችልም ብለህ ካመንክ ሃሳብህን መለወጥ ያለብህ አንተ ነህ፡፡
አንተ በሚመችህ  ቋንቋ እየተናገርህ ሌላው በቋንቋው ስለተናገረ ዘረኛ የሆነ ከመሰለህ ራስህን መርምር፡፡
የሌላው ብሄር ሰው ሲሰደድና ሲገፋ ምንም ካልመሰለህ ያንተ ብሄር ሲገፋና ሲሰደድ ብቻ ስለዘረኝነት አስከፊነት የምታነሳ ከሆንክ አንተ ራስህ በዘረኝነት ወጥመድ ውስጥ አለመግባትህን አረጋገጥ፡፡
በመከራ ቀን ብትላላ ጉልበትህ ጥቂት ነው። ወደ ሞት የሚነዱትን ታደግ፤ ሊታረዱ የተወሰኑትን አድን። እነሆ፥ ይህን አላወቀውም ብትል፥ ልቦችን የሚመረምር እርሱ አያስተውልምን? ነፍስህንም የሚመለከት እርሱ አያውቅምን? ለሰውስ ሁሉ እንደ ሥራው አይመልስለትምን? መጽሐፈ ምሳሌ 24፡10-12
ዘረኝነት ዘር የለውም፡፡ ዘረኝነት የሁላችንም ፈተና ነው፡፡ ዘረኝነት ዘራችንን በመውደድና የሌላውን ዘር በመጥላት መካከል ያለ ሚዛናዊነትን ያለመጠበቅ ችግር ነው፡፡ ዘረኝነት ዘራችንን በማክበርና ሌላውን ዘር በመናቅ መካከል ያለ ሚዛናዊነትን አለመጠበቅ ችግር ነው፡፡ ዘረኛ ሰው ለአንተ ወይም ለዘርህ ያለው የንቀት አስተያየት አንተም መልሰህ የእርሱን ዘር እንድትንቅ ይፈትንሃል፡፡
ዘረኝነት በሌላ በዘረኝነት አይስተካከልም፡፡ በዘረኛ ሰው ንግግርና አካሄድ ተነሳስተህ አንተም ወደ ዘረኝነት ወጥመድ ውስጥ እንዳተወድቅ መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ ዘረኝነት ወደ አንተም ህይወት እንዳይስፋፋ በአጭሩ የምትቀጨው ዘረኛን ዘረኛ የሚያደርገው የበታችነት ስሜት እንደሆነ አውቀህ ስታዝንለትና ስትራራለት ብቻ ነው፡፡ ዘረኛነት እንዳይስፋፋ የምታደርገው በሌሎች ዘረኝነት ንግግርና ድርጊት ተሸንፈህ አንተም በዘረኝነት ወጥመድ ውስጥ ላለመውደቅ ስታመልጥ ነው፡፡  
ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ። ወደ ሮሜ ሰዎች 12፡21
ከዘረኛ ሰው ጋር ፉክክር ውስጥ መግባት የዘረኞችን ቁጥር ያሳድጋል እንጂ ዘረኝነትን ለመዋጋት መፍትሄ አይሆንም፡፡
ዘር በራሱ ክፉ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ከቤተሰብ ጀምሮ በየደረጃው በዘመድ በጎሳ በብሄር በሃገር አብሮና ተረዳድቶ በወገንተኝነት ስሜት እንዲኖር አድርጎ ነው፡፡ ማንም ሰው ስለተወለደበት ቤተሰብ ጎሳ እና ዘር መሳቀቅና መጸጸት የለበትም፡፡
ከሌሎች ሰዎች ሁሉ ይልቅ ለምን ቤተሰብህን ወደድክ የሚል ሰው እንደሌለ ሁሉ ማንም ዘርህን ለምን ወደድክና አከበርክ የሚል መኖር የለበትም፡፡ ለቤተሰብህ ማደግ ለምን ትተጋለህ የሚልህ እንደሌለ ሁሉ ለዘርህ ማደግ ለምን ትተጋለህ የሚል ሰው አይኖርም፡፡ ቤተሰብህን ስትወድና ስታከብር ዘርህ ይከብራል ያድጋል፡፡ ዘርህ ሲከብርና ሲያድግ አገር ትከብራለች ታደጋለች፡፡ ምድር ለሁላችን የሚበቃ በቂ ምንጭ አላት፡፡ እኔ ዘሬን ለመጥቀም የሌላውን ዘር መጉዳት የለብኝም፡፡ እኔ አገሪቱን ለመጥቀም ዘሬን መጉዳት የለብኝም፡፡ ሁላችንም ከቤተሰባችን ጀምረን እስከ ዘራችንና ብንሰራ አገር ታድጋለች፡፡
ዘረኝነት ዘርን መውደድ ሳይሆን ሌላውን ዘር መጥላት ነው፡፡ ዘረኝነት የራስን ዘር ማክበር ሳይሆን የሌላውን ዘር መናቅ ነው፡፡ ዘረኝነት የራስን ዘር መርዳት ሳይሆን የሌላውን ዘር መጉዳት ነው፡፡ ሌላውን ዘር እንድትጠላና እንድትንቅ የሚያደርግህ ማንኛውም ንግግር በዘረኝነት መርዙ እየመረዘህ እንደሆነ አውቀህ ሽሽ፡፡ ዘረኛ የዘረኝነቱን ንቀትና ጥላቻ ማስተላለፊያ ሊያደርግህ ሲሞክር ዘረኝነቱን ባለመከተልና ባለማስፋፋት ብለጠው፡፡  
ከዘረኝነት ነፃ የወጣ ሰው ከራሱ ዘር አልፎ ሌሎችን ዘሮች በማክበርና በመውደድ ይታወቃል፡፡ ዘረኝነት የሌለበት ሰው እያንዳንዱ ዘር እኩልና እኩል እድል ሊሰጠው እንደሚገባ ያምናል፡፡ ከዘረኝነት ነፃ የሆነ ሰው ጭቆናና በደል ሲደርስ ለራሱ ዘር ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ዘሮች ጥብቅና ሲቆም ይታያል፡፡ አንዱ ዘር ለሌላው ዘር ሲከራከር የምንሰማው ከዘረኝነት ነፃ በሆነ ህብረተሰብ ውስጥ ብቻ ነው፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #በክርስቶስ #መንፈስ #ማንነት #መልክ #አምሳል #የእግዚአብሄርልጅ #ክብር #ብሔር #ቋንቋ #ወገን #ነገድ #አፍሪካ #ኢትዮጲያ #ነገድ #ቤተሰብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ዘረኝነት #የእግዚአብሄርመንግስት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አዲስፍጥረት #ክርስቶስ #የእግዚአብሄርቤተሰብ #ማእረግ #ስልጣን #ዘውግ

Wednesday, March 20, 2019

ፀሎትን ፍሬያማ የሚያደርገው



ፀሎትን ውጤታማ የሚያደርገው ለቅሶዋችን አይደለም፡፡ እውነት ነው ስንፀልይ አንዳንድ ጊዜ ስሜታዊ እንሆንና እናለቅሳለን፡፡ ነገር ግን የፀሎት ውጤት ከለቅሶ ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር የለም፡፡  
ፀሎታችንን ውጤታማ የሚያደርገው መርዘሙ አይደለም፡፡ እውነት ነው አንዳንድ ጊዜ ፀሎታችን ይረዝማል፡፡ አንዳድ ጊዜ ለረጅም ጊዜ ከጌታ ጋር እንነጋገራለን፡፡ ፀሎታችን መርዘሙ ብዙ የፀሎት ርእሶችን ለመፀለይ ካልሆነ በስተቀር ፀሎታችን እንዲሰማ ወይም ፀሎታችን ፍሬያማ እንዲሆን የሚጠቅመው ጥቅም የለም፡፡  
ፀሎታችንን ውጤታማ የሚያደርገው ነገርን መደጋገማችንም አይደለም፡፡ ተመሳሳይን ነገር በደጋገምነው መጠን ፀሎታችን ይሰማል ብለን ማሰብ ሞኝነት ነው፡፡ እውነት ነው ፀሎትን ስንፀልይ ልባችን እስኪያርፍ ድረስና ሸክማችን እንከሚቀል ድረስ መፀለይ አለብን፡፡ ነገር ግን የፀሎት ርእሳችንን በደጋገምነው መጠን ፀሎታችን ይሰማል ብለን ማመን የለብንም፡፡
ፀሎትን ውጤታማ የሚያደርገው ስንፀልይ በምናሳየው ሃይል አይደለም፡፡ ፀሎታችን እንዲሰማ የሚያደርገው በድምፃችን ከፍታ መጠን ወይም በጣም በመወራጨታችን አይደለም፡፡ እግዚአብሄር የልብን ጩኸት ይሰማል፡፡
ፀሎትን ውጤታማ የሚያደርገው ስንናገረው ስላጣፈጥነው አይደልም፡፡ ፀሎታችን እንዲሰማ የሚያደርገው አንደበተ ርቱእ መሆናችን አይደለም፡፡
ፀሎታችን እንዲሰማ የሚያደርገው እንደ ፈቃዱ መፀለያችን ነው፡፡ እንደ ፈቃዱ ከፀለይን እግዚአብሄር ይሰማናል፡፡ እንደ ፈቃዱ ካልፀለይን እግዚአብሄር አይሰማንም፡፡
የእግዚአብሄርን ፈቃድ የምናገኘው በእግዚአብሄር ቃል ውስጥ ነው፡፡ እንደ እግዚአብሄር ቃል ከፀለይን እግዚአብሄር ይሰማናል፡፡ እንደ እግዚአብሄር ፈቃድ ካልፀለይን እግዚአብሄር አይሰማንም፡፡
በእርሱ ዘንድ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ እንደ ፈቃዱ አንዳች ብንለምን ይሰማናል። የምንለምነውንም ሁሉ እንዲሰማልን ብናውቅ ከእርሱ የለመነውን ልመና እንደ ተቀበልን እናውቃለን። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 5፡14-15
በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል። የዮሐንስ ወንጌል 15፡7
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #የእግዚአብሄርፈቃድ #ፀሎት #ልመና #እንዲሰማን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #የእግዚአብሄርቃል #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መጠየቅ #መንበርከክ #ምስጋና


Saturday, March 16, 2019

ታቦቱን መከተል


ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሄር ክብር እግዚአብሄርን ለማክበር ነው፡፡
ሰው የተፈጠረው የፈለገውን ነገር እንዲያደርግ ሳይሆን እግዚአብሄርን እንዲከተል ነው፡፡ ሰው የሚሳካለት እግዚአብሄርን በቅርበት ሲከተል ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄርን የማይከተል ሰው በነገሮች ሊሳካለት ይችላል በእግዚአብሄር ዘንድ ግን አይሳካለትም፡፡
ስለእኛ ከሃጢያት መዳን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሞተና በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ የምናምን ሁላችን የእግዚአብሄር መንፈስ በእኛ ውስጥ ይኖራል፡፡
የእስራኤል ህዝብ ከግብፅ ሲወጣ የእግዚአብሄርን ታቦት ይከተል ነበር፡፡ ታቦቱ ሲቆም ይቆም ነበር ታቦቱ ሲሄድ ደግሞ ይሄድ ነበር፡፡
ሕዝቡን፦ የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦትና ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ፥ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት። መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 3፡3
እንዲሳካልን ሌላ ማንንም ሰው መከተል የለብንም፡፡ እግዚአብሄር ለእያንዳንዳችን የተለየ የስኬት አላማ አለው፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።ትንቢተ ኤርምያስ 29፡11
በብሉይ ኪዳን እስራኤላዊያን ታቦቱን እንደሚከተሉ ሁሉ አሁንም እኛ በውስጥታችን ያለውን የእግዚአብሄርን መንፈስ በመከተል  ይሳካልናል፡፡
በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና። የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል። ወደ ሮሜ ሰዎች 8፡14፣16
እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም ታውቃላችሁ። እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 2፡20፣27
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መንፈስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #አማላጅ #ታቦት #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ኦርቶዶክስ #ማርያም #ቅዱሳን #ተዋህዶ 

Friday, March 15, 2019

የማንቂያ ደውል


እግዚአብሄርን ለሚወዱ ሰዎች ነገር ሁሉ ለበጎ ይደረጋል፡፡
ለምሳሌ እግዚአብሄርን ስንፈልግ ሰው ቢበድለን በደሉ እኛን የሚጥለን ሳይሆን የሚያነቃን ደውላችን ነው፡፡  
ሰው ሲበድለን ስለበደለን ሰው እንድናውቅ እና እንድንረዳ የማንቂያ ደውል ነው፡፡
ሰው ሲበድለን ስለበደለን ሰው እንድናዝን እንድንራራ የማንቂያ ደውል ነው፡፡
ባይበድለን እንድንፀልይለት ትዝ የማይለን ሰው ቢበድለን ስለበደለን ሰው እንድንፀልይና እንድንማልድ የማንቂያ ደውል ነው፡፡
ባይረግመን ጊዜ ወስደን የማንባርከው ሰው ቢረግመን እንድንባርከው ስለእርሱ መልካም እንድድናስብ መልካም እንድንናገርና መልካም እንድናደርግ የማንቂያ ደውል ነው፡፡
እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ የማቴዎስ ወንጌል 5፡44
ሰዎች ሲበድሉን የእግዚአብሄርን መልካምነትና ልበ ሰፊነት ስንቱን እንደቻለ እንድናስብ የሚያደርግ የማንቂያ ደውል ነው፡፡
እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና። የማቴዎስ ወንጌል 5፡45
ሰዎች ሲበድሉን ያሉበትን የህይወት ሁኔታ ችግር ላይ መሆናቸውን ማወቅና አንድ ነገር ማድረግ አለብን፡፡ ሰዎች ሲበድሉን የእኛን ፀሎትና በረከት እንደሚያስፈልጋቸው የማንቂያ ደውሉን መስማትና መረዳት አለብን፡፡ የበደሉንን ሰዎች መልሰን ለመበደል ስንፈተን ይልቁንም በደሉን መልካም ለማድረግ እንደማንቂያ ደውል ልንጠቀምበት ይገባል፡፡
ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3፡9
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #መልካም #ክፉ #አሸንፍ #ብቃት #የእግዚአብሄርችሎታ #የእግዚአብሄርሃይል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ፅድቅ #እግዚአብሄርንመምሰል #ራስንመግዛት #ልብ #ምስክርነት