Popular Posts

Monday, November 14, 2022

የእግዚአብሔር ፈቃድ ወይም ሞት!

 


የእግዚአብሔር ፈቃድ ወይም ሞት!

የተፈጠርኩት ለእግዚአብሔር ክብር እንደሆነ አውቃለሁ፡፡

በስሜ የተጠራውን ለክብሬም የፈጠርሁትን፥ የሠራሁትንና ያደረግሁትን ሁሉ አምጣ እለዋለሁ። ትንቢተ ኢሳይያስ 43፡6-7

በዋጋ እንደተገዛሁ አውቃለሁ፡፡

በዋጋ ተገዝታችኋል፤ የሰው ባሪያዎች አትሁኑ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7፡23

እኔ የራሴ እንዳልሆንኩ አውቃለሁ

በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6፡20

የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ላረጋግጥ እንጂ ምንም ነገር አደርጋለሁ!

የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ላረጋግጥ እንጂ የፈለገውን ያክል ሞኝ ያስብለኝ እንጅ ምንም ነገር አደርጋለሁ፡፡

የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ላረጋግጥ እንጂ ተቃውሞ በሁሉም አቅጣጫ ያስነሳብኝ እንጂ ፈቃዱ እንደሆነ ያመንኩበትን ምንም ነገር አደርጋለሁ፡፡

የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ያላረጋገጥኩት ነገር በወርቅ ቢንቆጠቆጥ ዞር ብዬ እንኳን አላየውም፡፡ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማድረግ የማንንም እሺታ አልጠብቅም፡፡

ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም፥ ወደ ገላትያ ሰዎች 1፡15-16

የእግዚአብሔር ፈቃድ ከሆነ ሰዎች የሚያከብሩትን ነገር ሁሉ እንቃለሁ ሰዎች የሚንቁትን ነገር ሁሉ አከብራለሁ፡፡

አዎን፥ በእውነት ከሁሉ ይልቅ ስለሚበልጥ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ጌታዬ እውቀት ነገር ሁሉ ጉዳት እንዲሆን እቈጥራለሁ፤ ስለ እርሱ ሁሉን ተጐዳሁ፥ ክርስቶስንም አገኝ ዘንድ፥ በክርስቶስም በማመን ያለው ጽድቅ ማለት በእምነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ያለው ጽድቅ እንጂ ከሕግ ለእኔ ያለው ጽድቅ ሳይሆንልኝ፥ በእርሱ እገኝ ዘንድ ሁሉን እንደ ጕድፍ እቈጥራለሁ፤ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 3:8-9

የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ላረጋግጥ እንጂ በሁሉም ዘንድ ያስጠላኝ እንጂ ለሚያስከትልብኝ አደጋ ወይም ሪስክ ራሴን እሰጣለሁ፡፡

ሰውን ወይስ እግዚአብሔርን አሁን እሺ አሰኛለሁን? ወይም ሰውን ደስ ላሰኝ እፈልጋለሁን? አሁን ሰውን ደስ ባሰኝ የክርስቶስ ባሪያ ባልሆንሁም። ወደ ገላትያ ሰዎች 1፡10

የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ላረጋግጥ እንጂ ሁሉን ባጣ እንደክብር እቆጥረዋለሁ፡፡

ከአእላፍ ይልቅ በአደባባዮችህ አንዲት ቀን ትሻላለች፤ በኃጥኣን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ፥ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ። መዝሙር 84፡10

የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዳለበት ያወቅኩትን ነገር ምክኒያቱ ባይገባኝም እንኳን አብሬው እሞታለሁ፡፡

እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ፥ የተሰጣቸውን የተስፋ ቃል አላገኙምና፤ ዳሩ ግን ከሩቅ ሆነው አዩትና ተሳለሙት፥ በምድሪቱም እንግዶችና መጻተኞች እንዲሆኑ ታመኑ። ወደ ዕብራውያን 11፡13

ለእኔ ሃብት ማለት በእጦትም ቢሆን የእግዚአብሔርን ፈቃድ መፈፀም ነው፡፡ ለእኔ ድህነት ማለት ሁሉም ሞልቶለት የእግዚአብሔርን ፈቃድ መሳት አለመፈፀም ነው፡፡ ለእኔ ዝና ማለት በመደበቅ እና በመጥፋት የእግዚአብሔርን ፈቃድ መፈፀም ነው፡፡ ለእኔ ዝነኛ አለመሆን ማለት በአለም ሁሉ ተከቦ እና ተደንቆ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መሳት አለመፈፀም ነው፡፡ ለእኔ ሃያልነት ማለት በድካም የእግዚአብሔርን ፈቃድ መፈፀም እና ጌታን ደስ ማሰኘት ነው፡፡ ለእኔ ድካም ማለት እጅግ ሃያል ሆኖ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር መተላለፍ ነው፡

ለእኔ ስኬት ማለት አይን ውስጥ የማይገባውን የተደበቀውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ መፈፀም ነው፡፡ ለእኔ ውድቀት ማለት የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሌለበትን ታላላቅ ነገር ማድረግ ነው፡፡

የእግዚአብሔር ፈቃድ ከሆነ የሚያስጠላው ያምረኛል፡፡ የእግዚአብሔር ፈቃድ ከሌለበት የሚያምረው ያስጠላኛል፡፡

የእግዚአብሔር ፈቃድ ካለበት የሚመረው ይጣፍጠኛል፡፡ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሌለበት የሚጣፍጠው ነገር ያቅለሸልሸኛል፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa 

Friday, November 11, 2022

Don’t dream big for God.


 Don’t dream big for God.

I hear people say, "Dream big for God." I'm telling you never dream big about God. God is not lacking in dreams. God is sufficiently creative to know what He wants of you. God knows why he created you. God knows what brings the greatest glory into your life.

The best thing you can do instead is to discover what goal He has for your life. Leaving your comfort zone to do what He wants you to do beyond your capabilities is the best thing you can do for Him. The best thing you can do is to go beyond your natural boundaries and be in the realm of the supernatural possibility that he shows you. You leave "your ship" to "walk on the water", obedient to the voice of the master.

"Lord, if it’s you," Peter replied, "tell me to come to you on the water." "Come," he said. Then Peter got down out of the boat, walked on the water and came toward Jesus. Matthew 14:28-29

The best risk you can take is obeying the teacher to do the most "strange" thing on earth. The most effective way to take a risk is to stretch yourself to the level of doing the will of God for your life.

Your childhood dream is too small for God. That's not even his dream for you. It isn’t worth living for. Besides, it is a cheap imitation of God's goal in your life.

Dream big with the Lord!

Abiy Wakuma Dinsa