Popular Posts

Wednesday, November 30, 2016

ፍቅር እና "ፍቅር"

እንደ ፍቅር በጣም አስፈላጊ ነገር የለም፡፡ እንደ ፍቅር ደግሞ ትርጉሙ የተዛባ ነገር በአለም ላይ ምንም ነገር የለም፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ፍቅር የሚሉት ምኞታቸውን ነው፡፡ የፍቅርንና የምኞትን ባህሪያት ከእግዚአብሄር ቃል በመመልከት ልዩነታቸውን እስኪ እንመልከት፡፡
ፍቅር የሚያተኩረው ሌላው ላይ ነው፡፡ ፍቅር ሌላውን በመጥቀም ሌላውን በማንሳት ሌላውን በማገልገልና በሌላው ላይ ዋጋን በመጨመር ላይ ያተኩራል፡፡
ምኞት የሚያተኩረው ራስ ላይ ነው፡፡ ምኞት በማንኛውም ግንኙነት የሚያስበው እርሱ ምን እንደሚያገኝና እንደሚያተርፍ ብቻ ነው፡፡ ፍቅር የሌላውን ፍላጎት ለማሟላት ሲሄድ ምኞት ግን የራሱ ፍላጎት ብቻ ለማሟላት ይሄዳል፡፡
ፍቅር ሌላውን ሲያስቀድም ምኞት ራሱን ያስቀድማል፡፡ ፍቅር የራሱን ፍላጎት ስለሌላው ፍላጎት ያዘገየዋል፡፡ ምኞት ግን ስለሌላው ፍላጎት የሚያዘገየው ምንም ጥቅም የለም፡፡
ሁሉን ይታገሣል፥ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል። 1ኛ ቆሮንቶስ 13፡7
ፍቅር በመረዳት የሚደረግ ሲሆን ምኞት በስሜት የሚመራ ነው፡፡ ፍቅር ሌላውን እንዳይወድ የሚፈትኑትን አሉታዊ ስሜቶች ሰምቶ ፍቅርን ከመከተል አይመለስም፡፡ ምኞት ግን ስሜቱን ብቻ ይከተላል፡፡
ፍቅራችሁ በእውቀትና በማስተዋል ሁሉ ከፊት ይልቅ እያደገ እንዲበዛ ይህን እጸልያለሁ። ፊልጵስዩስ 1፡9
ፍቅር እኔ እበልጣለሁ ፣ እኔ ይገባኛል ፣ እኔ የእኔ ለእኔ ነው ሁልጊዜ የሚለው፡፡ ፍቅር ግን አንተ ይገባሃል ፣ አንተ ትሻላለህ ፣ አንተ ትበልጣለህ ብሎ ሌላውን በትህትና ይቆጥራል፡፡
ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ፥ ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር፤ ፊልጵስዩስ 2፡3
ፍቅር ምክኒያታዊ ያልሆነ ሲሆን ምኞት ምክኒያታዊ ብቻ ነው፡፡ ፍቅር እንካ በእንካ አይደለም፡፡ ፍቅር የሌላውን ሁኔታ ሳያይ የራሱን ሌላውን የማክበር ሃላፊነት ይወጣል፡፡ ምኞት ቀድሞ እንኳን መልካም ካደረገ ያደረገው የተሻለ ጥቅምን ፈልጎ ብቻ ነው፡፡ ወይም መልካም ላደረጉለት ብቻ ነው መልካም የሚያደርገው፡፡ ምኞት ምንም ጥቅም ያላገኘበት ወይም ወደፊት የማያገኝበት ከሆነ ዞር ብሎ አያየውም፡፡
የሚወዱአችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ? አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? ማቴዎስ 5፡46-47
ዓይን ስለ ዓይን ጥርስም ስለ ጥርስ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ክፉውን አትቃወሙ፤ ዳሩ ግን ቀኝ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ ሁለተኛውን ደግሞ አዙርለት፤ ማቴዎስ 5፡38-39
ፍቅር የህይወት ዘመን ሃላፊነት ሲሆን ምኞት የአንድ ሰሞን ጊዜያዊ ነው፡፡ ፍቅር የእውነተኛ ሰው ህይወቱ ነው፡፡ ሰው ፍቅርን የሚከታተለው በውሳኔ ስለሆነ ሰው ከፍቅር መቼም አይለወጥም፡፡ ምኞት ግን ከሌላው በሚገኘው ጥቅም ላይ ስለተመሰረተ ጥቅሙ በቆመ ጊዜ ለመቀጠል አቅም አይኖረውም፡፡
እንዲህም ከሆነ፥ እምነት ተስፋ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፤ ከእነዚህም የሚበልጠው ፍቅር ነው። 1ኛ ቆሮንቶስ 13፡13
ፍቅር ሌላውን ለማገልገል በሌላው ላይ የማይደገፍ ሲሆን ምኞት የራሱን ስለሚፈልግ በሌላው ላይ ያለመጠን የሚደገፍ ነው፡፡ ፍቅር ለሰው መልካም ለማሰብ መልካም ለመናገርና መልካም ለማድረግ የማንም ፈቃድ አያስፈልገውም፡፡ ምኞት ግን ሌላውን ለማስወጣት በሌላው ላይ ከመጠን ያለፈ መደገፍ ይኖርበታል፡፡ ስለዚህ ምኞት ሁልጊዜ ያዝናል ተስፋ ይቆርጣል፡፡
ፍቅር ሌላውን በማርካት ብቻ ይረካል ምኞት ራሱን በማርካት ብቻ ይረካል፡፡ ፍቅር የምሰጠው አለኝ ባለጠጋ ነኝ ስለሚል ለሌላው በመስጠት ይረካል፡፡ ምኞት ግን ምስኪን እኔ አስተሳሰብ ስላለው እኔ ምንም የለኝም ፣ የምሰጠው የለኝም ፣ ደሃ ነኝ የሚሰጠኝ እፈልጋለሁ ስለሚል የሚረካው በመቀበል ብቻ ነው ፡፡
ፍቅር ሌላውን ለመንከባከብ እንዲያስችለው ሌላውን ለመረዳት ይጥራል፡፡ ፍቅር ትጉህ ነው፡፡ ፍቅር ሌላውን በተሻለ ለመንከባከብ እንዲያስችለው የሌላውን ፍላጎትና ባህሪ በትጋት ያጠናል፡፡ ምኞት ለሌላው ግድ ስለሌለው ሌላውን ለማጥናት ስንፍና ስለአለበት የራሱን ስሜት ብቻ ያዳምጣል፡፡ ፍቅር በስንፍና እይመጣም ፍቅር ጥረትና ድካም ይጠይቃል፡፡
በጸሎታችን ጊዜ ስለ እናንተ ስናሳስብ፥ የእምነታችሁን ስራ የፍቅራችሁንም ድካም በጌታችንም በኢየሱስ ክርስቶስ ያለውን የተስፋችሁን መጽናት በአምላካችንና በአባታችን ፊት ሳናቋርጥ እያሰብን፥ እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ በሁላችሁ ምክንያት እናመሰግናለን፤ 1ኛ ተሰሎንቄ 1፥2-3
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልዕክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ፍቅር #ምኞት #አላማ #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ጥሪ #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Tuesday, November 29, 2016

ኤጭ ደግሞ ለኑሮ

እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ማቴዎስ 6፡31-32
ኢየሱስን የምንከተል ሁላችን ለኑሮ እንዳንጨነቅ ኢየሱስ ደጋግሞ ደጋግሞ ያስተምረናል፡፡ ስለኑሮ መጨነቅ የእናንተ አይደለም እያለን ነው፡፡ ለኑሮ መጨነቅ አይመጥናችሁም እያለን ነው፡፡ ስለኑሮ መጨነቅ ክብራችሁ አይፈቅደውም እያለንም ነው፡፡
ስለኑሮ መጨነቅንና ለመኖር መኖርን እንደትልቅ ነገር አይተውት የሚኖሩለትና የሚሞቱለት ሰዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ለመኖር ነው የሚኖሩትና የሚሰሩት፡፡ እነዚህ ሰዎች ለመኖር የማያደርጉት ነገር የለም፡፡ ከመኖር ውጭ የሚኖሩለት ምንም ነገር የላቸውም፡፡ እነዚህ ሰዎች መኖር የሙሉ ጊዜ ሃላፊነት ነው፡፡
ህይወታቸውን ሁሉ የሰጡት ለመኖር የሚያስፈልገውን በማሟላት ነው፡፡ የሚኖሩለት የእግዚአብሄር ጥሪ በህይወታቸው ላይ የለም፡፡ እግዚአብሄር ለህይወታቸው ያስቀመጠውን የተለየ አላማ አላገኙትም፡፡ ስለሚበላና ስለሚለበስ ከመጨነቅ የተሻለ ስራ የላቸውም፡፡
ስለኑሮ መጨነቅ እግዚአብሄርን የማያውቁ የተሻለ የህይወት አላማ የሌላቸው ሰዎች የህይወት ዘይቤ እንደሆነ ኢየሱስ ያስተምራል፡፡ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ማቴዎስ 6፡32
ለመኖር የሚጨነቁት ሌላ ምንም ሃላፊነት የሌለባቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ለመኖር የሚጨነቁት ሌላ የተሻለ የሚኖሩለት የህይወት ራእይ ስለሌላቸው ነው፡፡ ለመኖር የሚጨነቁት በህይወታቸው የሚከተሉት የእግዚአብሄር አላማ በህይወታቸው የሌላቸው ናቸው፡፡ እነዚያ ለመኖር የሚጨነቁት መንገዱ የጠፋባቸውና እግዚአብሄር ለከበረ የህይወት አላማ እግዚአብሄርን ለማምለክና ለማገልገል እንደጠራቸው የማያውቁ ናቸው፡፡ ስለኑሮ የሚጨነቁት የሚፈልጉት የእግዚአብሄር መንግስት ስሌላቸው ነው፡፡ እነዚህ ስለሚበላና ስለሚጠጣ የሚጨነቁት የሚፈልጉት የእግዚአብሄር ፅድቅ ስለሌላቸው ነው፡፡
ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ማቴዎስ 6፡33
ኑሮን ዋና የህይወት አላማ ያደረጉት ናቸው ስለመኖር ብለው የሚኖሩት፡፡ እነዚህ ሰዎች ህይወታቸውን ሁሉ የሚጨርሱት ለመኖር በመጨነቅ ለመኖር በመሞከር ብቻ ነው፡፡ እንደው ከመኖር የተሻለ ምንም የሚከተሉት የህይወት አላማ የላቸውም፡፡ የመጨረሻውና ታላቁ ግባቸው መኖር ነው፡፡
በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን። 1ኛ ቆሮንቶስ 15፡19
ለእነርሱ መኖር ብቻውን ትልቅ ነገር ነው፡፡ ለእነርሱ እግዚአብሄር ሊሰሩት ያዘጋጀውን መልካሙን ስራ መስራት ሳይሆን ኖሮ ኖሮ መሞት ትልቅ ገድል ነው፡፡
እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን። ኤፌሶን 2፡10
ኢየሱስ ስለኑሮ አትኑሩ ለመንግስቴ ኑሩ እያለን ነው፡፡ ፅድቅን ለማሳየት ስትኖሩ ይህ ሁሉ ነገር ምርቃት ነው እያለን ነው፡፡
እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ማቴዎስ 6፡31-32
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #ህልም #አላማ #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ጥሪ #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Friday, November 25, 2016

ካለ ንግግር ማመስገኛ መንገዶች

እግዚአብሄርን ማመስገን በአፍ እግዚአብሄር ሆይ አመሰግንሃልሁ ከማለት ያለፈ ነው፡፡
ለእግዚአብሄር መስእት ያመጡ ሰዎች በእግዚአብሄር ተገስፀዋል፡፡ የምስጋናን መስዋእት እንዲያመጡ እግዚአብሄር አዞዋል፡፡ በመኝሃፍ ቅዱስ ካለቃልና ካለንግግር ቀን ለቀን የእግዚአበሄርን ክብር እንደሚናገሩ ያስተምራል፡፡
ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል። ቀን ለቀን ነገርን ታወጣለች፥ ሌሊትም ለሌሊት እውቀትን ትናገራለች። ነገር የለም መናገርም የለም፥ ድምፃቸውም አይሰማም። ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ፥ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ። መዝሙር 19፡1-4
እግዚአብሄርን በቃላችን አመስግነን አንጠግብም፡፡ እግዚአብሄር ካደረገልን አንፃር የእግዚአብሄርን ውለታ በምንም አንከፍለውም፡፡ ከንግግር ውጭ ግን እግዚአብሄርን አመሰግንሃልሁ የምንልበት ሌሎች መንገዶች አሉ፡፡ ከንግግር ያለፈ በእያንዳንዱ አስተሳሰባችንና አካሄዳችን እግዚአብሄርን ለማመስገን እድሉ ተሰጥቶናል፡፡ ካለንግግር እግዚአብሄርን የምናመሰግንበት ሰባቱ የህይወት ዘይቤዎች
  • · ለሰዎች በጎን ማድረግ
ከእግዚአብሄር መልካምነት የተቀበለ ሰው ሁሉ በተራው ለሰዎች መልካም በማድረግ እግዚአብሄርን በተዘዋዋሪም አመሰግናለሁ ይለዋል፡፡ መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ። ማቴዎስ 5፡16
  • · ሰዎችን ይቅር ማለት
እግዚአብሄር እርሱን ይቅር እንዳለው የተረዳና አመሰግናለሁ የሚል ሰው በተራው ይቅርታ የሚፈልግ ሰው ሲያገኝ ይቅር በማለት ካለንግግር እግዚአብሄርን በድርጊቱ ያመሰግናል፡፡ ብዙም ከተሰጠው ሰው ሁሉ ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል፥ ብዙ አደራም ከተሰጠው ከእርሱ አብዝተው ይሹበታል።ሉቃስ 12፡48 ከዚያ ወዲያ ጌታው ጠርቶ፦ አንተ ክፉ ባሪያ፥ ስለ ለመንኸኝ ያን ዕዳ ሁሉ ተውሁልህ፤ እኔ እንደ ማርሁህ ባልንጀራህ የሆነውን ያን ባሪያ ልትምረው ለአንተስ አይገባህምን? አለው። ማቴዎስ 18፡32-33
  • · እግዚአብሄርን መታዘዘ
እግዚአብሄርን በንግግር ብቻ ማመስገን ፈፅሞ አያረካንም ፡፡ እግዚአብሄርን የምናመሰግንበት ሌላው መንገድ እግዚአብሄር እንዳስደሰተን እርሱን በመታዘዝ ማስደሰት ነው፡፡ በጌታ እንደረካንና ደስ እንደተሰኘን ማሳያው መንገድ ቃሉን በመታዘዝ በድርጊት ስናመሰግነው ነው፡፡ ኢየሱስም መለሰ አለውም፦ የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን። ዮሃንስ 14፡23
  • · አለማጉረምረም
ህይወቱ እግዚአብሄርን የሚያመሰገን ሰው በንግግሩ እግዚአብሄርን ማመስገን ብቻ ሳይሆን በሚያልፍበት በማንኛውም መንገድ እግዚአብሄር ላይ አያጉረመርምም፡፡ የምትባረክ ነፍስ ትጠግባለች፥ የረካም እርሱ ደግሞ ይረካል። ምሳሌ 11፥25 ደስ ያላት ልብ መልካም መድኃኒት ናት፤ ያዘነች ነፍስ ግን አጥንትን ታደርቃለች። ምሳሌ 17፡22
  • · ራስን ማዋረድና ወይም ትህትና
የሚያመሰግን ልብ ሁል ጊዜ ራሱን ለማዋረድ ዝግጁ ነው፡፡ የሚያመሰግን ልብ ያለው ሰው ሌሎች ሊሰሩት የማይፈቅዱትን ዝቅ ያለውን ነገር ያደረጋል፡፡ የምስጋና ህይወት ያለው ሰው ራሱን ከዝቅተኛ ሰዎች ጋር ሲያስተባብር ይታያል፡፡ እርስ በርሳችሁ በመስማማት ኑሩ። ዝቅተኛ ኑሮ ውስጥ ካሉ ጋር አብራችሁ ለመሆን ፍቀዱ እንጂ አትኵራሩ፤ በራሳችሁም አትመኩ። ሮሜ 12፡16 (መደበኛ ትርጉም)
  • · በአስተሳሰብ ህይወታችን እግዚአብሄርን መፍራት
እግዚአብሄርን የምናመሰግን ከሆነ የእግዚአብሄር ያልሆኑትን ሃሳቦች እንጠየፋቸዋለን፡፡ የሚያመሰግን ልብ ካለን የእግዚአብሄርንና የእኛ ጠላት የሆነውን የሰይጣንን ሃሳብ አናስተናግድም፡፡ ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ። ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። መዝሙር 1፡1-2
  • እግዚአብሄርን መፈለግ
ለእግዚአብሄር በምስጋና የተሞላ ልብ ያለው ሰው ሁል ጊዜ እግዚአብሄርን በሁሉም የህይወት ክፍሉ ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ጥሩ፥ ለአሕዛብም ሥራውን አውሩ። ተቀኙለት፥ ዘምሩለት፥ ተአምራቱንም ሁሉ ተናገሩ። በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው። እግዚአብሔርን ፈልጉት ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። መዝሙር 105፡1-4
ይህንን ፅሁፍ ሼር ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ምስጋና #እምነት #መደገፍ #ልብ #ቃል #ምስጉን #ሃሳብ #ማሰላሰል #ወንጌል #ደቀመዝሙር #ኢየሱስ #ጌታ #መዳን #አማርኛ #ኢትዮጲያ #አቢይዋቁማ #ፌስቡክ #አዋጅ

10 Reasons Why Every Day is a Thanksgiving Day?

It is very wise to seize any opportunity set-aside to give thanks to the Lord.  But thanks-giving isn’t a once a year activity to be observed. There are good reasons that every day must be a thanksgiving day.
There are valid reasons that in everything we give thanks to the Lord and there are enough reasons that God deserves our thank you in each and every moment of our lives. We make a big mistake if we forget to thank him for everything he is doing in our lives, and it will be equally wrong if we stop thanking him or murmur against him for any reason. 
Thanksgiving should be a day-to-day attitude towards God. Whatever we do we have to do it recognizing his goodness in our lives. Any day in which we don’t actively praise the Lord is a waste of time. 
  • · God is good all the time 
The Lord is good, a refuge in times of trouble. He cares for those who trust in him, Nahum 1:7
  • · His compassion is new every day
Because of the LORD's great love we are not consumed, for his compassions never fail. They are new every morning; great is your faithfulness. Lamentations 3:22-23
  • God personally sustains us.
We could never sustain ourselves. I lie down and sleep; I wake again, because the Lord sustains me. Psalm 3:5
  • God deserves our praise as He holds our breath we live and we have our being in him
For in him we live and move and have our being.' As some of your own poets have said, 'We are his offspring.' Acts 17:28
  • We have to use every day every day for He loved and saved us while we were yet sinners and his enemies. he saved us, not because of righteous things we had done, but because of his mercy.
He saved us through the washing of rebirth and renewal by the Holy Spirit, Titus 3:5
  • · God deserves our thank you as he provides our needs each day. 
And my God will meet all your needs according to the riches of his glory in Christ Jesus. Philippians 4:19
  • · The fact we have breath reminds us to praise the Lord.
Let everything that has breath praise the LORD. Praise the LORD. Psalm 150:6
  • · Everyday is a thanksgiving day as God is our light and fortress that we shall not fear anyone or anything.
Of David. The LORD is my light and my salvation-- whom shall I fear? The LORD is the stronghold of my life-- of whom shall I be afraid? Psalm 27:1
  • · We are grateful every day as our gratefulness attitude is the way we acknowledge his goodness. 
What shall I return to the LORD for all his goodness to me? Psalm 116:12
  • · We can’t have any valid reason to be ungrateful.
God isn’t only He loves us he is also loved. He can’t be anything else except love. In whatever way you look at God he is love and nothing else.
 His mouth is sweetness itself; he is altogether lovely. This is my beloved, this is my friend, daughters of Jerusalem. Song of Solomon 5:16
Whoever does not love does not know God, because God is love. 1 John 4:8

#God #Jesus #knowledge #rejoice #trustgod #grace #salvation #church #testimony #rejoice #preaching #Bible #theword #Abiydinsa #scriptures #abiywakumadinsa

Wednesday, November 23, 2016

የአቋም መግለጫ

እኔ እግዚአብሔር ነኝ ስሜ ይህ ነው፤ ክብሬን ለሌላ፥ ምስጋናዬንም ለተቀረጹ ምስሎች አልሰጥም። ኢሳይያስ 42:8
እግዚአብሄር እንዲህ ይላል ክብሬን ለሌላ ምስጋናዬን ለተቀረፁ ምስሎች አልሰጥም፡፡ እግዚአብሄር ፡፡ ምንም ክርክር እንዳይነሳ እኔ እግዚአብሄር ነኝ ስሜም ይህ ነው በማለት በመጀመሪያ ስሙን ግልፅ አደረገልን፡፡
በሁለተኛ ደረጃ ክብሩን ለማንም ለማንም እንደማይሰጥ ተናገረ፡፡ ብዙ የሚያጋራው ነገሮች ቢኖሩም ክብሩን ግን ለማንም አይሰጥም፡፡ ከማንም ሰው ጋር እኩል መቆጠር አይፈልግም፡፡
ማንም የሰው ልጅ የእግዚአብሄርን ክብሩን እንዲሸፍን አይፈቅድም፡፡
የእግዚአብሄርን ክብር መውሰድ የስነመለኮት አመለካከት ብቻ ሳይሆን በሰው ልጅ የእለት ተእለት ህይወት ሊከሰት የሚችል የዘወትር ፈተና ነው፡፡ ሰው ካልተጠነቀቀ የእግዚአብሄን ክብር በመውሰድ እግዚአብሄርን ያስቆጣዋል፡፡ አንዳንደ ሰው እኔ ምን ክብር አለፅ ይላል ነገር ግን ሰዎች አንተን አልፈው እግዚአብሄርን ማየት ካቃታቸው ወድቀሃል፡፡ ለእግዚአብሄር የሚገባውን ትኩረት ራስህ ጋር ካስቀረኸው ክብሩን ወስደሃል፡፡ ሰዎች ወደ አንተ ሲያመለክቱ ወደእግዚአብሄር ካላመለከትክ ክብሩ ጣፍጦሃል ማለት ነው፡፡
ኢየሱስ በምድር ላይ ይመላለስ በነበረ ጊዜ ለእግዚአብሄር የሚገባውን ክብር ወደ እርሱ ሲያመጡ የእግዚአብሄርን ክብር ላለውሰድ ይጠነቀቅ ነበር፡፡
ኢየሱስም፦ ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም። ሉቃስ 18፡19
በበርናባስና በጳውሎስ ታዕምራት በተደረገ ጊዜ ሰዎች ሊያመልኳቸው ሲሞክሩ የእግዚአብሄርን ክብር መውሰድ በጣም ስሱና ሴልሲቲቭ ነገር ስለሆነ ወዲያው ነው ፊት ለፊት የተቃወሙት፡፡ ሰዎች እነርሱን ባከበሩዋቸው መጠን ራሳቸውን አዋረዱ፡፡
ሐዋርያት በርናባስና ጳውሎስ ግን ይህን በሰሙ ጊዜ ልብሳቸውን ቀደው ወደ ሕዝቡ መካከል እየጮኹ ሮጡ፥ ሐዋርያት 14፡14
የሰዎች ትኩረት ከእነርሱ ላይ ተነስቶ ወደ እግዚአብሄር እንዳይሄድ የሚፈልጉ ለእግዚአብሄር መሰጠት ያለበትን ክብር በተለያየ ምክኒያት ለራሳቸው የሚወስዱ ሰዎችን እግዚአብሄር ይናገራል ክብሬን ለሌላ ለማንም አልሰጥም፡፡
ካልተጠነቀቅን ደግሞ እግዚአብሄር ክብሩ እንደማይገባን የሚያሳይበትና የሚያስታውስበት የራሱ መንገድ እንዳለው ከናቡከደነፆር ታሪክ ልንማር ይገባል፡፡ ዳንኤል 5፡19-21
ንጉሱ የተናገረውን ንግግር አድምጠው ሰዎች ለእግዚአብሄር የሚገባውን ክብር ለሰው ሰጡ፡፡ ችግሩ ሰው ክብሩን መስጠቱ አይደለም፡፡ ችግሩ ግን የተሰጠውን ክብር ለእግዚአብሄር መልሶ አለመስጠቱ ነው፡፡ ሰው የእግዚአብሄርን ክብር እንዳይሸፍን ራሱን አለመደበቁ ነው ችግሩ ፡፡
ሕዝቡም፦ የእግዚአብሔር ድምፅ ነው የሰውም አይደለም ብለው ጮኹ። ለእግዚአብሔርም ክብር ስላልሰጠ ያን ጊዜ የጌታ መልአክ መታው በትልም ተበልቶ ሞተ። ሐዋርያት 12፡22-23
የእግዚአብሄርን ክብር መውሰድ እኔን አይመለከተኝም የሚል ሰው የለም፡፡ ፍራ እንጂ የትእቢትን ነገር አታስብ፡፡ ራስህን አዋርድ፡፡ ሁልጊዜ ለእግዚአብሄር አምላክነት እውቅና ስጥ፡፡ በምንም ምክኒያት ይሁን የሰዎች ትኩረት አንተ ጋር እንዳይቀር ተጠንቀቅ፡፡ ሰዎች ክብር ሲሰጡህ በተራህ አንተ ለእግዚአብሄር ክብር ስጥ፡፡
እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት። 1ኛ ቆሮንቶስ 10፡31
ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን። ሮሜ 11፡36
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ክብር #ትእቢት #ኩራት #እግዚአብሄር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ