Popular Posts

Sunday, May 29, 2022

እግዚአብሔር እንዳለ

 

ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ወደ ዕብራውያን 116

ወደ እግዚአብሄር ገብቶ ጉዳይን ለማስፈፀም የመጀመሪያው መመዘኛ እግዚአብሄር እንዳለ ማመን ነው፡፡

እግዚአብሄር እንዳለ ማለት ደግሞ አንድ ሃይል እንዳለ ማመን ማለት ብቻ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር እንዳለ ማለት እግዚአብሄር የሚባል እንዳለ ብቻ ማለት አይደለም፡፡

እግዚአብሄር እንዳለ ማለት እግዚአብሄር የምድር እና የሰማይ ፈጣሪ ፣ ባለቤት እና አስተዳዳሪ እንደሆነ ማመን አለበት፡፡

እግዚአብሄር እንዳለ ማመን ማለት እግዚአብሄር ጀማሪ ወይም ቆርቋሪ እንደሆነ ማመን ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር መሪ ነው፡፡ እግዚአብሄ የማንም ተከታይ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር ለህይወታችን የራሱ ራእይ እና አላማ ያለው የአላማ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር በአላማው መሰረት በትጋት እየሰራ ምድርን እያስተዳደረ እንደሆነ ማመን ይጠይቃል፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር ጋር ያለው ግንኙነት እንዲሰምር እግዚአብሄር በፍቅር በጥበብ እና በሃይል ምድርን እያስተዳደረ መሆኑን ማወቅ አለብን፡፡

ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። የዮሐንስ ወንጌል 1፡3

እግዚአብሄር ጀማሪ ነው፡፡ በምድር ላይ ይሁን በህይወታችሁ ውስጥ የተጀመረ ትርጉም ያለው ነገር ካለ የጀመረው እግዚአብሄር መሆኑን ማመን ይጠይቃል፡፡ አንዳንዱን ነገር እናንተ ብትተዉት እንኳን እግዚአብሄር ግን እንደ ባለቤት ከግቡ ሳያደርስ አይተወውም፡፡

ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ትንቢተ ኤርምያስ 29፡11

እግዚአብሔር ምድርን ፈጥሮ አልተዋትም፡፡ እግዚአብሄር በምድር ላይ ያሉትን ማንኛውንም እንቅስቃሴዎች በትጋት ይከታተላል ይመዝናል ይቆጣጠራል ይመራል፡፡

ከሕዝቡ መኳንንት ጋር ያስቀምጣቸው ዘንድ፥ የክብርንም ዙፋን ያወርሳቸው ዘንድ፥ ችግረኛውን ከመሬት ያስነሣል፥ ምስኪኑንም ከጉድፍ ያስነሣል፤ የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና፥ በእነርሱ ላይም ዓለምን አደረገ። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 2፡8

እግዚአብሔር ፈራጃችን ነው፥ እግዚአብሔር ሕግን ሰጪያችን ነው፥ እግዚአብሔር ንጉሣችን ነው፤ እርሱ ያድነናል። ትንቢተ ኢሳይያስ 33፡22

አትታበዩ፥ በኩራትም አትናገሩ፤ እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፥ እግዚአብሔርም ሥራውን የሚመዝን ነውና፥ ከአፋችሁ የኵራት ነገር አይውጣ። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 2፡3

ኢየሱስ ግን፦ አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል እኔም ደግሞ እሠራለሁ ብሎ መለሰላቸው። የዮሐንስ ወንጌል 5፡17

ይህን በመረዳት ወደ እግዚአብሄር የሚቀርብ ሰው ከእግዚአብሄር ጋር በመልካም ግንኙነት ተጠቃሚ ይሆናል፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

Believe God exists

 


Believe God exists

And without faith, it is impossible to please God because anyone who comes to him must believe that he exists and that he rewards those who earnestly seek him. Hebrews 11:6

To come to God and have our request accepted, we first and for most need to believe on the existence of God.

Believing God exists doesn’t just mean believing that there is a higher power or a god. It means that God is the creator, the owner, the initiator, the sustainer, the judge, and the administrator of all the earth.

God is the creator; He didn’t create the earth and left it to its fate. He is the active sustainer and manager. God is the initiator. If anything meaningful is created on earth or in our individual lives, it is initiated by God Himself.

Through him all things were made; without him, nothing was made that has been made. John 1:3

God is the leader. God isn’t following anyone. He doesn’t need any creativity from any of us, He has his own idea. He has his own purpose for the earth and our individual lives in particular.

He is busy leading the earth by wisdom, power, and love.

For I know the plans I have for you,” declares the Lord, “plans to prosper you and not to harm you, plans to give you hope and a future. Jeremiah 29:11

Even if we leave out some things in our lives, He doesn’t leave it as the owner until He fulfils them.

God is actively following up, evaluating, and judging everything happening on earth and in our lives.

In his defense Jesus said to them, “My Father is always at his work to this very day, and I too am working.” John 5:17

“Do not keep talking so proudly or let your mouth speak such arrogance, for the Lord is a God who knows, and by him, deeds are weighed. 1 Samuel 2:3

He raises the poor from the dust and lifts the needy from the ash heap; he seats them with princes and has them inherit a throne of honor. 1 Samuel 2:8

For the Lord is our judge, the Lord is our lawgiver, the Lord is our king; it is he who will save us. Isaiah 33:22

Anyone who comes to God must believe that God is the creator, owner, judge and administrator of heaven and earth. Even if we sometimes don’t see it visibly, God is busy working on his plan for our lives.

For I know the plans I have for you,” declares the Lord, “plans to prosper you and not to harm you, plans to give you hope and a future. Jeremiah 29:1

God created the earth. God carefully monitors, evaluates, controls, and directs every movement on earth.

A person who draws close to God in this understanding benefits from a good relationship with God.

Abiy Wakuma Dinsa

For more articles https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

For video messages https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#Vision #hiswill #hisleading #hisagenda #Jesus #Lord #Church #success # #inspired #sermon #church #leadership #steward #bible #theword #christ #purpose #Eternal #Word #HolySpirit #Church #Amharic #Sermon #Bible #HolySpirit #Life #Facebook #AbiyWakuma #AbiyWakumaDinsa

Wednesday, May 25, 2022

የዝነኝነት አደጋ


 ለማንም አንዳች እንዳትናገር ተጠንቀቅ፥ ነገር ግን ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ስለ መንጻትህ ሙሴ ያዘዘውን አቅርብ አለው። የማርቆስ ወንጌል 144

ለማንም አትንገሩ ብሎ አዘዛቸው እነርሱ ግን ባዘዛቸውም መጠን ይልቅ እጅግ አወሩት የማርቆስ ወንጌል 736

ወደ ቤቱም ሰደደውና፦ ወደ መንደሩ አትግባ በመንደሩም ለማንም አንዳች አትናገር አለው። የማርቆስ ወንጌል 826

ስለ እርሱም ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው። የማርቆስ ወንጌል  830

ከተራራውም ሲወርዱ የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሣ ድረስ ያዩትን ለማንም እንዳይነግሩ አዘዛቸው። የማርቆስ ወንጌል 99

እርሱም ለማንም እንዳይናገር አዘዘው፥ ነገር ግን፦ ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ፥ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ስለ መንጻትህ ሙሴ እንዳዘዘ መሥዋዕት አቅርብ አለው። የሉቃስ ወንጌል 514

ወላጆችዋም ተገረሙ፤ እርሱ ግን የሆነውን ለማንም እንዳይነግሩ አዘዛቸው። የሉቃስ ወንጌል 856

ኢየሱስ ከፈወሰ እና ድንቅ እና ታእምራት ካደረገ በኋላ ለማንም አትናገሩ ሲል በተከታታይ እናያለን፡፡ ሰዎች የእግዚአብሄርን ድንቅ መናገራቸው መልካም ቢሆንም ነገር ግን ያለጊዜው የሰዎችን ትኩረት መሳብ እና ዝነኛ መሆን በኢየሱስ ላይ የሚያመጣው ጉዳት ስለሚበልጥ ለማንም አትናገሩ ብሎ ድንቅ የተደረገላቸውን ያስጠነቅቅቃአቸው ነበር፡፡

ኢየሱስ የትኩረት እጥረት አልነበረበትም፡፡ የኢየሱስ ትኩረት የእግዚአብሄርን የአባቱን ፈቃድ በምድር ላይ አድርጎ አብን ማክበር ነበር፡፡ በትኩረትም ያለትኩረትም የእግዚአብሄርን ፈቃድ መፈፀም አነደሚቻል ኢየሱስ በአገልግሎቱ አሳትይቶዋል፡፡ የእግዚአብሄርን የልቡን ፈቃድ አድርጎ ለማለፍ የሰውን ትኩረት መሳብ ግዴታ አይደለም፡፡

እነሆ የመረጥሁት ብላቴናዬ፥ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ወዳጄ፤ መንፈሴን በእርሱ ላይ አኖራለሁ፥ ፍርድንም ለአሕዛብ ያወራል።

አይከራከርም አይጮህምም፥ ድምፁንም በአደባባይ የሚሰማ የለም። ማቴዎስ 12፡18-19

የኢየሱስ ትኩረት ብዙ ሰዎችን መሰብሰብ ሳይሆን ወደ እርሱ የመጡትን በታማኝነት እና  በትጋት ማገልገል ነበር፡፡

የኢየሱስ የምድር ላይ አገልግሎት የሚመዘነው በተከተሉት ሰዎች ብዛት እንዳልነበረ ኦየሱስ ጠንቅቆ ያውቅ ስለነበረ ትኩረቱ ወደእርሱ የመጡትን በታማኝነት እና በትጋት ማስተማር እና መፈወስ ነበር፡፡

እንዲያውም ኢየሱስ ይጠነቀቀ የነበረው ካለጊዜው የመጣ ዝና በአገልግሎቱ ላይ አላስፈላጊ ጫና እንዳይፈጥርበት እና ከአገልግሎቱ እንዳያስተጓጉለው ነበር፡፡  

እግዚአብሄር አብ ብዙዎች በኢየሱስ አገልግሎት የሚጠቀሙበት ጊዜው ሲደርስ የኢየሱስ ዝና እስከ ሶርያ ድረስ እንደ ወጣ መፅሃፍ  ቅዱስ ይናገራል፡፡

ያም ዝና ወደዚያ አገር ሁሉ ወጣ። ማቴዎስ 926

ኢየሱስ ከፈወሰ በሁዋላ ለማንም አትናገሩ ቢልም የኢየሱስ ዝና የሚወጣበት ትክክለፃው ጊዜ ሲመጣ ግን ኢየሱስን ዝነፃ እንዳይሆን ምንም ነገር አላገደውም ነበር፡፡

ጊዜ በጊዜው የሚመጣ ርያ ድረስ ወጣ

ዝናውም ወደ ሶርያ ሁሉ ወጣ፤ በልዩ ልዩ ደዌና ሥቃይም ተይዘው የታመሙትን ሁሉ አጋንንትም ያደሩባቸውን በጨረቃም የሚነሣባቸውን ሽባዎችንም ወደ እርሱ አመጡ፥ ፈወሳቸውም። የማቴዎስ ወንጌል 424

ያም ዝና ወደዚያ አገር ሁሉ ወጣ። የማቴዎስ ወንጌል 926

በዚያ ዘመን የአራተኛው ክፍል ገዥ ሄሮድስ የኢየሱስን ዝና ሰማ፥ የማቴዎስ ወንጌል 141

ዝናውም ወዲያው በየስፍራው ወደ ገሊላ ዙሪያ ሁሉ ወጣ።የማርቆስ ወንጌል 128

ኢየሱስም በመንፈስ ኃይል ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ ስለ እርሱም በዙሪያው ባለችው አገር ሁሉ ዝና ወጣ።የሉቃስ ወንጌል 414

ዝናም በዙሪያው ባለች አገር ወደ ስፍራው ሁሉ ስለ እርሱ ወጣ። የሉቃስ ወንጌል 437

ይህም ዝና ስለ እርሱ በይሁዳ ሁሉ በዙሪያውም ባለች አገር ሁሉ ወጣ።የሉቃስ ወንጌል 717

እግዚአብሄር ሞገስን ሲያበዛ ካለምንም ጥረት እና ጭንቀት በጊዜው ስማችንን ያወጣዋል፡፡

እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤ 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 5፡6

የእግዚአብሄር ሞገስ ህዝቡን በጥረት ሳይሆን በመለኮታዊ መንገድ በቀላሉ ይጠራል፡፡

እነሆ፥ የማታውቀውን ሕዝብ ትጠራለህ፥ የእስራኤልም ቅዱስ አክብሮሃልና ስለ አምላክህ ስለ እግዚአብሔር የማያውቁህ ሕዝብ ወደ አንተ ይሮጣሉ። ትንቢተ ኢሳይያስ 55፡5

ጊዜውን የጠበቀ ዝና ሰዎችን ለፈውስ እና ለነፃነት እንደሚሰበስብ ሁሉ ያለጊዜው የሆነ የሰዎችን ትኩረት መፈለግ በአገልጋዩ ላይ ከፍተኛ ጫና በመፍጠር ከአገልግሎት ሊያስተጓጉል ይችላል፡፡

እግዚአብሄር አንዳንዴ ህይወታችንን ቀለል የሚያደርገው እና ለጊዜው የሚደብቀን ከጊዜው በፊት ያለውን የዝነኝነት አላስፈላጊ ሸክም እንዳንሸከም ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ስራ ለመስራት ትኩረትን መሳብ አስፈላጊ አይደለም፡፡

አገልጋይም ዝና ያለውን ጥቅም ብቻ ካየ እና ከዝናው መምጣት ጋር ተያይዞ የሚመጣውን ሃላፊነቱን ካላየ ዝናውን ብቻ ሲያሳድድ እግዚአብሄር ከሰጠው አገልግሎት ይስተጓጎላል፡፡

ከዝና ጋር አብረው የሚመጡ ብዙ አላስፈላጊ ሸክሞች አሉ፡፡ ሰው ራሱ ፈልጎ ዝናውን ካላመጣው እና እግዚአብሄር በራሱ ጊዜ ካመጣው ከዝና ጋር የሚመጡ ሸክሞችን የሚሸከምበት ፀጋን ራሱ እግዚአብሄር ያበዛለታል፡፡

ነገር ግን ሰው ራሱን የሰዎችን ትኩረት ከሳበ ፣ ራሱን ዝነኛ ካደረገ እና በቅልጥፍናው ራሱን አላግባብ ካስተዋወቀ ዝናውን ለማግኘት ብቻ ሳይሆን ዝናውን ለመጠበቅ አላስፈላጊ ዋጋ ይከፍላል፡፡ በተጋነነው ማስታወቂያ የመጡትን ሰዎች ማርካት ችግር ይሆናል፡፡ አላግባብ ትኩረታቸው የተሳበውን ሰዎች ለማስደሰት እግዚአብሄር ከሰጠው የህይወት አላማ ለመውጣት ይፈተናል፡፡ በራሱ ያመጣውን ታዋቂነት  እና ዝና ለማስጠበቅ እግዚአብሄርን ያማከለ ሳይሆን ህዝብን ያማከለ ሰው ይሆናል፡፡ እግዚአብሄር ህዝቡን እንዲያገለግልበት የሰጠውን አቅርቦት ዝናን ለማስጠበቅ ሊያባክነው ይችላል፡፡

በጊዜው እግዚአብሄር ያመጣውን ዝና የሚጠብቅለት ማንም ሰው እስከማያስፈልገው ድረስ ራሱ እግዚአብሄር ይጠብቀዋል፡፡ ሰው በራሱ ያመጣውን ዝነኝነት ራሱ እንዳመጣው በራሱ ወጭ ይጠብቀዋል እንጂ እግዚአብሄር አይጠብቅለትም፡፡

አገልጋዩ የሚያገለግለውን አገልግሎት አያስተዋውቅ ማለት ሳይሆን የራሱን የስጋ ክንድ በመጨመር ትከረቱ ማስተዋወቁ ላይ አይሁን ነው፡፡ የአገልጋይ ትኩረት መሆን ያለበት እግዚአብሄር የላከለትን ሰዎች በታማኝነት ማገልገል ላይ መሆን አለበት፡፡

በምንም ነገር ላይ ማስተዋወቅ ያለብን ጌታን እንጂ ራሳችንን መሆን የለበትም፡፡ መታወቅም ካለብን ጌታን በማስተዋወቅ እንጂ ራሳችንን ብቻ በማስተዋወቅ መሆን የለበትም፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ መጣጥፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

#ራዕይ #የቅንጦት #አስፈላጊነቱ #ፈቃዱ #መምራቱ #አጀንዳው #ኢየሱስ #ጌታ #ቤተ ክርስቲያን #ስኬት # #ተመስጦ #ስብከት #ትኩረት #ዝና #ማስታወቅ 

Monday, May 23, 2022

Only the Contented Can Serve God

 

 Only the Contented Can Serve God

Our want is limitless. You wish to have something and as soon as you get it, it loses its honor. By the time you get it, you have already started wishing for something different. And as soon as you get the higher one, it loses its glory. You wish to have something more and as soon you get it, it becomes less in your sight.

This is the vicious cycle of life. It must be stopped as soon as possible. You can’t serve God if you fall into this cycle.

Don’t get me wrong, I am not against better and more. I am against the attitude toward the "better and more". We have an overestimation for "better and more". And when better and more arrive they disappoint us as it can’t deliver our expectation. "Better and more" are limited. There is something "better and more" can’t provide. We are expecting too much from a youth.

The other question is that "What you are doing with what you already have?” Are you just following "better and more" just for the sake of getting "better and more"? Or do you have a purpose of reaching out to others and serving them with whatever you have?

But If you always look for "better and more" just for the sake of getting "better and more" you will do nothing when you get it and waste your life. You don’t enjoy "the better and more when you get it. You despise it the sooner you get it, as the motive to look for "better and more" was distorted in the first place.

But if you are grateful for what you have, you can reach out to others and can serve them with whatever you have.  

Then the apostles said to the Lord, “Give us more faith.” The Lord said, “If you have faith the size of a mustard seed, you could say to this mulberry tree, ‘Pull yourself up by the roots, and plant yourself in the sea!’ and it would obey you. Luke 17:5-6

 

Most of our problems don’t come for lack of better and more things. Most of our problems come from not using what we already have. We wait for better and more while we have everything, need to do something about it.

If we understand that it isn’t always a matter of "better and more" our prayer life would have changed.

Abiy Wakuma Dinsa 

For More Articles https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

#Vision  #luxury #necessity   #hiswill #hisleading #hisagenda #Jesus #Lord #Church #success # #inspired #sermon #church #leadership #steward #bible #theword #christ #purpose #contented


እግዚአብሄርን ማገልገል የሚችለው ባለው ነገር የሚረካ ሰው ብቻ ነው


 እግዚአብሄርን ማገልገል የሚችለው ባለው ነገር የሚረካ ሰው ብቻ ነው

በህይወት የምንፈልገው ገደብ የለሽ ነው። የሆነ ነገር እንዲኖርህ ትመኛለህ እና ልክ ስታገኘው በፊትህ ክብሩን ያጣል። አንድን የተሻለን ነገር የሚፈልጉ ሰዎች ባገኙት ጊዜ የተለየ ነገር መፈለግ ይጀምራሉ፡፡ እና ከፍተኛውን ነገር ላይ እንደደረሱ ነገሩ የበፊት ክብሩን ያጣል፡፡ አሁንም የተሻለ እና የበለጠ ነገር እንዲኖራቸው ይመኛሉ እና አሁንም ልክ እንዳገኙት ያንስባቸዋል።

ይህ በተቻለ ፍጥነት መውጣት መላቀቅ ያለብን የሕይወት ክፉ አዙሪት ነው። በዚህ ዑደት ውስጥ ከወደቁ እግዚአብሔርን ማገልገል አይቻልም።

አትሳሳቱ እኔ የተሻለ እና የበለጠ አልቃወምም፡፡ እኔ ጥያቄዬ "የተሻለ እና የበለጠ" ለመፈለግ ያነሳሳን መነሻ የልብ ሃሳብ /motive/ ላይ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ  "ለተሻለ እና ለበለጠ" ያለን ግምት የተሳሳተ ነው። የተሻለ እና የበለጠ" አቅሙ የተገደበ ነው፡፡ "የተሻለ እና የበለጠ" የማይሰጠን በጣም ብዙ ነገር አለ። "የተሻለ እና የበለጠ" ሲገኝ እኛ የምንጠብቀውን ነገር ሊሰጠን ስለማይችል ያሳዝነናል። "የተሻለ እና የበለጠ" ከአለአቅሙ በላይ ብዙ ነገር እንጠብቅበታለን።

ሌላው ጥያቄ "ባለን ነገር ምን እየሰራን ነው?" የሚል ጥያቄ ነው፡፡ "የተሻለ እና የበለጠ" ን ነገር የምንከተለው እንዲያው "የተሻለ እና የበለጠ" ነገር ለመከተል ያህል ብቻ ነው ወይስ "በተሻለ እና በበለጠ" ነገር ሌሎችን በመድረስና እና ባለን ነገር ሌሎችን በማገልገል አላማ ነው?

ባለን ካልረካን እና ባለን ካልተጠቀምን ሁል ጊዜ "የተሻለ እና የበለጠ" የምንፈልግ ከሆነ "የተሻለ እና የበለጠ" ለማግኘት ስንል ምንም ሳናደርግ ህይወታችንን በከንቱ እናባክነዋለን። በተሳሳተ መልኩ "የተሻለ እና የበለጠን" ነገር የሚፈልጉ ሰዎች ሲያገኙትም አይደሰቱበትም፡፡ ሲያገኙት ወዲያው ይንቁታል፡፡ ምክንያቱም በመጀመሪያ ደረጃ  "የተሻለ እና የበለጠ" የመፈለግ ተነሳሽነታቸው /motive/ የተዛባ ነው።

ስላላችሁ ነገር አመስጋኝ ከሆናችሁ እና ከረካችሁ ከራሳችሁ ህይወት አልፋችሁ ሌሎችን መድረስ እና ማገልገል ትችላላችሁ።

ሐዋርያትም ጌታን፦ እምነት ጨምርልን አሉት። 

ጌታም አለ፦ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ሾላ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተተከል ብትሉት፥ ይታዘዝላችሁ ነበር። ሉቃስ 17፡5-6

አብዛኛዎቹ ችግሮቻችን "የተሻሉ እና የበለጡ" ነገሮች ከማጣት አይመጡም። አብዛኛው ችግሮቻችን የሚመነጩት ያለንን ነገር ካለመጠቀም ነው። ትርጉም ያለው ነገር ለማድረግ የሚያስችለን ነገር ሁሉ እያለን አሁንም "የተሻለ እና የበለጠ" ነገር እንጠብቃለን፡፡ ባለን ነገር አንድ ነገር ለማድረግ ዛሬ መወሰን አለብን፡፡

ሁልጊዜ ልዩነት የሚያመጣው “የተሻለ እና የበለጠ” ጉዳይ እንዳልሆነ ብንረዳ የጸሎት ሕይወታችን ይለወጥ ነበር።

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa 

ለተጨማሪ መጣጥፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

#ራዕይ #የቅንጦት #አስፈላጊነቱ #ፈቃዱ #መምራቱ #አጀንዳው #ኢየሱስ #ጌታ #ቤተ ክርስቲያን #ስኬት # #ተመስጦ #ስብከት #እናማጥናለን

Sunday, May 22, 2022

ቅንጦት በጣም ውድ ነው

 


ቅንጦት በጣም ውድ ነው።
ቅንጦት በጣም ውድ ነው የሚለውን ስታይ እና ታዲያ ቅንጦት ርካሽ አይደለም ልትል ትችላለህ፡፡ ቅንጦት ስል ውድ ነገሮችን ማለቴ አይደለም፡፡ ቅንጦት ስል ከሚያስፈልጉን ነገሮች ውጭ ያሉ ነገር ግን እኛ የምንፈልጋቸው ነገሮች ማለቴ ነው፡፡ 
ጥራት ያላቸው ነገሮች ጥራት ከሚያንሳቸው ነገሮች በበለጠ ዋጋ እንደሚገዙ አውቃለሁ፡፡ የቅንጦትን ነገር ሳነሳ ለህይወት አላማችን በእርግጥ የማያስፈልጉን እኛ ግን የምንፈልጋቸውን ነገሮች ማንሳቴ ነው።
እግዚአብሔር አባታችን ነው። እርሱ ያለማቋረጥ የሚያስፈልገንን ነገር ያዘጋጅልናል። ያ ማለት ግን እኛ የምንፈልገውን ሁሉ ያቀርባል ማለት አይደለም። እግዚአብሄር ፍላጎትህን እንደሚያሟላ የተረጋገጠ ነገር ነው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር የምትፈልገውን ነገር ሁሉ እንደሚሰጥህ ዋስትና የሚሰጥ የመፅሃፍ ቅዱስ ቃል የለም። ይልቁንም ቅዱሳት መጻህፍት የሚናገሩት የቅንጦት ኑሮን የሚፈልጉ ሰዎችን ፀሎት እግዚአብሄር እንደማይሰማ ነው፡፡ 
በእናንተ ዘንድ ጦርና ጠብ ከወዴት ይመጣሉ? በብልቶቻችሁ ውስጥ ከሚዋጉ ከእነዚህ ከምቾቶቻችሁ አይደሉምን? ትመኛላችሁ ለእናንተም አይሆንም፤ ትገድላላችሁ በብርቱም ትፈልጋላችሁ፥ ልታገኙም አትችሉም፤ ትጣላላችሁ ትዋጉማላችሁ ነገር ግን አትለምኑምና ለእናንተ አይሆንም፤ ትለምናላችሁ፥ በምቾቶቻችሁም ትከፍሉ ዘንድ በክፉ ትለምናላችሁና አትቀበሉም። የያዕቆብ መልእክት 4፡1-3
በህይወታችን ለሚያስፈልገን ነገር ሁሉ የእግዚአብሄር ፀጋ በቂ ነው፡፡ 
ሰዎች በቅንጦት መኖር ሲፈልጉ እግዚአብሔር ለአላማው ያዘጋጀላቸውን አቅርቦት እግዚአብሔር ላላሰበው ነገር አላግባብ ይጠቀሙበታል። የእግዚአብሔርን አቅርቦት አላግባብ ስናባክን ሌላውን የሕይወታችንን ክፍል እንጎዳዋለን።
እግዚአብሔር በሕይወታችን ያለውን ዓላማ ለመፈጸም የሚያስፈልገንን ሁሉ እንደሚሰጠን ቃል ገብቷል። እግዚአብሄር የሚያቀርበው አቅርቦት ሁሉ ከህይወት ዓላማችን ጋር የተቆራኘ ነው።  "ይህ ነገር ተልእኮዬን ለመፈፀም አስፈላጊ ነው ወይ?" የሚለው ጥያቄ በሕይወታችን ውስጥ ፍላጎትን እና ቅንጦትን ለመለየት ወሳኝ መመዘኛ ነው፡፡ በድፍረት ለአላማዬ መሳካት ግዴታ ያስፈልገኛል ማለት ካልቻልን በስተቀር የምንፈልገው ነገር ቅንጦት እንጂ አስፈላጊ ላይሆን ይችላል። የቅንጦት ፍላጎት ተገቢ ካልሆነ ፉክክር ፣ ከራስ ወዳድነት እና ከስግብግብነት ይመነጫል። ከእኛ ጋር ተመሳሳይ የህይወት ዓላማ ከሌላቸው ከሌሎች ሰዎች ጋር እንድንወዳደር እና እንድንፎካከር አልተጠራንም። በሕይወታችን ውስጥ ልዩ የሆነ የእግዚአብሄር ዓላማ አለ።
የእግዚአብሔር አቅርቦት በሕይወታችን ውስጥ ባለው ልዩ ዓላማ የተገደበ ነው። የእግዚአብሄር አቅርቦት በህይወታችን ላለው አላማ አያንስም አይበዛም፡፡ እግዚአብሄር ያዘጋጀልንን አቅርቦት እግዚአብሔር ላልጠራን ነገር ስናውል እግዚአብሔር የሰጠንን አቅርቦት እናባክናለን። ከዓላማችን ውጪ ለሆነ ነገር የምናጠፋው ነገር ሁሉ የምናባክነው ለዓላማችን ከተሰጠን አቅርቦት ላይ ነው።
የቅንጦት ህይወት እንዲኖረን ከፈለግን ከሰዎች ጋር ጦር እና ጠብ ውስጥ እንገባለን፡፡ እግዚአብሄር ለቅንጦት አቅርቦትን ስለማያዘጋጅ የቅንጦት ፍላጎታችንን ለማሟላት ጠብ ውስጥ በመግባት እግዚአብሄር የሰጠንን እጅግ የከበረውን የህይወት አላማ እናባክነዋለን፡፡ 
ቅንጦትን መፈለግ ሰው በራሱ ዝነኛ ለመሆን ከመፈለግ ይመጣል። እራሳችንን ዝነኛ ካደረግን ዝናችንን ጠብቆ ማቆየት ከባድ ሸክም ይሆንብናል፡፡ እኛ ራሳችን ዝነኛ ለማድረግ ምንም የምናደርገው ነገር ከሌለ ጊዜውን ጠብቆ በተፈጥሮአዊ መንገድ እስከመጣ ድረስ ዝነኛ መሆን ምንም ስህተት የለበትም፡፡ ራስን ዝነኛ ለማድረግ የሚከፈለው እና ዝነኝነቱን ለመጠበቅ የሚከፈለው ዋጋ በጣም ከፍተኛ ብቻ ሳይሆን ሊከፍሉት የማይችሉት ውድ ዋጋን የሚያስከፈል ነገር ነው፡፡
ትርፍ ነገር ስለሌለ ዝናን የምትከተለው የእግዚአብሔር ዓላማ ለመኖር ከተሰጠህ ጊዜ ጉልበት እና እውቀት ላይ ቀንሰህ ነው። በመሠረቱ ዝናን መከተል  በእግዚአብሔር የተሰጠ አይደለም። ዝናን የምትከተል ከሆነ ዝናን የምትከተለው ራስህ ነህ እንጂ እግዚአብሔር የለበትም። ከሌሎች ጋር ከተወዳደርክ እና ከተፎካከርክ እግዚአብሔር ውድድሩን ስፖንሰር አያደርግም፡፡ 
ቅንጦቶቻችንን መፈለግ ካልተውን እና በሚያስፈልገን ነገር ላይ ካልረካን ሌሎችን መድረስ እና እነሱን ማገልገል አንችልም።
በሆንከው ነገር ካልረካህ በምታገኘው ነገር አትረካም።
ለተጨማሪ መጣጥፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/
#ራዕይ #የቅንጦት #አስፈላጊነቱ #ፈቃዱ #መምራቱ #አጀንዳው #ኢየሱስ #ጌታ #ቤተ ክርስቲያን #ስኬት # #ተመስጦ #ስብከት

Sunday, May 8, 2022

Let's all be Mothers

 Mothers are mostly known for their compassion, love, and forgiveness. Let’s be compassionate to others. Let’s accept others as they are. Let’s not judge others with an evil heart. Let’s not judge others from a place of strength. Let’s not judge others, look them down.


Let’s also be loving. Let’s think good, speak good, and do good to others. Let’s share goodness with others.

Let’s also forgive. Let’s understand others. People don’t wrong as if they really understand what they are doing. Even if we think they do, let’s leave it to God who knows our hearts. Our responsibility is to forgive. Don’t hold anything against them. Let them live. Release them and live your life.

Motherhood is a spirit we all practice in little or much. Let’s all be mothers.

በአብዛኛው እናቶች የሚታወቁት በርህራሄ፣ በፍቅር እና በይቅርታ ነው። እኛም ዛሬ ይህንን የእናትነት ፍቅር በመያዝ ለሌሎች ርህሩህ እንሁን። ሌሎችን እንዳሉ እንቀበላቸው። በሌሎች ላይ በክፉ ልብ አንፍረድ። በራሳችን ጥንካሬ ተመክተን በሌሎች ላይ አንፍረድ። ሌሎችን ዝቅ አድርገን በመመለከት ሌሎች ላይ አንፍረድ።

የፍቅር ሰዎች እንሁን። ለሌሎች መልካም እናስብ መልካም እንናገር መልካም እናድርግ። የተፈጠርነው ለሌሎች ነውና መልካምነትን ለሌሎች እናካፍል።

እንዲሁም ይቅር እንበል። ሌሎችን እንረዳቸው። ሰዎች የሚያደርጉትን በትክክል ከተረዱት ሌላውን ሰው አይበድሉም። አውቀው እንደበደሉን ብናያስብም እንኳን ልባችንን ለሚያውቅ አምላክ እንተወው። የእኛ ኃላፊነት ይቅር ማለት ብቻ ነው:: በበደሉን ላይ ምንም ነገር አንያዝ:: እንፍታቸው እንልቀቸው ይኑሩ። እንፍታቸው በህይወት ይኑሩ።

እናትነት ሁላችንም በጥቂቱም ሆነ በብዙ የምንለማመደው መንፈስ ነው። ሁላችንም እናቶች እንሁን::