Popular Posts

Sunday, November 22, 2020

ከእውነት_ጋር_እቆማለሁ!

 

ሰሞኑን የኢትዮጲያ መንግስት ሰራዊት ጁንታ ከሚለው ከትግራይ ክልላዊ መንግስት ሰራዊት ጋር ወደ ጦርነት ውስጥ ገብቷል፡፡ ሁለቱም እነርሱ ትክክል እንደሆኑና ሌላው ወገን ስህተት እንደሆነ ሲናገሩ እንሰማለን፡፡

እኔም በዚህ ረገድ የራሴ አስተያየት ቢኖረኝም የራሴ አስተያየት ሙሉ ለሙሉ ትክክል ላይሆን ስለሚችል ላለመፃፍ ወስኛለሁ፡፡ አብዛኛው ሰው አንዱን በስሜት በሚደግፍበት ጊዜ የራሴ አስተያየት መፃፍ ለሚወዱኝና ለሚያከብሩኝ አንባቢዎቼ እንቅፋት ስለሚሆን እንዲሁም ደግሞ የእኔ የግል አስተያየቴ ምንም ስለማይጠቅም ትቼዋለሁ፡፡

ነገር ግን ከእግዚአብሄር ቃል እንፃር ግን የተረዳሁትን ለመፃፍ ልቤ ወደደ፡፡

እንደ ዜጋ የመንግስት መሪዎችን መታዘዝ ትክክል ነው፡፡ ግልፅ የሆነ የእግዚአብሄር ቃልንና ህሊናን የጣሰ ግልፅ ስህተት የሆነ ነገር አይዘዙት እንጂ ሰው የመንግስት መሪዎቹን በመታዘዙ አይሳሳትም፡፡

ሰው ከግል ጥላቻ ተጠብቆ መንግስትን ሰምቶ ወታደርነት ቢሄድና አገርንና ህዝብን ቢጠብቅ ምንም ስህተት የለበትም፡፡  ወንድምም ቢሆን እንኳን ሊገድለን የመጣን ሰው እንደ ግለሰብም እንደ ሃገርም መከላከል ተፈጥሮአዊ ነው፡፡

ሰው ግን በጥላቻ እና በንቀት ተነሳስቶ ስለሚያደርገው ነገር ሁሉ ተጠያቂ ነው አንድ ቀን በእግዚአብሄር ፊት መልስም ይሰጥበታል፡፡   

መልካም ሰው ከልቡ መልካም መዝገብ መልካም ነገርን ያወጣል፥ ክፉ ሰውም ከክፉ መዝገብ
ክፉ ነገርን ያወጣል። እኔ እላችኋለሁ፥ ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል፤ የማቴዎስ ወንጌል 12፡35-36

ሁሉም ወገን እግዚአብሄር ከእርሱ ጎን ያለ ይመስለዋል ወይም ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር የሰውን ፊት አይቶ አያዳላም፡፡ እግዚአብሄር የሚቆመው እውነትን ከያዘው ሰው ጋር ነው፡፡

እንዲህም ሆነ፤ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ዓይኑን አንሥቶ ተመለከተ፥ እነሆም፥ የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ ሰው በፊቱ ቆሞ ነበር፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ፦ ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህን? አለው። እርሱም፦ አይደለሁም፤ እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቼአለሁ አለ። መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 5፡13-14

አሳየዋለሁ ብሎ በትእቢት ከሚነሳ መንግስትም ሆነ ግለሰብም ጋር እግዚአብሄር አይቆምም፡፡ እግዚአብሄር በጥላቻ ተነስቶ ሰውን ለማጥፋት ከሚንቀሳቀስ ግለሰብም ይሁን ቡድንም ጋር አይወግንም፡፡

እግዚአብሄር ከእውነት ጋር ይቆማል፡፡ ሰው ከእውነት በተቃራኒ ራሱን እንዳያገኝና እንዳይጨፈለቅ የሚያዋጣው ከእውነት ጋር መወገን ብቻ ነው፡፡ ተቃራኒዎቼ እውነት ይኖራቸው ይሆን? ብሎ መፍራት ጉዳዩን ከሌላው ወገን ለማየት እና በጭፍን ከመፍረድ ያድናል፡፡

አሁንም እላችኋለሁ፦ ከእነዚህ ሰዎች ተለዩ ተዉአቸውም፤ ይህ አሳብ ወይም ይህ ሥራ ከሰው እንደ ሆነ ይጠፋልና፤ ከእግዚአብሔር እንደ ሆነ ግን ታጠፉአቸው ዘንድ አይቻላችሁም፥ በእርግጥ ከእግዚአብሔር ጋር ስትጣሉ ምናልባት እንዳትገኙ። የሐዋርያት ሥራ 5፡38-39

ማንኛውም ገንዘብ ያለው ሰው ፣ ሃያል የሆነ ሰው እንዲሁም ጠቢብ የሆነ ሰው ቢሆን በእውነት ላይ ግን ተነስቶ ሊበረክት አይችልም፡፡ የትኛውም ሰው ከእውነት ጋር ሊወግን እንጂ እውነትን ሊለውጥ አይችልም፡፡    

ለእውነት እንጂ በእውነት ላይ ምንም ለማድረግ አንችልምና። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡8

በአለም ታሪክ እግዚአብሄር በግለሰብ ህይወት ውስጥ ብቻ ሳይሆን በሃገር ጉዳይ ላይ ጣልቃ ይገባል፡፡ እግዚአብሄር ህዝቡን ስለሚወድ አለምን በፍቅር በሃይልና በጥበብ ያስተዳደራል፡፡ እግዚአብሄር በማይፈራው በትእቢተኛ ግለሰብ ላይ ብቻ ሳይሆን በትእቢተኛ ሀገር እና መንግስት ላይ ይነሳል፡፡ እግዚአብሄር በማን አለብኝነት ክፋት በሚሰራ ግለሰብ ላይ ብቻ ሳይሆን  በትእቢተኛን መንግስት ላይ ይፈርዳል፡፡ እግዚአብሄር ትእቢተኛን ግለሰብ ብቻ ሳይሆን ከተማንና አገርን ያዋርዳል፡፡

አቤቱ፥ ተነሥ፥ በምድር ላይ ፍርድ፥ አንተ አሕዛብን ሁሉ ትወርሳለህና። መዝሙረ ዳዊት 82፡8

እግዚአብሄርን ፈርቶ ክፋት ላለማድረግ በመጠንቀቁ እንጂ ንጉስ በሰራዊቱ ብዛት አይድንም፡፡ ሰው በሃይሉ ብዛት ቢታመን እግዚአብሄርን ያሳዝናል እንጂ አያስደስትም፡፡

ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም፥ ኃያልም በኃይሉ ብዛት አያመልጥም። ፈረስም ከንቱ ነው፥ አያድንም፤ በኃይሉም ብዛት አያመልጥም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደሚፈሩት ናቸው፥ በምሕረቱም ወደሚታመኑ፥ መዝሙረ ዳዊት 33፡16-18

አሸናፊው ማነ ነው ብትሉኝ ትሁት የሆነ እውነት ከእርሱ ጋር ያለችው እግዚአብሄርን የሚፈራ ቡድን አሸናፊ ነው፡፡ ተሸናፊው ማነው ብትሉኝ ትእቡተኛው በሃይሉ የሚተማመነው ይሸነፋል፡፡

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው፦ ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ትንቢተ ኤርምያስ 9፡23-24

ከጥላቻና ከንቀት ተጠቃሚው ሰይጣን ብቻ ነው፡፡ ፀሎታችን መሆን ያለበት እግዚአብሄር በየደረጃው ላሉት መሪዎቻችን ጥበብን እንዲሰጣቸው ራሳቸውን ትሁት እንዲያደርጉና እግዚአብሄር እንዲፈሩ ነው፡፡  

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa .37/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የመንፈስፍሬ #ፍቅር #ሰላም #እውነት #ዘር #ባህሪ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ትህትና #መፅሃፍቅዱስ #የእግዚአብሄርህይወት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #በጎነት #የዋሃት #ራስንመግዛት #ትግስት #መሪ

Wednesday, November 18, 2020

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው፦ ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ትንቢተ ኤርምያስ 9.23-24

 

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥  ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው፦ ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ትንቢተ ኤርምያስ 9.23-24


Sunday, November 15, 2020

መጽሐፈ ምሳሌ 31፡10-31 10 ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል። 11 የባልዋ ልብ ይታመንባታል፥ ምርኮም አይጐድልበትም። 12 ዕድሜዋን ሙሉ መልካም ታደርግለታለች፥ ክፉም አታደርግም። 13 የበግ ጠጕርና የተልባ እግር ትፈልጋለች፥ በእጆችዋም ደስ ብሎአት ትሠራለች። 14 እርስዋ እንደ ነጋዴ መርከብ ናት፤ ከሩቅ አገር ምግብዋን ትሰበስባለች። 15 ገና ሌሊት ሳለ ትነሣለች ለቤትዋም ሰዎች ምግባቸውን፥ ለገረዶችዋም ተግባራቸውን ትሰጣለች። 16 እርሻንም ተመልክታ ትገዛለች፤ ከእጅዋም ፍሬ ወይን ትተክላለች። 17 ወገብዋን በኃይል ትታጠቃለች፥ ክንድዋንም ታበረታለች። 18 ንግድዋ መልካም እንደ ሆነ ትመለከታለች፤ መብራትዋ በሌሊት አይጠፋም። 19 እጅዋን ወደ አመልማሎ ትዘረጋለች፥ ጣቶችዋም እንዝርትን ይይዛሉ። 20 እጅዋን ወደ ድሀ ትዘረጋለች፥ ወደ ችግረኛም እጅዋን ትሰድዳለች። 21 ለቤትዋ ሰዎች ከበረዶ ብርድ የተነሣ አትፈራም፥ የቤትዋ ሰዎች ሁሉ እጥፍ ድርብ የለበሱ ናቸውና። 22 ለራስዋም ግብረ መርፌ ስጋጃ ትሠራለች፤ ጥሩ በፍታና ቀይ ግምጃ ትለብሳለች። 23 ባልዋ በአገር ሽማግሌዎች መካከል በሸንጎ በተቀመጠ ጊዜ በበር የታወቀ ይሆናል። 24 የበፍታ ቀሚስ እየሠራች ትሸጣለች፥ ለነጋዴም ድግ ትሸጣለች። 25 ብርታትና ከበሬታ ልብስዋ ነው፤ በኋላም ዘመን ላይ ትስቃለች። 26 አፍዋን በጥበብ ትከፍታለች፤ የርኅራኄም ሕግ በምላስዋ አለ። 27 የቤትዋንም ሰዎች አካሄድ በደኅና ትመለከታለች፥ የሀኬትንም እንጀራ አትበላም። 28 ልጆችዋ ይነሣሉ፥ ምስጋናዋንም ይናገራሉ፤ ባልዋ ደግሞ እንዲህ ብሎ ያመሰግናታል፦ 29 መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ፥ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ። 30 ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች። 31 ከእጅዋ ፍሬ ስጡአት፥ ሥራዎችዋም በሸንጎ ያመስግኑአት።

 

መጽሐፈ ምሳሌ 3110-31

10 ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል።

11 የባልዋ ልብ ይታመንባታል፥ ምርኮም አይጐድልበትም።

12 ዕድሜዋን ሙሉ መልካም ታደርግለታለች፥ ክፉም አታደርግም።

13 የበግ ጠጕርና የተልባ እግር ትፈልጋለች፥ በእጆችዋም ደስ ብሎአት ትሠራለች።

14 እርስዋ እንደ ነጋዴ መርከብ ናት፤ ከሩቅ አገር ምግብዋን ትሰበስባለች።

15 ገና ሌሊት ሳለ ትነሣለች ለቤትዋም ሰዎች ምግባቸውን፥ ለገረዶችዋም ተግባራቸውን ትሰጣለች።

16 እርሻንም ተመልክታ ትገዛለች፤ ከእጅዋም ፍሬ ወይን ትተክላለች።

17 ወገብዋን በኃይል ትታጠቃለች፥ ክንድዋንም ታበረታለች።

18 ንግድዋ መልካም እንደ ሆነ ትመለከታለች፤ መብራትዋ በሌሊት አይጠፋም።

19 እጅዋን ወደ አመልማሎ ትዘረጋለች፥ ጣቶችዋም እንዝርትን ይይዛሉ።

20 እጅዋን ወደ ድሀ ትዘረጋለች፥ ወደ ችግረኛም እጅዋን ትሰድዳለች።

21 ለቤትዋ ሰዎች ከበረዶ ብርድ የተነሣ አትፈራም፥ የቤትዋ ሰዎች ሁሉ እጥፍ ድርብ የለበሱ ናቸውና።

22 ለራስዋም ግብረ መርፌ ስጋጃ ትሠራለች፤ ጥሩ በፍታና ቀይ ግምጃ ትለብሳለች።

23 ባልዋ በአገር ሽማግሌዎች መካከል በሸንጎ በተቀመጠ ጊዜ በበር የታወቀ ይሆናል።

24 የበፍታ ቀሚስ እየሠራች ትሸጣለች፥ ለነጋዴም ድግ ትሸጣለች።

25 ብርታትና ከበሬታ ልብስዋ ነው፤ በኋላም ዘመን ላይ ትስቃለች።

26 አፍዋን በጥበብ ትከፍታለች፤ የርኅራኄም ሕግ በምላስዋ አለ።

27 የቤትዋንም ሰዎች አካሄድ በደኅና ትመለከታለች፥ የሀኬትንም እንጀራ አትበላም።

28 ልጆችዋ ይነሣሉ፥ ምስጋናዋንም ይናገራሉ፤ ባልዋ ደግሞ እንዲህ ብሎ ያመሰግናታል፦

29 መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ፥ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ።

30 ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች።

31 ከእጅዋ ፍሬ ስጡአት፥ ሥራዎችዋም በሸንጎ ያመስግኑአት።