Popular Posts

Friday, November 16, 2018

የኢዮብ የታላቅነት ሚስጥር


መፅሃፍ ቅዱስ ስለ ኢዮብ ሲናገር ፍፁም ቅን እግዚአብሄርን የሚፈራ ከክፋትም የራቀ ሰው ነበር በማለት ስለኢዮብ ይመሰክራል፡፡ ኢዮብ በምስራቅ ካሉ ሰዎች ይልቅ ታላቅ የነበረበትን ምክኒያት በእግዚአብሄር ፊት የኖረውን ኑሮ በጥቂቱ እንመለክት፡፡  
ዖፅ በሚባል አገር ስሙ ኢዮብ የተባለ አንድ ሰው ነበረ፤ ያም ሰው ፍጹምና ቅን፥ እግዚአብሔርንም የሚፈራ፥ ከክፋትም የራቀ ነበረ። ያም ሰው በምሥራቅ ካሉ ሰዎች ሁሉ ይልቅ ታላቅ ነበረ። መጽሐፈ ኢዮብ 1፡1፣3
መጽሐፈ ኢዮብ 29፡11-17
·         ኢዮብን ያወቁ ሰዎች ሁሉ ስለደግነቱ ይመሰክሩ ነበር፡፡
ቁጥር 11 የሰማችኝ ጆሮ አሞገሰችኝ፥ ያየችኝም ዓይን መሰከረችልኝ፤
·         ችግረኛንና ደሃ አደጉን ይረዳ ነበር፡፡
·         ቁጥር 12 የሚጮኸውን ችግረኛ፥ ድሀ አደጉንና ረጂ የሌለውን አድኜ ነበርሁና።
·         የሰዎችን ችግር በመፍታት ደስ የሚያሰኛቸው ሰው ነበር፡፡
ቁጥር 13 ለጥፋት የቀረበው በረከት በላዬ መጣ፤ የባልቴቲቱንም ልብ እልል አሰኘሁ።
·         ትክክለኛን ፍርድ በመፍረድ እለት በእለት ለእውነት የሚቆም በእውነተኝነቱ የሚታወቅ ሰው ነበር
ቁጥር 14 ጽድቅን ለበስሁ እርስዋም ለበሰችኝ፤ ፍርዴም እንደ መጐናጸፊያና እንደ ኵፋር ነበረ።
ቁጥር 15 ለዕውር ዓይን፥ ለአንካሳ እግር ነበርሁ።
·         በእውቅና በአድልዎ ሳይሆን በእውነት የሚፈርድ ሰው ነበር
ቁጥር 16 ለድሀው አባት ነበርሁ፤ የማላውቀውንም ሰው ሙግት መረመርሁ።
·         በፍርሃት የማያመቻምች ክፉን ፊት ለፊት የሚጋፈጥ ሰው ነበር፡፡
ቁጥር 17 የኃጢአተኛውን መንጋጋ ሰበርሁ፥ የነጠቀውንም ከጥርሱ ውስጥ አስጣልሁ።

መጽሐፈ ኢዮብ 29፡5-34

·         ህይወቱን ከሃሰት ይጠብቅ ነበር
ቁጥር 5-6 በእውነተኛ ሚዛን ልመዘን፥ እግዚአብሔርም ቅንነቴን ይወቅ። በሐሰት ሄጄ እንደ ሆነ እግሬም ለሽንገላ ቸኵላ እንደ ሆነ፥
·         ነውርን ይንቅ ነበር
ቁጥር 7 እርምጃዬ ከመንገድ ፈቀቅ ብሎ፥ ልቤም ዓይኔን ተከትሎ፥ ነውርም ከእጄ ጋር ተጣብቆ እንደ ሆነ፥
·         ህይወቱን ከመጆምጀት በትጋት ይጠብቅ ነበር
ቁጥር 9 ልቤ ወደ ሌላይቱ ሴት ጐምጅቶ እንደ ሆነ፥ በባልንጀራዬም ደጅ አድብቼ እንደ ሆነ፥
·         ለሰዎች ሁሉ ታላቅ አክብሮት ነበረው
ቁጥር 13 ወንድ ባሪያዬ ወይም ሴት ባሪያዬ ከእኔ ጋር በተምዋገቱ ጊዜ፥ ሙግታቸውን ንቄ እንደ ሆነ፥
·         ድሃን መርዳት ሃላፊነት እንደራሱ ሃላፊነት ይወስድ ነበር
ቁጥር 16 ድሀውን ከልመናው ከልክዬ፥ የመበለቲቱን ዓይን አጨልሜ እንደ ሆነ፥
·         ስለደሃ አለመብላት ሃላፊነት ይወሰድ ነበር
ቁጥር 17 እንጀራዬን ለብቻዬ በልቼ እንደ ሆነ፥ ድሀ አደጉም ደግሞ ከእርሱ ሳይበላ ቀርቶ እንደ ሆነ፤
·         ለብዙዎች ላልወለዳቸው ልጆች አባት ነበር
ቁጥር 18 እርሱን ግን ከታናሽነቴ ጀምሬ እንደ አባቱ ከእኔ ጋር አሳድጌው ነበር፥
·         እርስዋንም ከእናቴ ማኅፀን ጀምሬ መራኋት፤
·         በታላቅ የህይወት ደረጃ ይመላለስ ነበር
ቁጥር 19 ራቁቱን የሆነው ሰው ሲጠፋ፥ ወይም ድሀ ያለ ልብስ ሲሆን አይቼ እንደ ሆነ፥
ቁጥር 20 ጐንና ጐኑ ያልባረከችኝ፥ በበጎቼም ጠጕር ያልሞቀ እንደ ሆነ፤
·         ያለውን ተሰሚነት ተጠቅሞ የሚረዳው የሌለውን ሰው አይጨቁንም
ቁጥር 21 በበሩ ረዳት ስላየሁ፥ በድሀ አደጉ ላይ እጄን አንሥቼ እንደ ሆነ፥
·         በእግዚአብሄር እንጂ በወርቅና በር ተስፋ አያደርግም አይመካም ነበር  
ቁጥር 24 ወርቅን ተስፋ አድርጌ፥ ጥሩውንም ወርቅ፦ በአንተ እታመናለሁ ብዬ እንደ ሆነ፤
·         በእግዚአብሄር እንጂ ሃብቱ ደስ ላለመሰኘት ይጠነቀቅ ነበር
ቁጥር 25 ሀብቴ ስለ በዛ፥ እጄም ብዙ ስላገኘች ደስ ብሎኝ እንደ ሆነ፤
·         ከእግዚአብሄር ውጭ ምንም ነገርን ላለማድነቅና ላለማምለክ ይጠነቀቅ እንደክህደት የቆጥረው ነበር  
ቁጥር 26 ፀሐይ ሲበራ ጨረቃ በክብር ስትሄድ አይቼ፥
ቁጥር 27 ልቤ በስውር ተታልሎ፥ አፌም እጄን ስሞ እንደ ሆነ፤
·         በሚጠላው ሰው ውድቀት ላለመደሰት ራሰነ ይገዛ ነበር
ቁጥር 29 በሚጠላኝ መጥፋት ደስ ብሎኝ ክፉ ነገርም ባገኘው ጊዜ ሐሤት አድርጌ እንደ ሆነ፤
·         ጠላቱን ላለመርገም ይጠነቀቅ ነበር
ቁጥር 30 ነገር ግን በመርገም ነፍሱን በመሻት አንደበቴን ኃጢአት ይሠራ ዘንድ አልሰጠሁም፤
·         ያለው ነገር ለሌሎች እንደተሰጠው ያምን ነበር
ቁጥር 32 መጻተኛው ግን በሜዳ አያድርም ነበር፥ ደጄንም ለመንገደኛ እከፍት ነበር፤
·         ሃጢያቱን ከመሸሸግ ይልቅ ለመናዘዝና ለመተው ፈጣን ነበር
ቁጥር 33 በደሌንም በብብቴ በመሸሸግ ኃጢአቴን እንደ ሰው ሰውሬ እንደ ሆነ፤
·         እውነትን ከመናገር የሰው ብዛት እንዳያስፈራው እና ከፍርድ እንዳያስተው ይጠነቀቅ ነበር
ቁጥር 34 ከሕዝብ ብዛት ፈርቼ፥ የዘመዶቼም ንቀት አስደንግጦኝ፥ ዝም ብዬ ከደጅ ያልወጣሁ እንደ ሆነ፤

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የመንፈስፍሬ #ፍቅር #ሰላም #ደስታ #ኢዮብ #ባህሪ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #የእግዚአብሄርህይወት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #በጎነት #የዋሃት #ራስንመግዛት #ትግስት #መሪ

Saturday, November 10, 2018

ፍቅር ገደብ ያስፈልገዋል


ኢትዮጰያና የኤርትራ መለያየት ያልነበረባቸው ህዝቦች ነበሩ፡፡ አሁንም ኢትዮጰያና የኤርትራ ግንኙነት መታደስና መጠናከር ሁለቱንም ህዝቦች ደስ ሊያሰኝ ይገባል፡፡ ሁለቱ አገሮት በፖለቲካ በኢኮኖሚያ በማህበራዊው ዘርፍ እጅ ለእጅ ተያይዘው ቢሰሩ በግላቸው ከሚሮጡት በላይ ፍሬያማ ይሆናሉ፡፡
ነገር ግን ማንኛውም ግንኙነት ደግሞ ገደብ ሊኖረው ይገባል፡፡ ማንኛውም ግንኙነት በመርህ ላይ የተመሰረተ መጀመሪያውና መጨረሻው የሚታወቅ ሊሆን ይገባል፡፡ ማንኛውም ግንኙነት ቅድሚያ የሚሰጠውና የማይሰጠው ነገር ሊኖር ይገባል፡፡
ይህን ፅሁፍ ለመፃፍ ያነሳሳኝ ሰሞኑን የኤትርራው ፕሬዝዳንት የአማራ ክልል ጉብኝት ወቅት በንንግግራቸው ላይ ያነሱት ነጥብ ነው፡፡ 
በንግግራቸው የአማራ ህዝብ ወዳጅ እንደሆኑ ነገር ግን ችግር የፈጠረባቸው ህወአት መሆኑን በንግግራቸው ገልፀዋል፡፡ ይህ አሁን አገሪትዋ እየተከተለችው ላለችው የህዝቦች መቀራረብ እርቅና ሰላም የሚሰጠው ምንም ፋይዳ የሌለና እንዲያውም እንቅፋት የሚሆን ንግግር ነው፡፡
ኢትዮጲያና ኤርትራ ሁለት የተለያዩ አገሮች ናቸው፡፡ የሚያደርጓቸው ግንኙነቶች በአገር ደረጃ የተወሰነ ግንኙነቶች መሆን አለባቸው፡፡ የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የአማራ ክልል ጉብኝት በፌደራል መንግስቱ በኩል የተደረገ ከሆነ ምንም ችግር የለውም፡፡ ነገር ግን የፕሬዝዳንት አፈወቀርቂ ንግግር በመንግስታት ደረጃ ከሚደረግ የጉብኝት ንግግር የዘለለ ነበር፡፡
ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በንግግራቸው ህወአትን በመቃወም "ተከፍሎ የማያልቅ ግፍ የፈፀመብን ህወሃት ነዉ" ብለው የተናገሩን እውነት ቢሆንም እንኳን በአሁኑ ጊዜ ላለው ለህዝቦች መቀራረብ እርቅና ሰላም የማይጠቅም ብሎም የሚጎዳ ንግግር ነው፡፡ 
ኢትዮጲያን የሚመራው የኢሃዲግ መንግስት ነው፡፡ ህወአት ደግሞ የኢህአዲግ አባል ድርጅት ነው፡፡ ህወአት በኢህአዲግ በኩል ኢትዮጲያን እየመራ ያለ ገዢ ፓርቲ ነው፡፡
ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጲያ መንግስት ለጉብኝት ተጋብዘው የኢትዮጲያን መንግስት እየመራ ያለውን የገዚውን ፓርቲ የኢህአዲግን አባል ድርጅት መተቸት የሚገባቸው አይመስለኝም፡፡ የኢትዮጲያን መንግስት እያስተዳደረ ያለውን የኢሃዲግን አንዱን አባል ድርጅት ሲኮንኑ  አሁን ላለንበት የሰላም የእርቅና የመቀራረብ ደረጃ ስለማይመጥን ማስተካከያ ሊሰጥበት ይገባል፡፡ 
ይህ አይነት በህወአትና በኤአግ /በሻብያ/ መካከል የነበረው ድንበርንና ወስንን ያልለየ ፈር የለቀቀ ግንኙነት ለኢትዮ ኤርትራ ጦርነት መነሳት አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ አሁንም የሁለቱ አገሮች ግንነት እንደጉርብትና ድንበት ሊበጅለት ይገባል፡፡
ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂም ቢሆኑ ከኢትዮጲያ ጋር ያለላው ግንኙነት ድንበሩን ያላለፈ ሊሆን ይገባዋል፡፡ የፕሬዝዳንት ኢሳያስ በኢትዮጲያ የውስጥ ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ ባይገቡ ለሚመለከታቸው ክልሎችና የፖለቲካ ድርጅቶች ቢተዉት ይመረጣል፡፡
አሁን ኢትዮጲያና ኤርትራ የተለያዩ አገሮች ናቸው፡፡ ግንኙነታቸውም የጉርብትና በሁለት አገሮች መካካል ያለ ግንኙነት ሊሆን ይገባዋል፡
የአማራ ክልላዊ መንግስት ከኤርትራ ሃገር ጋር ካለው ግንኙነት ይልቅ በኢትዮጲያ ውስጥ ያለውን ከትግራይ መንግስትና የትግራይን መንግስትን ከሚመራው ከህወአት ጋር ያለው ግንኙነት ይበልጥበታል፡፡ የአማራ ክልላዊ መንግስት ከትግራይ ክልላዊ መንግስት ጋር የሚያጋጨውን ነገር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቢጥር ይመረጣል፡፡ የትግራይ ክልላዊ መንግስት አመራሮችና የአማራ ክልላዊ መንግስት አመራሮች ለመነጋገርና ለመተማመን የሌላ አገር መሪ በጉዳያቸው ውስጥ ጣልቃ እንዲገባ አያስፈልጋቸውም፡፡ 
የአማራ ክልላዊ መንግስትና የትግራው ክልላዊ መንግስታት በክልልም የሚዋሰኑ በመሆናቸው ያለባቸውን ማንኛውም ችግር በእርጋታ ቢፈቱ ይመረጣል፡፡ ሁለቱ ክልሎች እና ሁለቱ ፓርቲዎች ካለማንም የውጭ ጣልቃ ገብነት በመቀራረብ ለሰላምና ለአብሮነት መስራታቸው ለአገሪቱ አንድነትና እድገት ትልቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡
ፕሬዝዳንት ኢሳያስም ቢሆኑ በኢትዮጲያ ውስጥ ባሉ ክልሎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ ያን ያህል ጣልቃ እንዲገቡ በፌደራል መንግስቱ በኩል ገደብ ሊበጅላቸው ይገባል፡፡ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአጠቃላይ የአገር ጉዳዮች ላይ የአገር ለአገር ግንኙነት ብቻ ላይ ማተኮት ይኖርባቸዋል፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ኤርትራ #ሰላም #እርቅ #ክልል #ህወአት #ፍትህ #ፍርድ #አናሳ #አብላጫ #ዲሞክራሲ #ጭቆና #እምባገነን #ሰብአዊመብት #ገደብ #ወሰን #ነገ #ትላንት #መሪ#ድሃ  #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Wednesday, November 7, 2018

የእስራኤል ዳንሳ ንግግር በእግዚአብሄር ቃል ሲፈተሽ

ነቢይ የእግዚአብሄር አፍ ነው፡፡ ነቢይ ከለአግዚአብሄር ሰምቶ የሚናገር ነው፡፡ ነቢይ የእግዚእብህር በልቡና ያለውን ተረድቶ ለህዝቡ የሚገልፅ ነው፡፡
በድሮ ዘመን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሄር ነቢይን በዚህ በእኛ ዘመን እንደሚያስነሳ ከእግዚአብሄር ቃል እንረዳለን፡፡  
እውነተኛ ነቢያት ባሉበት ሁሉ ግን ሃሳተኛ ነቢያት ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ እውነተኛ ነቢያት በፊትም እንደነበሩ አሁንም እውነተኛ ነቢያት አሉ፡፡ ሃሰተኛ ነቢያት በፊትም እንደነበሩ አሁንም ሃሰተኛ ነቢያት አሉ፡፡ የሃሰተኛ ነቢያት መኖር የእውነተኛ ነቢያትን መኖር እንጂ አለመኖር አያሳይም፡፡
ማንኛውም ሰው እንደሚሳሳት ሁሉ ነቢይ ሊሳሳይት ይችላል፡፡ ነቢይ ሲሳሳት ግን እንደማንኛውም አገልጋይ ፈጥኖ ንስሃ መግባትና ከስህተቱ መመለስ አለበት፡፡ ነቢይ በአንድ ነገር ተሳሳተ ማለት ደግሞ በሁሉም ነገር ተሳሳተ ማለት አይደለም፡፡ እያንዳንዱ ቃሉና ድርጊቱ በእግዚአብሄር ቃል መመርመር ይኖርበታል፡፡
ከእግዚአብሄር ቃል በላይ የሆነ አገልጋይም አገልግሎትም የለም፡፡ የነቢይ ብቻ ሳይሆን የማንም ሰው አገልግሎት በእግዚአብሄር ቃል መፈተሽ አለበት፡፡
አንዳንድ የስህተት ነቢያት የሚያደርጉትናና የሚናገሩትን ስናይ ነቢያትን በደፈናው ላለመቀበል አንፈተናለን፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ ትንቢትን አትናቁ ሲለን ከምናያቸውና ከምንሰማቸው አንዳንደ የተሳሳቱ ነገሮች አንፃር ትንቢትን በደፈናው እንዳንጥል እያስጠነቀቀን ነው፡፡ ነቢያት አንዳንድ ከእግዚአብሄር ቃል ውጭ የተናገሩት ነገር አለ ብለን የሚናገሩትን ሁሉ መጣል የለብንም፡፡ አንዳንድ የስህተት ነቢያት ስላሉ ብቻ እግዚአብሄር በትክክለኛው ነቢያት ውስጥ ያስቀመጠልንን ፀጋ እንዳንገፋ የእግዚአብሄር ቃል ያስጠነቅነቀናል፡፡  
መፅሃፍ ቅዱስ ደግሞ ትንቢትን መርምሩም ይለናል፡፡ ነቢይ ስለተናገረ ብቻ መቀበል ጥፋት ነው፡፡ የነቢይም ይሁን የማንኛውም አገልጋይ ንግግር ወይም ድርጊት በእግዚአብሄር ቃል መፈተን አለበት፡፡ ከእግዚአብሄር ቃል ጋር የማይሄድ ማንኛውም ንግግር ማንም ይናገረው ማን ተቀባይነት የለውም፡፡
መንፈስን አታጥፉ፤ ትንቢትን አትናቁ፤ ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ፤ 1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 5፡19-21
ከዚህ በፊት በፃፍኳቸው ፅሁፎች ነቢይነት ምን እንደሆነ እንዲሁም የነቢይትነት ፈተናዎች ምን አንደሆኑ ጠቃቅሻለሁ፡፡ አሁን ግን ይህን ፅሁፍ ለመፃፍ ያነሳሳኝ የእስራኤል ዳንሳ ንግግር ነው፡፡
የዚህ ፅሁፍ አላማ እስራኤል ዳንሳ ስህተተኛ ነቢይ ነው ወይስ ትክክለኛ ነቢይ ነው የሚለውን ጥያቄ መመለስ አይደለም፡፡  
የዚህ ፅሁፍ አላማ እስራኤል ዳንሳ የተናገረውን አንድ ንግግር በማንሳት እንደ እግዚአብሄር ቃል ትክክል ነው አይደለም የሚለውን መለየት ነው፡፡  
ነቢያትም ሁለት ወይም ሦስት ሆነው ይናገሩ ሌሎችም ይለዩአቸው፤ 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 14፡29
በመጀመሪያ ደረጃ ነቢይነት ይሁን ሌሎች የአገልግሎት ስጦታዎች በሰው ፈቃድ የሚመጡ አይደሉም፡፡ ነቢይነት የእግዚአብሄር ስጦታ ነው፡፡ እግዚአብሄር እንደወደደ አንዳንዶቹን ብቻ ነቢያት በማድረግ ለቤተክርስትያን ሰጥቶዋል፡፡ ነቢይነት እግዚአብሄር እንደወደደ ለአንዳንዶች የሚሰጠው የአገልግሎት ስጦታ ነው፡፡
እርሱም አንዳንዶቹ ሐዋርያት፥ ሌሎቹም ነቢያት፥ ሌሎቹም ወንጌልን ሰባኪዎች፥ ሌሎቹም እረኞችና አስተማሪዎች እንዲሆኑ ሰጠ፤ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4፡11
ነቢይነት ወይም ሌላ ማንኛውም የአገልገሎት ስጦታ በሰው ፍላጎትና ፈቃድ አይመጣም፡፡
ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ። 2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1፡21
ይህ የእስራኤል ዳንሳ በንግግር ውስጥ እስራኤል ዳንሳ እንደዚህ ይላል፡፡
"እስኪ ነቢይ መሆን የምትፈልጉ??_______አንተን ነቢይ ለማድረግ ከጌታ መስማት አይጠበቅብኝም:: በራሴ ወጭ ነቢይ አደርግሃለሁ:: "
እኔ ከፈለግኩ ብቻ እግዚአብሄር ሳይናገረኝ ነቢይ ላደርግህ እችላለሁ ማለት ስህተት ነው፡፡ እግዚአብሄር እንጂ ሰው ሰውን ወደአግልግሎት ሊጣረ አይችልም፡፡ ይህ አባባል አደገኛና ሰዎች ጥሪው ሳይኖራቸው እግዚአብሄር ለዚያ የተለየ አገልግሎት ሳይጠራቸው እንዲገቡበትና ህይወታቸውን እግዚአብሄር በማይፈልጋቸው ቦታ ላይ እንዲያባክኑ የሚያደርግ አሳች ንግግር ነው፡፡
እነዚህም ጌታን ሲያመልኩና ሲጦሙ መንፈስ ቅዱስ፦ በርናባስንና ሳውልን ለጠራኋቸው ሥራ ለዩልኝ አለ። የሐዋርያት ሥራ 13፡2
ኢየሱስ እንኳን በምድር በነበረበት ጊዜ እንደ ሰው ልጅ በእግዚአብሄር አብ ላይ ሙሉ ለሙሉ ይደገፍ ነበር፡፡ ኢየሱስ እንኳን የሰማሁትን አደርጋለሁ እያለ ይናገር ነበር፡፡
እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ። ስለዚህ እኔ የምናገረውን አብ እንደ ነገረኝ እንዲሁ እናገራለሁ። የዮሐንስ ወንጌል 12፡49-50
እኔ በአባቴ ዘንድ ያየሁትን እናገራለሁ፤ እናንተም ደግሞ በአባታችሁ ዘንድ ያያችሁትን ታደርጋላችሁ። የዮሐንስ ወንጌል 12፡38
እንዲያውም ከጌታ የሰማውምን ከማድረግ ውጭ ኢየሱስ በራሱ ምንም ማድረግ እንደማይችል ይናገር ነበር፡፡
ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብ ሲያደርግ ያየውን ነው እንጂ ወልድ ከራሱ ሊያደርግ ምንም አይችልም፤ ያ የሚያደርገውን ሁሉ ወልድ ደግሞ ይህን እንዲሁ ያደርጋልና። የዮሐንስ ወንጌል 12፡19
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የመንፈስፍሬ #ቅባት #መንፈስቅዱስ #የእግዚአብሔርመንፈስ #መሪ #ቤተመቅደስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ነቢያት #ነቢይ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ