Popular Posts

Tuesday, August 31, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 16

 


እግዚአብሄር በመጀመሪያ የፈጠረን በጤንነት ነው፡፡ ከጥንት እግዚአብሄር ሙላትን ጤንነትን እና ብርታትን እንጂ በሽታንና ደዌን አልፈጠረም፡፡

በማንኛውም ምክኒያት ጤንነታችንን ብናጣና ብንታመም የእግዚአብሄር የልብ ፍላጎት መፈወሳችን ነው፡፡ እግዚአብሄር ሁልጊዜ ፈውሳችንን ይፈልገዋል፡፡

በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሄር ህዝብ አንዱ ቃልኪዳን የስጋ ፈውስ መሆኑን ስናስብ እግዚአብሄር ህዝቡ እንዲፈወሱና በጤንነትና በብርታት እንዲኖሩ ያለውን በጎ ፈቃድ ያሳያል፡፡

 እርሱም፦ አንተ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ቃል አጥብቀህ ብትሰማ፥ በፊቱም የሚበጀውን ብታደርግ፥ ትእዛዙንም ብታደምጥ፥ ሥርዓቱንም ሁሉ ብትጠብቅ፥ በግብፃውያን ላይ ያመጣሁትን በሽታ አላደርስብህም፤ እኔ ፈዋሽህ እግዚአብሔር ነኝና አለ። ዘፀአት 1526

እግዚአብሔርም ሕማምን ሁሉ ከአንተ ያርቃል፤ የምታውቀውንም ክፉውን የግብፅ በሽታ ሁሉ በአንተ ላይ አያደርስብህም፥ በጠላቶችህም ሁሉ ላይ ያመጣባቸዋል። ዘዳግም 715

በአዲሱም ኪዳን የኢየሱስን አጠቃላይ አገልግሎት ስንመለከት ለህዝቡ ያለውን የእግዚአብሄርን ልብ እንመለከታለን፡፡

እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤ ሃዋሪያት 1038

በመሸም ጊዜ አጋንንት ያደረባቸውን ብዙዎችን ወደ እርሱ አመጡ፤ በነቢዩ በኢሳይያስ፦ እርሱ ድካማችንን ተቀበለ ደዌያችንንም ተሸከመ የተባለው ይፈጸም ዘንድ፥ መናፍስትን በቃሉ አወጣ፥ የታመሙትንም ሁሉ ፈወሰ። ማቴዎስ 816-17

ከዘፍጥረት እስከ ራእይ የእግዚአብሄር አላማ መፈወሳችን ነው፡፡

በዘመኑም መጨረሻ የእግዚአብሄር አላማ የሰው ልጆች ፈውስ ነው፡፡  

በወንዙም ወዲያና ወዲህ በየወሩ እያፈራ አሥራ ሁለት ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት ዛፍ ነበረ፥ የዛፉም ቅጠሎች ለሕዝብ መፈወሻ ነበሩ። የዮሐንስ ራእይ 222

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Monday, August 30, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 15

 

እግዚአብሄር የታመሙትን በመፈወስ የታወቀ አምላክ ነው፡፡

እግዚአብሔርም ሕማምን ሁሉ ከአንተ ያርቃል፤ የምታውቀውንም ክፉውን የግብፅ በሽታ ሁሉ በአንተ ላይ አያደርስብህም፥ በጠላቶችህም ሁሉ ላይ ያመጣባቸዋል። ዘዳግም 7፡15

እግዚአብሄር ሰዎች  እንዲወጡ ፣ እንዲገቡ ፣ እንዲሰሩ እና እንዲኖሩ ስለፈጠራቸው ሊያደክማቸው ሊያሳምማቸው እና የሚመጣውን ደዌንና ህማምን በመፈወስ ይታወቃል፡፡

ቃሉን ላከ ፈወሳቸውም፥ ከጥፋታቸውም አዳናቸው። መዝሙር 107፡20

እግዚአብሄር የቆሰሉትን በመፈወስ ይታወቃል፡፡

ልባቸውን የቈሰሉትን ይፈውሳል፥ ሕማማቸውንም ይጠግናል። መዝሙር 147፡3

እግዚአብሄር የተሰበሩትን በመጠገን የታወቀ አምላክ ነው፡፡

እኔ ጤናህን እመልስልሃለሁ ቍስልህንም እፈውሳለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር ማንም የማይሻት፥ የተጣለች ጽዮን ብለው ጠርተውሻልና። ኤርሚያስ 30፡17

እግዚአብሄር የፈውስ አምላክ ነው፡፡

የነቢዩንም የኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጡት፥ መጽሐፉንም በተረተረ ጊዜ፦ የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ለታሰሩትም መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፥ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል ተብሎ የተጻፈበትን ስፍራ አገኘ። ሉቃስ 4፡17-19

በኢየሱስ አገልግሎትም የተተረከው የእግዚአብሄር የፈውስ ቅናት ነው፡፡

እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤ ሐዋሪያት 10፡38

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Sunday, August 29, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 14

 


ለፈውስ እምነት ይጠይቃል፡፡ እኛ ብዙውን ጊዜ ራሳችንን ዝቅ አድርገን እንደምናየው እግዚአብሄር አያየንም፡፡ እግዚአብሄር የሚያየን እንደአብሮ ሰራተኛ አጋር ነው፡፡ ለፈውስ እምነት ይጠይቃል፡፡

እግዚአብሄር በኢየሱስ ክርስቶስ የሰራውን ለማየትና ለመጠቀም የእምነት እጅ ይጠይቃል፡፡ ፈውስን የምንቀበለው በእምነት ነው፡፡

ስለዚያም ነው ኢየሱስ ቃሉን ይሰብክ ነበር፡፡ ኢየሱስ በምድር አገልግሎቱ የእግዚአብሄርን ልብ ያሳይ ነበር፡፡ ኢየሱስ በምድር አገልግሎቱ እግዚአብሄርን ይተርከው ነበር፡፡

ፈውስን የሚያመጣው ለእኛ ያለውን የእግዚአብሄርን የፈውስ ፈቃድ መረዳት ስለሆነ በኢየሱስ የምድር አገልግሎት ዘመን ሰዎች ኢየሱስን ሊሰሙትና ሊፈወሱ ይመጡ ነበር፡፡

ከእነርሱም ጋር ወርዶ በተካከለ ስፍራ ቆመ፥ ከደቀ መዛሙርቱም ወገን ብዙ ሕዝብ ነበረ፥ ደግሞም ሊሰሙትና ከደዌአቸው ሊፈወሱ ከይሁዳ ሁሉ ከኢየሩሳሌምም ከጢሮስና ከሲዶና ባሕር ዳርም የመጡ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ሉቃስ 617

ኢየሱስ ኢየሱስ ስለሆነ ብቻ ከቃሉ ውጭ ምንም ሊያደርግላቸው አይችልም ነበር፡፡ ፈውስ ያለው የእግዚአብሄርን ሃሳብ በመረዳት ውስጥ ስለሆነ በኢየሱስ አገልግሎት ሰዎች ኢየሱስን ሊሰሙትና ሊፈወሱ ይመጡ ነበር፡፡

ወሬው ግን አብዝቶ ወጣ፥ ብዙ ሕዝብም ሊሰሙትና ከደዌአቸው ሊፈወሱ ይሰበሰቡ ነበር፤ ሉቃስ 515

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Saturday, August 28, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 13

 

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 13
ለፈውስ እምነት ይጠይቃል፡፡ እኛ ብዙን ጊዜ ራሳችንን ዝቅ አድርገን እንደምናየው እግዚአብሄር አያየንም፡፡ ለፈውስ እምነት ይጠይቃል፡፡ 
እግዚአብሄር በኢየሱስ ክርስቶስ የሰራውን ለማየትና ለመጠቀም የእምነት እጅ ይጠይቃል፡፡ ፈውስን የምንቀበለው በእምነት ነው፡፡ 
ስለዚያም ነው ኢየሱስ ቃሉን ይሰብክ ነበር፡፡ ኢየሱስ በምድር አገልግሎቱ የእግዚአብሄርን ልብ ያሳይ ነበር፡፡ ኢየሱስ በምድር አገልግሎቱ እግዚአብሄርን ይተርከው ነበር፡፡ 
ፈውስን የሚያመጣው ለእኛ ያለውን የእግዚአብሄርን የፈውስ ፈቃድ መረዳት ስለሆነ በኢየሱስ የምድር አገልግሎት ዘመን ሰዎች ኢየሱስን ሊሰሙትና ሊፈወሱ ይመጡ ነበር፡፡ 
ከእነርሱም ጋር ወርዶ በተካከለ ስፍራ ቆመ፥ ከደቀ መዛሙርቱም ወገን ብዙ ሕዝብ ነበረ፥ ደግሞም ሊሰሙትና ከደዌአቸው ሊፈወሱ ከይሁዳ ሁሉ ከኢየሩሳሌምም ከጢሮስና ከሲዶና ባሕር ዳርም የመጡ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ሉቃስ 6፡17
ኢየሱስ ኢየሱስ ስለሆነ ብቻ ከቃሉ ውጭ ምንም ሊያደርግላቸው አይችልም ነበር፡፡ ፈውስ ያለው የእግዚአብሄርን ሃሳብ በመረዳት ውስጥ ስለሆነ በኢየሱስ አገልግሎት ሰዎች ኢየሱስን ሊሰሙትና ሊፈወሱ ይመጡ ነበር፡፡ 
ወሬው ግን አብዝቶ ወጣ፥ ብዙ ሕዝብም ሊሰሙትና ከደዌአቸው ሊፈወሱ ይሰበሰቡ ነበር፤ ሉቃስ 5፡15
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa 
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Friday, August 27, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 12

 


ፈውስን የመለማመጃው መንገድ እግዚአብሄር ለእኛ ያለውን የፈውስ አላማ ከእግዚአብሄር ቃል መረዳት ነው፡፡ እግዚአብሄር ለእኛ ያለውን የፈውስ ልብ ስንረዳ ፈውሳችንን መለማመድ እንችላለን፡፡

ፈውሳችን በኢየሱስ ክርስቶስ መገረፍ ተሰርቶ አልቆዋል፡፡ አሁን ለፈውሳችን የሚያስፈልገው ነገር ስለፈውስ የእግዚአብሄርን ፈቃድ መረዳትና የእኛ የሆነውን በእምነት እጅ መቀበል ብቻ ነው፡፡

ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። 1ኛ ጴጥሮስ 2፡24

ሰዎች ለመዳን አግዚአብሄርን መጠበቅ የለባቸውም፡፡ እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል ደህንነትን ሰርቶ ጨርሶዋል፡፡ ሰው ደህንነትን በፈለገ ቁጥር እግዚአብሄር እንደ አዲስ የሚሰራው ደህንነት የለም፡፡ ሰው ለመዳን የሚያስፈልገው ኢየሱስ በመስቀል ላይ የሰራውን ነገር መስማትና መቀበል ብቻ ነው፡፡

ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው። ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ ሮሜ 10፡8-9

በተመሳይ መልኩ ሰው በታመመ ቁጥር እግዚአብሄር ፈውስን እንደገና አይሰራም፡፡ እግዚአብሄር ብልጁ በኢየሱስ ክርሰሰቶስ መገረፍ ፈውስን ሰርቶ ጨርሶዋል፡፡ ሰው ለመፈወስ የሚያስፈልገው ክርስቶስ ስለፈውሱ የተገረፈውን መገረፍ በመረዳት ፈውሱን እርምጃ መውሰድ ብቻ ነው፡፡

ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል። ዮሐንስ 314-15

ፈውስ የሚደገፈው በእግዚአብሄር የፈውስ ፈቃድ ላይ ባለን እምነታችን ላይ ነው፡፡ እግዚአብሄር በኢየሱስ የፈውስ ነገራችንን ሰርቶ ቢጨርስም እኛ በእምነት እስካልተቀበልን ድረስ ፈውስ ሊሰራልን አይችልም፡፡ ኢየሱስ በምድር አገልግሎቱ ጊዜ ከእምነታችው ማነስ ምክኒያት ያልፈወሳቸው ሰዎች ነበሩ፡፡

በአለማመናቸውም ምክንያት በዚያ ብዙ ተአምራት አላደረገም። ማቴዎስ 13፡58

በዚያም በጥቂቶች ድውዮች ላይ እጁን ጭኖ ከመፈወስ በቀር፥ ተአምር ሊያደርግ ምንም አልቻለም። ማርቆስ 6፡5

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Thursday, August 26, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 11

 

ክርስቶስ ስለሃጢያታችን  ከቃሉ በመስቀል ላይ እንደሞተ ከቃሉ ስናይ ደህንነታችንን እንቀበላለን፡፡ እንዲሁም ኢየሱስ ስለሃጢያታችን መገረፉን ከልባችን ስንረዳ በሽታ በእኛ ላይ አቅም አይኖረውም፡፡

የሰው ፈውስ በመስቀል ላይ ተሰርቶ አልቆዋል የሚባለው ስለዚህ ነው፡፡ ኢየሱስ ስለሃጢታታችን እንደገና አይሞትልንም እርሱ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ተሰቀለልን፡፡ የእኛ ፋንታ ለእኔ ነው የተሰቀለው ብለን የተሰቀለውን ማየትና እውቅና መሰጠት ብቻ ነው፡፡

ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል። ዮሐንስ 3፡14-15

እንዲሁም ኢየሱስ ስለበሽታችን እንደገና አይገረፍልንም፡፡ ኢየሱስ ለሃጢያትንና ለሃጢያት ተያያዥ ጥቃቄዎችን በመስቀል ላይ መልስ መልሶ ተፈፀመ ብሎዋል፡፡

አሁን የሚጠበቅብን ነገር የእግዚአብሄር ቃል ስለፈውሳችን የሚለውን መፈለግ ፣ ማንበብ ፣ ማጥናትና ማሰላለስ ብቻ ነው፡፡ ክርስቶስ ስለበሽታችን የሰራውን ስራ የተገረፈውን መገረፍ ማየት ስንጀምር ፈውሳችንን እንቀበላለን፡፡

ፈውስ የሚመጣው በእምነት ነው፡፡ ክርስቶስ በመስቀል ያደረገልንን ነገር ከእግዚአብሄር ቃል ስናይ እምነት ይመጣል፡፡

እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ሮሜ 10፡17

መጽሃፍ ቅዱስ የእምነት ፀሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል የሚለን ለዚህ ነው፡፡

የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል። ያዕቆብ 5፡15

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Wednesday, August 25, 2021

የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 10

 

 የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 10

ፈውስ የልጆች እንጀራ ነው፡፡ ፈውስ የልጆች መብት ነው፡፡ 

እርሱ ግን መልሶ፦ የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም አለ። ማቴዎስ 15፡26

ኢየሱስ ስለነፍሳችን ብቻ ሳይሆን ስለስጋችን ፈውስ ዋጋ ከፍሎዋል፡፡ 

ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። 1ኛ ጴጥሮስ 2፡24

በመሸም ጊዜ አጋንንት ያደረባቸውን ብዙዎችን ወደ እርሱ አመጡ፤ በነቢዩ በኢሳይያስ፦ እርሱ ድካማችንን ተቀበለ ደዌያችንንም ተሸከመ የተባለው ይፈጸም ዘንድ፥ መናፍስትን በቃሉ አወጣ፥ የታመሙትንም ሁሉ ፈወሰ። ማቴዎስ 8፡16-17

የታመመ ሰው ከበሽታው ጋር ከመኖር ይልቅ የቤተክርስትያን ሽማግሌዎችን እንዲጠራና ለፈውስ እንዲፀልዩለት መፅሃፍ ቅዱስ የሚያዘው ለዚህ ነው፡፡  

ከእናንተ የታመመ ማንም ቢኖር የቤተ ክርስቲያንን ሽምግሌዎች ወደ እርሱ ይጥራ፤ በጌታም ስም እርሱን ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት። የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል። ያዕቆብ መልእክት 5፡14-15

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa 

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Tuesday, August 24, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 9

 

እግዚአብሄር የፈጠረው ፍጥረት ሁሉ መልካም ነበር፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው በነፍስም በስጋም ሙሉ አድርጎ ነው፡፡

በሰንበትም በአንድ ምኵራብ ያስተምር ነበር። እነሆም፥ ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባት ሴት ነበረች፥ እርስዋም ጐባጣ ነበረች ቀንታም ልትቆም ከቶ አልተቻላትም። ኢየሱስም ባያት ጊዜ ጠራትና። አንቺ ሴት፥ ከድካምሽ ተፈትተሻል አላት፥ እጁንም ጫነባት፤ ያን ጊዜም ቀጥ አለች፥ እግዚአብሔርንም አመሰገነች። የምኵራብ አለቃ ግን ኢየሱስ በሰንበት ስለ ፈወሰ ተቈጥቶ መለሰና ሕዝቡን፦ ሊሠራባቸው የሚገባ ስድስት ቀኖች አሉ፤ እንግዲህ በእነርሱ መጥታችሁ ተፈወሱ እንጂ በሰንበት አይደለም አለ። ጌታም መልሶ፦ እናንተ ግብዞች፥ ከእናንተ እያንዳንዱ በሰንበት በሬውን ወይስ አህያውን ከግርግሙ ፈትቶ ውኃ ሊያጠጣው ይወስደው የለምን? ይህችም የአብርሃም ልጅ ሆና ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ ሰይጣን ያሰራት በሰንበት ቀን ከዚህ እስራት ልትፈታ አይገባምን? አለው። ሉቃስ ወንጌል 1310-16

ከምናስበው በላይ ብዙ ነገር መንፈሳዊ ነው፡፡ ዶክተሮች በመንፈሳዊ አለም ሊገልፁት ስለማይችሉ የዲስክ መንሸራተት ነው ሊሉ ይችላሉ፡፡ ጌታ ግን ከስጋዊው አለም አሻቅቦ መንፈሳዊውን አለም ስለሚያይ ሰይጣን ያሰራትን አለ፡፡

ከብዙ ጥቃቶች ጀርባ ሰይጣን ዲያቢሎስ አለ፡፡ ሰይጣን ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ እንጂ ስለሌላ አይመጣም፡፡

ስለዚህም ነው ኢየሱስ በምድር በተመላለሰ ጊዜ በታላቅ ቅናት የዲያቢሎስን ስራ ያፈርስ የነበረው፡፡

ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። 1ኛ ዮሃንስ 3፡9

እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤ ሐዋሪያት 10፡38

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ