Popular Posts

Showing posts with label Learn to Enjoy life. Show all posts
Showing posts with label Learn to Enjoy life. Show all posts

Wednesday, August 12, 2020

አንተን ካገኘሁ ጀምሮ ህይወቴ በአንተ አምሮ

 

አንተን ካገኘሁ ጀምሮ
ህይወቴ በአንተ አምሮ
የምህረትን ብዛት አልችልም ልገልጣት
የፍቅርህን ብዛት አልችልም ልገልጣት
ዘማሪ አገኘሁ ይደግ

Sunday, June 21, 2020

ሰው ደስ ከሚለውና በሕይወቱ ሳለ መልካምን ነገር ከሚያደርግ በቀር መልካም ነገር እንደሌለ አወቅሁ። ደግሞም ሰው ሁሉ ይበላና ይጠጣ ዘንድ በድካሙም ሁሉ ደስ ይለው ዘንድ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው። ከሚበላውና ከሚጠጣው ደስም ከሚለው በቀር ለሰው ከፀሐይ በታች ሌላ መልካም ነገር የለውምና እኔ ደስታን አመሰገንሁ፤ ከፀሐይም በታች ከድካሙ እግዚአብሔር በሰጠው በሕይወቱ ዘመን ይህ ደስታው ከእርሱ ጋር ይኖራል። መጽሐፈ መክብብ 3፡12-13 ፣ 8፡5

ሰው ደስ ከሚለውና በሕይወቱ ሳለ መልካምን ነገር ከሚያደርግ በቀር መልካም ነገር እንደሌለ አወቅሁ። ደግሞም ሰው ሁሉ ይበላና ይጠጣ ዘንድ በድካሙም ሁሉ ደስ ይለው ዘንድ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው። ከሚበላውና ከሚጠጣው ደስም ከሚለው በቀር ለሰው ከፀሐይ በታች ሌላ መልካም ነገር የለውምና እኔ ደስታን አመሰገንሁ፤ ከፀሐይም በታች ከድካሙ እግዚአብሔር በሰጠው በሕይወቱ ዘመን ይህ ደስታው ከእርሱ ጋር ይኖራል። መጽሐፈ መክብብ 3፡12-13 ፣ 8፡5

Sunday, April 26, 2020

በምድር ያለነው


በተለያየ ጊዜ በህይወታችን የተለያዩ ተግዳሮቶች ይመጣሉ፡፡ ታዲያ ይህን አልፈው ይሆን ብለን የምናስብበት ውጥረት በህይወታችን ይመጣል፡፡ እንደዚህ አይነት ውጥረት በህይወታችን ሲገጥመን "በምድር ላይ ያለሁት ለምንድነው?" ብለን ይህን ጥያቄ ከልባችን እንጠይቃለን፡፡
በምድር ላይ ያለሁት ለምንድነው? የሚለው ጥያቄ ሁል ጊዜ መጠየቅና በትክክል መመለስ ያለበት ጥያቄ ነው፡፡
እውነት ግን በምድር ላይ ያለነው ለምንድነው?
የማንሞተው ለምንድነው ? ወይም መሞት የማንፈልገው ለምንድነው ?
በምድር ላይ ያለነው ስላልሞትን ነው ? ወይስ በምድር ላይ ስለመኖራችን ሌላ አለማ አለ?
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው አስቦና አቅዶና በአላማ ነው፡፡
እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ። እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። ኦሪት ዘፍጥረት 1፡26-27
ወደምድር ከመምጣታችን በፊት ወደምድር የመጣንበት ልዩ አላማ ነበር፡፡
ማንም ሰው በድንገት ውይም በአጋጣሚ በምድር ላይ የተወለደ ሰው የለም፡፡ ሰው በምድር ላይ የመወለዱ ምልክት ከመወለዱ በፊት የተወለደበት ልዩ አላማ የመኖሩ ምልክት ነው፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ኤርሚያስ 29፡11
እኛ በምድር ላይ ለመኖር ከምንፈልገው በላይ እግዚአብሄር በምድር ላይ እንድንኖር ይፈልጋል፡፡ በምድር ላይ ለመኖር ካለን ፍላጎት በላይ በምድር ላይ እንድንኖር የተፈለገበት የእግዚአብሄር አላማ ይበልጣል፡፡
በሰው ልብ ብዙ አሳብ አለ፤ የእግዚአብሔር ምክር ግን እርሱ ይጸናል። ምሳሌ 19፡21
በመጀመሪያ መጨረሻውን፥ ከጥንትም ያልተደረገውን እነግራለሁ፤ ምክሬ ትጸናለች ፈቃዴንም ሁሉ እፈጽማለሁ እላለሁ። ኢሳያስ 46፡10
ይህን በህይወታችን ላይ ያለውን የእግዚአብሄርን አላማ ስንረዳ እናርፋለን፡፡
እግዚአብሄር እንዴት እንደሚወደን ስንረዳ እና በህይወት ለመኖራችን ልዩ አላማ እንዳለው ስንረዳ ከፍርሃት ነፃ እንወጣለን፡፡
እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን። ኤፌሶን 2፡10
ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፥ ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም አይደለም። እርሱ አስቀድሞ ወዶናልና እኛ እንወደዋለን። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፡18-19
ፍርሃት የእግዚአብሄርን ፍቅር የመረዳታችንን ደረጃ ያመለክታል፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ያለውን የፍቅር አላማ በተረዳን መጠን ፍርሃት ከህይወታችን ቦታ እያጣ ይሄዳል፡፡  
የእግዚአብሄርን ፍቅር በተረዳን መጠን ከፍርሃት ነፃ እንወጣለን፡፡ እግዚአብሄር እንዴት በፍቅር እንደሚያየን በህይወታች ላይ ያለውን የእግዚአብሄርን የፍቅር አላማ እየተረዳን ስንመጣ በፍርሃት ሳይሆን በፍቅር እንንቀሳቀሳለን፡፡
የእግዚአብሄርን የፍቅር አለማ ስንረዳ የሚያንቃቅሰን ፍርሃት ሳይሆን ፍቅር ብቻ ይሆናል፡፡
በእኔ ላይ ያለው ዓላማውም ፍቅር ነው። መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 2፡4
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #እይታ #አላማ #ተስፋ #ፍፃሜ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ተስፋ #ፍፃሜ #የእግዚአብሄርሃሳብ #የእግዚአብሄርእቅድ #የእግዚአብሄርፈቃድ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Wednesday, February 12, 2020

ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም



ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም። መጽሐፈ መክብብ 11፡4
ህይወት የእምነት ጉዞ ነው፡፡ ህይወትን በሚገባ ማጣጣም ከፈለግክ በእምነት መኖር መጀመር አለብህ፡፡ በእምነት መራመድ ካልጀመርክ የህይወትን እውነተኛውን ጣእም በፍፁም አታገኘውም፡፡ ሰው መኖር የሚጀምረው በእምነት መራመድ ሲጀምር ብቻ ነው፡፡ የሰው እውነተኛ መኖሪያ የእግዚአብሄር ቃል እምነት ነው፡፡
እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። የማቴዎስ ወንጌል 4፡4
ሰው ዲዛይን የተደረገው ለእምነት ኑሮ ነው፡፡ ሰው የሚኖረው በእምነት ነው፡፡
እነሆ፥ ነፍሱ ኰርታለች፥ በውስጡም ቅን አይደለችም፤ ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል። ትንቢተ ዕንባቆም 2፡4
እምነት የሚመጣው ከእግዚአብሄር ቃል ነው፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡17
በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ለተፈጠረው ክቡር ለሆነው ሰው ለሰው ልጅ ከእግዚአብሄ ቃል ያነሰ ኑሮ አይገባውም፡፡
እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። የማቴዎስ ወንጌል 4፡4
የሰው እውነተኛ እርካታ በእምነት ሲኖር ነው፡፡
ነገሮች ሆነው ከማየትህ በፊት የእግዚአብሄርን ቃል አምነህ እርምጃ ካለወሰድክ ከእግዚአብሄር ጋር መኖር አትችልም፡፡
ከእግዚአብሄር ጋር የምትገናኘው በስጋ አይን የማይታየውን መንፈስ የሆነውን እግዚአብሄርን የምትሰማው ፣ እግዚአብሄርን የምትነካው ፣ እግዚአብሄርን የምታየው ሁሉ በእምነት ነው፡፡ የእግዚአብሄር ነገር ሁሉ በእምነት ነው፡፡
የእግዚአብሔር ቃል ቅን ነውና ሥራውም ሁሉ በእምነት ነውና። መዝሙረ ዳዊት 334
ነገሮች ተለውጠው ደስ ለመሰኘት የምትጠብቅ ከሆነ ደስ መሰኘቱን እርሳው፡፡ ነገሩን የሚለውጠው በእምነት እርምጃ በመውሰድ ደስ በመሰኘትህ ብቻ ነው፡፡
የምትፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ ኪስህ ከገቡ በኋላ እፎይ ለማለት እየጠበቅክ ከሆነ የማይፈፀም ተስፋ እየጠበክ ነው፡፡
ለማመን ፀሎትህ እስኪመለስ እየጠበቅክ ከሆነ ፀሎትህ ለመፈፀም የአንተን እምነት እየጠበቀ ነው፡፡
እውነት እላችኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል። ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል። የማርቆስ ወንጌል 11፡23-24
ሁሉ ደህና ነው ለማለት ነገሮች ሁሉ ተስተካክለው እስክታይ አየጠበቅክ ከሆነ በከንቱ ትጠብቃለህ፡፡   
ከመዝራትህ በፊት ሁኔታዎችን እየጠበቅክ ከሆነ መቼም አታጭድም፡፡
ምልክት ከማየትህ በፊት ማመን አለብህ፡፡ እምነትንም የሚያመጣው የእግዚአብሄር ቃል እንጂ ምልክት እምነትን አያመጣም፡፡ ምልክቱን የሚያመጣው እምነትህ ነው፡፡  
ከውጤት እና ከምልክት በፊት የእምነት እርምጃ ይቀድማል፡፡
እንጀራህን በውኃ ፊት ላይ ጣለው፥ ከብዙ ቀን በኋላ ታገኛዋለህና። መጽሐፈ መክብብ 11፡1
አስቀድመው ምልክትን የሚፈልጉ ካላየሁ አላምንም የሚሉ ሰዎች እግዚአብሄርን የማይፈልጉ አሿፊ ሰዎች ናቸው፡፡
ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያንም ቀርበው ሲፈትኑት ከሰማይ ምልክት እንዲያሳያቸው ለመኑት። ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፥ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም። ትቶአቸውም ሄደ። የማቴዎስ ወንጌል 16፡1፣4
ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም። መጽሐፈ መክብብ 11፡4
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እምነት #ወንጌል #ስብከት #ቃል #ዝራ #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ 

Thursday, November 3, 2016

ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን

ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ በእግዚአብሔር እመኑ። እውነት እላችኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል። ማርቆስ 11፡22-23
መፅሃፍ ቅዱሳችንን ስናጠና በጣም የሚያስደንቀንና የሚያስገርመን ነገር በእግዚአብሄር ዘንድ ያለን ቦታ እጅግ የከበረ እንደሆና እኛ ራሳችንን እንደምናየው እግዚአብሄር እኛን እነደማያየን ነው፡፡ እኛ በእግዚአብሄር ዘንድ ያለንን ቦታ በትክክል የሚያሳየን የእግዚአብሄር ቃል ብቻ ነው፡፡
በእግዚአብሄር ዘንድ ያለንን ስልጣን የምንጠቀምበት በመናገር እንደሆነ ኢየሱስ ያስተምራል፡፡ በክርስቶስ የዳነ ሰው ቃል ስልጣን አለው፡፡ በክርስቶስ ያለ ሰው በቃሉ ያለው ስልጣን አስደናቂ ነው፡፡
ማንም ያለው እንዲደረግለት በማለት በእግዚአብሄር ዘንድ ያለን የልጅነት ስልጣንና ቦታ እጅግ ልዩ እንደሆነና መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡ ማንኛውም ነገር ንግግራችንን እንደሚያከብርና ለቃላችን እንደሚገዛ ኢየሱስ በዚህ ጥቅስ ላይ ያስተምራል፡፡ ንግግራችን ግን የእምነት ንግግር መሆን እንዳለበት መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡ የእምነት ንግግራችን ተራራን መንቀል የሚችል ጉልበት አለው፡፡
ንግግራችን ሁኔታችንን የመለወጥ ውጤት እንዳያመጣ የሚያደርገው የልብ ጥርጥር እንደሆነም ይነግረናል፡፡ ንግግራችን በልብ ጥርጥር ከሆነ አይሰራም፡፡ ቃላችን ግን በልብ በእምነትና ጥርጥር የሌለበት ከሆነ ንግግራችን ነገራችንን ይለውጣል፡፡ ነገራችን ቃላችንን ከመታዘዝ ውጭ ሌላ አማራጭ የለውም፡፡
ስለ ሁኔታችን የማንጠራጠረው ደግሞ እምነት ሲኖረን ነው፡፡ እምነት ደግሞ የሚመጣው የእግዚአብሄር ቃል ከመስማት ነው፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ሮሜ 10፡17
ስለምናገረውን ነገር እምነት የሚኖረን የእግዚአብሄር ቃል ስለሁኔታው ምን እንደሚል ፈልገን ስናገኝ ነው፡፡ ስለሁኔታችን ከእግዚአብሄር ቃል የእግዚአብሄርን ፈቃድ ካገኘን እምነት ይኖረናል፡፡ በእምነት የምንናገረው ነገር ደግሞ ሁኔታችንን ይለውጣል፡፡ ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Saturday, October 1, 2016

ህልሜን እየኖርኩት ነው

እግዚአብሄር ይመስገን ህልሜን እየኖርኩት ነው፡፡ ይህንን ንግግር ስናገር ሰዎች በአንድ አቅጣጫ ብቻ ስለሚመለከቱት ህልሜ ውስንና ትንሽ እንደሆነ ያስባሉ፡፡ ህልሜን እየኖርኩት ነው ስል ማለም እንዳቆምኩኝና ህልሜ ያለቀ ይመስላቸዋል፡፡ ህልሜን አየኖርኩት ነው ስል አንዳንዶች ተስፋ የቆረጥኩ ከዚህ በላይ ማየት ያቃተኝም ሁሉ ይመስላቸዋል፡፡
በፍፁም አይደለም፡፡ ህልሜን እየኖርኩት ነው ስል ምን ማለቴ እንደሆነ እኔ ነኝ የማውቀው፡፡
በመጀመሪያ ደረጃ አሁን ያለኝ ነገር ሁሉ የእኔ አይደለም፡፡ አሁን ያለኝ ነገር እኔጋ ስለቆየ የእኔ እንደሆነ አላስብም፡፡ አሁን ያለኝ ነገር ሁሉ ከእግዚአብሄር የተቀበልኩት ነው እንጂ የእኔ አይደለም፡፡
አንተ እንድትበልጥ ማን አድርጎሃል? ያልተቀበልኸውስ ምን አለህ? የተቀበልህ ከሆንህ ግን እንዳልተቀበልህ የምትመካ ስለ ምንድር ነው? 1ኛ ቆሮንቶስ 4፡7
ስለዚህ ህልሜን እየኖርኩት ነው ስል እግዚአብሄ ታማኝ አምላክ ነው እንደተራራ የከበደብኝን ነገር እርሱ ራሱ አድርጎልኛል ማለቴ ነው፡፡
በሁለተኛ ደረጃ አሁን የደረስኩበት ደረጃ ከአመታት በፊት ተራራ ሆኖብኝ የነበረ መንፈሳዊ ደረጃ ነው፡፡ አሁን ያለሁበት የአገልግሎት ደረጃ ላይ እንደምደርስ እኔን ለማሳመን እግዚአብሔር ብዙ ቃል መጠቀም ነበረበት፡፡ እግዚአብሄር ተስፋ ስቆርጥ አፅናንቶኛል፡፡ ህልሜን ለመጣል ስፈተን ይቻላል ይደረስበታል ብሎ አበረታቶኛል፡፡
ዳዊትን ከበግ እረኝነት ወደንግስና ያመጣው እግዚአብሄር ነው፡፡ ህልሙን እየኖረ እያለ እግዚአብሄር ከተጨማሪ ህልሞች ጋር ወደእርሱ ሲመጣ እግዚአብሄርን እየኖረ ስላለው ህልምና ሊፈፀም ስላለው ህልም አመሰገነ፡፡
ንጉሡ ዳዊትም ገባ፥ በእግዚአብሔርም ፊት ተቀምጦ እንዲህ አለ፦ ጌታዬ እግዚአብሔር ሆይ፥ እስከዚህ ያደረስኸኝ እኔ ማን ነኝ? 2ኛ ሳሙኤል 7፡18
ስለዚህ ነው ህልሜን እየኖርኩት ነው የምለው፡፡ በፊት ያልነበረኝ አሁን የደረስኩበት የህይወትና የአገልግሎት ደረጃ ሰላለ ነው ህልሜን እየኖርኩት ነው የምለው፡፡
ሶስተኛ እግዚአብሄር ስለዚህ ስለደረስኩበት ደረጃ ሊመሰገን ስለሚገባው ነው፡፡ ይህ ማለት ከአሁን በኋላ ምንም ህልም የለኝም ማለት ግን አይደለም፡፡ አንዳንድ ሰዎች እግዚአብሄርን ስለደረሱበት ማመስገን የማይፈልጉት ሌላ የሚፈልጉት ነገር የሌለ ይመስልብናል ብለው በማሰብ ነው፡፡ ህልምን መኖርና ሌላ ህልም ማለም አብረው የሚሄዱ እንዲያውም የአንዱ እምነት ለሌላው ምስክር የሚሆንበት እንጂ የሚቃረኑ አይደሉም፡፡
አሁንም ብዙ የሚፈፀሙ ህልሞች አሉኝ፡፡ ወደፊት የማያያቸው ብዙ ደረጃዎች አሉኝ፡፡ ብዙ የምደርስባቸው ግቦች አሉኝ፡፡ ልደርስባቸው የምዘረጋባቸው ህልሞች ከፊቴ አሉ ማለት ግን አሁን የምኖረውን ኑሮና የመንፈሳዊ ህይወት ደረጃ ስለደረስኩበትር ብቻ አጣጥለዋለሁ ማለት አይደለም፡፡ የወደፊት ህልም አለኝ ማለት አሁን ስለደረስኩበት ጌታን አላመሰግንም ማለት አይደለም፡፡ ወደፊት ህልም አለኝ ማለት በደረስኩበት ህልም አልደሰትም ማለት አይደለም፡፡
የአሁኑም የህይወቴ ደረጃ ፣ አሁን በክርስቶስ ያለኝ የነፃነት ደረጃ ፣ አሁን ያለኝ መንፈሳዊ አርነት ፣ አሁን ያለኝ የአገልግሎት ደረጃ አንድ ቀን የፀለይኩበት ፣ አንድ ቀን በእጅጉ የፈለኩት ፣ አንድ ቀን ያወጅኩትና አንድ ቀን እንደተራራ የሆነብኝ ደረጃ ነበር፡፡ ስለእናንተን አላውቅም እኔ ግን ህልሜን እየኖርኩት ነው፡፡ እግዚአብሄ ይመስገን፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #ህልም #ስምረት #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Tuesday, August 30, 2016

በህይወት ደስተኛ ለመሆን

አምስት ቀላል የደስታ እርምጃዎች | ቢሾፕ ቲዲ ጄክስ ስቲቭ ሃርቪ ብዙ ሰዎች ደስተኛ ለመሆን ምን ማድረግ አለብኝ ብለው ይጠይቃሉ ለሚለው ጥያቄ የሰጠው ምላሽ
1. ለደስተኝነት በሌላው ላይ አትደገፍ
በራስህ ደስተኛ የሚያደርግህን ነገር የመያዝ ሃላፊነቱ ያንተ ነው፡፡ ባለቤትህ ልጆችህ ያለህ ሃብት ደስታን ይሰጠኛል ብለህ ተስፋ አታድርግ፡፡ከምንም ጋር ባለተያያዘ መልኩ ደስተኛ ለመሆን በልብህ ወስን፡፡ ስለራስህ ደስታ ራስህ ሃላፊነቱን ውሰድ፡፡
2. ታሪክህን ፈትን
ሰዎች ራሳቸውን በተሳሳተ መልኩ በማየት ይሰቃያሉ፡፡ ራስህን የምታይበት ፡ ስለራስህ የምትናገርበትን መንገድና ስለራስን ያለህን እቅድ ተመልከትና ለውጥ፡፡ ህይወትህን መለወጥ አንደምትችል አስብ ተናገር፡፡ 3. በጉዞህ ተደሰት በህይወት ደስተኛ ለመሆን የሆነ ጊዜ አትጠብቅ አንዳንድ ሰዎች ሁልጊዜ ደስታቸውን ያስተላልፋሉ፡፡ ትምህርቴን ስጨርስ ፣ ሳገባ ፣ ልጅ ስወልድ በማለት አሁን ደስተኛ መሆን ያቅታቸዋል፡፡ ህይወት መዳረሻ ግብ አይደለም፡፡ ህይወት ጉዞ ነው፡፡ በጉዞህ እያንዳንዱ ደረጃና እርምጃ ሁሉ ተደሰትበት፡፡
4. ግንኙነትን አክብር
ተፈጥሮ እንደሚያስተምረን ያለግንኙነት ምንም ፍሬ የለም ካለግንኙነት ምንም ልታደርግ አትችልም፡፡ ካለግንኙነት ፍሬ በቤተሰብ በአገር በቤተክርስቲያን ፍሬ ልታፈራ አትችልም፡፡ ምንም ሁን ምን ካለህ ግንኙነት በላይ ልትሆን አትችልም፡፡ ስለዚህ መጀመሪያ ከእግዚአብሄር ጋር ላለህ ግንኙነት ትኩረት ስጥ፡፡ ከዚያም ከራስህ ጋር ባለህ ግንኙነት ራስህን ተቀበል ራስህን አክብር ውደድ፡፡ ራስህን ካላከበርክ እንድናከብርህ ከባድ ታደርግብናለህ፡፡
5. ስራንና መዝናናትን በሚዛናዊነት ያዛቸው
በህይወት በአንዱ ብቻ የተሳካልህ ልትሆን አትችልም፡፡ የሚሳካልህ ሁለቱንም በሚዛናዊነት የምትይዝ ከሆንክ ነው፡፡ ጠንክረህ ስራ ለመዝናናትም ትጋ፡፡ ስራ ብቻ የህይወትን ሃላፊነት የማይሸከሙት እጅግ ከባድ ያደርግብናል፡፡ ስለዚህ የስራህ ድካም በመዝናናት መካካስ አለበት፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakum...

Tuesday, June 28, 2016

ፈጣን ባለጠግነት

የታመነ ሰው እጅግ ይባረካል ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኵል ግን ሳይቀጣ አይቀርም። ምሳሌ 28፡20
እግዚአብሄር በልጆቹ ብልፅግና መሳካትና መከናወን ደስ ይለዋል፡፡ እግዚአብሄር ይባርካል፡፡ እግዚአብሄር በማንም መባረክና ማግኘት ላይ ተቃውሞ የለውም፡፡ እንዲያውም መፅሃፍ ደስም እንዲለን ሁሉን አትርፎ በሚሰጠን በሕያው እግዚአብሔር እንድንመካ ያስተምረናል፡፡ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡17 
የሰው ታማኝነት የሚታየው በአንድ ቀንና በአንድ ወር አይደለም፡፡ የሰው ታማኝነት የሚታየው በጊዜያት ውስጥ ነው፡፡ የታመነ ሰው በመታመን በቀጠለ መጠን ጥቂት በጥቂት እየጨመረ እየተባረከና እየበዛ ይሄዳል፡፡ 
እግዚአብሄር የራሱ እርምጃና ፍጥነት አለው፡፡ነገር ግን እግዚአብሄር በአንዴ አያሳድግም፡፡ 
ባለጠጋ ለመሆን መቸኮል ግን ችግር ነው፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነት የእግዚአብሄር እጅ የለበትም፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነት በፍፁም በንፅህና የሚመጣ አይደለም፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነትና ከእግዚአብሄር ውጭ የሚመጣ ነው፡፡ 
ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኩል ወይ ያጭበረብራል ወይ ይሰርቃል ወይ ይገድላል፡፡ ባለጠጋም ለመሆን ቸኩሎም ንፁህም መሆን አይቻልም፡፡ ባለጠጋ ለመሆን ቸኩሎም የእግዚአብሄርን በረከትንም ጠብቆም አይሆንም፡፡ 
ሰው ባለጠጋ ለመሆን ከቸኮለ የእግዚአብሄርን እርምጃ አልታገሰም ፡ እግዚአብሄርን በትግስት አልጠበቀም እንዲሁም የእግዚአብሄርን የበረከት መንገድ ትቶታል ማለት ነው፡፡ 
እግዚአብሄር የሚሰጠው ሃብት መሰረት ያለው ነው ሃዘንንም ከእርሱ ጋር አይጨምርም፡፡ 
የእግዚአብሔር በረከት ባለጠጋ ታደርጋለች፥ ኀዘንንም ከእርስዋ ጋር አይጨምርም። ምሳሌ 10፡22
በችኮላ የምትከማች ሃብት ግን የእግዚአብሄር እጅና ድጋፍ ስለሌለባት መሰረት እንደሌላት ቤት ነች፡፡ ተግንብታ ስታልቅ ከስርዋ ትናዳለች፡፡ 
በችኰላ የምትከማች ሀብት ትጐድላለች ጥቂት በጥቂት የተከማቸች ግን ትበዛለች። ምሳሌ 13፡11

ፈጣን ባለጠግነት

የታመነ ሰው እጅግ ይባረካል ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኵል ግን ሳይቀጣ አይቀርም። ምሳሌ 28፡20
እግዚአብሄር በልጆቹ ብልፅግና መሳካትና መከናወን ደስ ይለዋል፡፡ እግዚአብሄር ይባርካል፡፡ እግዚአብሄር በማንም መባረክና ማግኘት ላይ ተቃውሞ የለውም፡፡ እንዲያውም መፅሃፍ ደስም እንዲለን ሁሉን አትርፎ በሚሰጠን በሕያው እግዚአብሔር እንድንመካ ያስተምረናል፡፡ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡17 
የሰው ታማኝነት የሚታየው በአንድ ቀንና በአንድ ወር አይደለም፡፡ የሰው ታማኝነት የሚታየው በጊዜያት ውስጥ ነው፡፡ የታመነ ሰው በመታመን በቀጠለ መጠን ጥቂት በጥቂት እየጨመረ እየተባረከና እየበዛ ይሄዳል፡፡ 
እግዚአብሄር የራሱ እርምጃና ፍጥነት አለው፡፡ነገር ግን እግዚአብሄር በአንዴ አያሳድግም፡፡ 
ባለጠጋ ለመሆን መቸኮል ግን ችግር ነው፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነት የእግዚአብሄር እጅ የለበትም፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነት በፍፁም በንፅህና የሚመጣ አይደለም፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነትና ከእግዚአብሄር ውጭ የሚመጣ ነው፡፡ 
ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኩል ወይ ያጭበረብራል ወይ ይሰርቃል ወይ ይገድላል፡፡ ባለጠጋም ለመሆን ቸኩሎም ንፁህም መሆን አይቻልም፡፡ ባለጠጋ ለመሆን ቸኩሎም የእግዚአብሄርን በረከትንም ጠብቆም አይሆንም፡፡ 
ሰው ባለጠጋ ለመሆን ከቸኮለ የእግዚአብሄርን እርምጃ አልታገሰም ፡ እግዚአብሄርን በትግስት አልጠበቀም እንዲሁም የእግዚአብሄርን የበረከት መንገድ ትቶታል ማለት ነው፡፡ 
እግዚአብሄር የሚሰጠው ሃብት መሰረት ያለው ነው ሃዘንንም ከእርሱ ጋር አይጨምርም፡፡ 
የእግዚአብሔር በረከት ባለጠጋ ታደርጋለች፥ ኀዘንንም ከእርስዋ ጋር አይጨምርም። ምሳሌ 10፡22
በችኮላ የምትከማች ሃብት ግን የእግዚአብሄር እጅና ድጋፍ ስለሌለባት መሰረት እንደሌላት ቤት ነች፡፡ ተግንብታ ስታልቅ ከስርዋ ትናዳለች፡፡ 
በችኰላ የምትከማች ሀብት ትጐድላለች ጥቂት በጥቂት የተከማቸች ግን ትበዛለች። ምሳሌ 13፡11

Thursday, September 15, 2011

Learn to Enjoy life


Sometimes we think that one day we will be stress free and in that day


we will start enjoying life. No it isn't that way God designed it. you

are designed to enjoy life in devastation you find your self.

Go, eat your bread with joy, And drink your wine with a merry heart; For


God has already accepted your works. Let your garments always be white,

And let your head lack no oil. Live joyfully with the wife whom you love

all the days of your vain life which He has given you under the sun, all

your days of vanity; for that is your portion in life, and in the labor

which you perform under the sun. Ecclesiastic 9:7-9

I don't mean that it is OK to be pessimist who can't see bright future.

No we have a bright future. the things we long to see most are easy in

the sight of God.

What I mean is about enjoying life today and learning to enjoy life now.

Some of us lack the knowledge how to enjoy life now; we don't lack what

you want. We have to be careful how to use today and treat it properly.

We have to divide between today and tomorrow.

Matt 6:34 "Therefore do not worry about tomorrow, for tomorrow will

worry about its own things. Sufficient for the day is its own trouble.

Let’s not waste the now .let's enjoy today while waiting our hope of

tomorrow.
For more posts click More posts