I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ብዙ ጊዜ አመት ሲጠቀስ አብሮ ዓ.ም. ወይም አመተ ምህረት ተብሎ ይጠቀሳል፡፡ ይህ አመተ ምህረት የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ ሊሰቀል ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ያለውን ጊዜ ነው...
-
የብልጽግና ወንጌል ምሥጢር ሲገለጥ በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና። ወደ ሮሜ ሰዎች 1፡16 ወንጌል በሃጢያታቸው ምክኒያት ለዘላለም ከእ...
-
ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። 2 ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5 ፡ 17 የሰውን ማንነቱን ፣ ተፈጥሮውን ፣ ባህ...
-
ስለ ፍቅር ብዙ ይዘከራል ይወራል፡፡ ሁሉም ሰው ይህ የሚዘመርለትንና የሚሰበክለትን ፍቅር ማወቅ ፣ መኖር እና ማጣጣም ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን ወደ ተግባር ሲመጣ ፍቅር በተግባር ሊተረጎም የማይችል ረቂቅ ነገር ብቻ ይሆ...
-
ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡8 ፍቅር ዘላለማዊ ነው፡፡ ፍቅር የእግዚአብሄር ባህ...
-
ጸሎት ከእግዚአብሄር ጋር መነጋገር ነው። ጸሎት ሊደረግ የሚችለው ከእግዚአብሄር ጋር በመግባባት ብቻ ነው። ጸሎት የሚሰምረው እንደ እግዚአብሄር አሳብ ስንጸልይ ብቻ ነው። በአጠቃላይ ለእግዚአብሄር ያለን አመለካከት ...
-
We are created to be free moral beings. Man thinks before he decided to do something. He only does what he decided to do. For as he ...
-
Blessed are those who can say like Caleb “I am just as vigorous to go out to battle now as I was then”. I am still as strong today ...
-
እግዚአብሔር ሆይ እኔ ልቀየር የማልችላቸውን ነገሮች በዝምታ እንድቀበል ፀጋን ስጠኝ፡፡ እኔ መለወጥ የሚገባኝን ነገር ለመቀየር ድፍረት ስጠኝ፡፡ ልቀይር በምችላቸውና ልቀይር በማልችላቸው በሁለቱ ነገሮ...
-
ክርስትና ስር ነቀል የህይወት ለውጥ ነው፡፡ ክርስትና ጌታን መከተል ነው፡፡ ክርስትና ጌታ በቃሉ ያዘዘንን መፈፀም ነው፡፡ ጌታ በቃሉ የከለከለውን አለማድረግ ነው፡፡ ከሰሞኑ ዘፈን ሃጢያት ነው? አይደለም? የሚሉ ክር...
Monday, May 13, 2019
የደስተኝነት ምርጫ
በህይወት ደስተኛ መሆን የእድል ጉዳይ ሳይሆን የምርጫ ጉዳይ ነው:: ሰው ሁሉ ደስተኛ መሆን ይፈልጋል:: ነገር ግን ሰው ሁሉ ደስተኛ የሚያደርገውንነገር አይመርጥም:: እንዳንድ ሰው ደስተኛ ለመሆን ቢፈልግም ደስተኛ የሚያደርጉትን ሳይሆን ደስተኛ የማያደጉትን ነገሮች ስለሚመርጥ ደስተኛ ሳይሆን ጊዜውን ያባክናል::
ክፉ ሀዘን ጉልበትን ያደክማል:: ክፉ ሀዘን የኑሮ መነሳሳትን ይገድለዋል::
እርሱም፡— ሂዱ፥ የሰባውንም ብሉ፥ ጣፋጩንም ጠጡ፥ ለእነዚያም ላልተዘጋጀላቸው እድል ፈንታቸውን ስደዱ፤ ዛሬ ለጌታችን የተቀደሰ ቀን ነው፤ የእግዚአብሔርም ደስታ ኃይላችሁ ነውና አትዘኑ፡ አላቸው። መጽሐፈ ነህምያ 8:10
ደስተኝነት ለመኖር ለመስራትና ወደህይወት ግባችን ለመድረስ ጉልበት ይሰጠናል::
በህይወት ደስተኛ የማያደርገንን ነገሮች እስካልመረጥን ድረስ ደስተኛ መሆናችን አይቀርም::
ደስተኛ የማያደርጉ ሀሳቦች
1. ራስን ከሌላ ሰው ጋር ማፎካከር
ደስተኛ ላለመሆን አቋራጩ መንገድ በህይወት የተለያየ የህይወት አላማና ስጦታ ያላቸውን ሰዎች ለማወዳደርና ለማበላለጥ መሞከር ነው::
ራሳቸውን ከሚያመሰግኑ ከአንዳንዶች ጋር ራሳችንን ልንቆጥር ወይም ራሳችንን ልናስተያይ አንደፍርምና፤ ነገር ግን እነርሱ ራሳቸውን ከራሳቸው ጋር ሲያመዛዝኑ፥ ራሳቸውንም ከራሳቸው ጋር ሲያስተያዩ፥ አያስተውሉም። 2ኛ ቆሮንቶስ 10:12
2. ያለፈን ህይወት በፀፀት ለማስተካከል መሞከር
ያለፈ ህይወት አልፎዋል:: ስላለፈ ህይወት መፀፀት ዛሬን መግደል ነው:: ስላለፈ ህይወት መፀፀት ከዛሬ ትላንት ይሻል ነበር ብሎ ዛሬን ማናናቅ ነው::
3. የሌለን ነገር ላይ ማተኮር
የሌለን ነገር ላይ ማተኮር ያለንን ነገር በአግባቡ እንዳንጠቀምበት ያደርገናል:: የሌለን ነገር ላይ ማተኮር ያለንን እንዳናከብረውና እንዳንንቀው ያደርገናል:: የሌለን ነገር እንደማያስፈልገን ምንም ማረጋገጫ የለንም::
4. ያልደረስንበት ደረጃ ላይ ማተኮር
ሁላችንም ህልሞች አሉን:: ነገር ግን አሁን አንዳንዱ ህልማችን እውን ሆኖ እየኖርነው አይደለም ማለት አይደለም:: ከዚህ በፊት ምንም ሆኖልን እንደማያውቅ ምንም አከናውነን እንደማናውቅ የነገ ግባችን ላይ ከመጠን በላይ ማተኮር ደስተኛ ላለመሆን መምረጥ ነው::
5. ከጌታ ውጭ ማተኮር
ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሄርና ከእግዚአብሄር ጋር እንዲኖር ነው:: ሰው ግን እግዚአብሄርን ካላሰበ ደስተኛ መሆን ያቅተዋል:: ብዙ ደስ የማያሰኙ ነገሮች በዙሪያችን እያሉ በጌታ ደስ መሰኘት ይቻላል::
ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ። ወደ ፊልጵስዩስ 4:4
Subscribe to:
Posts (Atom)