I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና . . . ማቴዎስ 28፡18 በመጀመሪያ ሰው ከሙሉ ስልጣን ጋር ተፈጥሮ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ ...
-
ኢየሱስ ወደምድር የመጣው በስጋ ነው፡፡ ኢየሱስ የመጣው ከሰው ልጅ ተወልዶ ሰው ሆኖ ነው፡፡ ኢየሱስ ሰው ሆኖ የመጣው በሰው የተሰራውን ሃጢያት በሰውነት ለመክፈል ነው፡፡ እንግዲህ በአንድ በደል ምክንያት ፍ...
-
የፈጠረን እግዚአብሄር ሁለንተናችንን ያውቃል፡፡ እግዚአብሄር በውጫዊ ነገራችን አይወሰድም፡፡ እግዚአብሄር ፊትን አያየም፡፡ እግዚአብሄር የፊትን መልክ አይቶ አይሳብም፡፡ እግዚአብሄር ቁመናችንን አይቶ አይደነቅም፡፡...
-
የማቴዎስ ወንጌል 22:1-14 1 ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ፦ 2 መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች። 3 የታደሙትንም ወደ ሰር...
-
People are devoted to get the right recipe for success. They study life and people diligently. They come up with many tactics and strat...
-
ከከንቱ ኑሮአችንም የተገዛነው እና የተዋጀነው በክርስቶስ ደም ነው፡፡ ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክ...
-
ብዙ ሰዎች አንደኛ መሆን ይፈልጋሉ፡፡ አንደኛ መሆን ምንም ጥፋተኛ የለበትም፡፡ ኢየሱስ ፊተኛ መሆን የሚፈልግህ ንስሃ ይግባ አይደለም ያለው፡፡ ፊተኛ የሚሆንበትን መንገዱን ነው እንጂ ያሳየው በፍፁም አልገሰፀም፡፡ አን...
-
ዕብራውያን 11 ፡ 1-40 እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው። ለሽማግሌዎች የተመሰከረላቸው በዚህ ነውና። ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እ...
-
እንዲሁም፥ እናንተ ሚስቶች ሆይ፥ ከባሎቻችሁ አንዳንዱ ለትምህርት የማይታዘዙ ቢኖሩ፥ በፍርሃት ያለውን ንጹሑን ኑሮአችሁን እየተመለከቱ ያለ ትምህርት በሚስቶቻቸው ኑሮ እንዲገኙ ተገዙላቸው። ...
Thursday, April 29, 2021
Wednesday, April 28, 2021
Wednesday, April 21, 2021
የልጅነት ስልጣን ክፍል ሁለት
\ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ የዮሐንስ ወንጌል 1፡12
እንዲህም አላቸው ሰይጣንን
እንደ መብረቅ
ከሰማይ ሲወድቅ
አየሁ። እነሆ፥
እባቡንና ጊንጡን
ትረግጡ ዘንድ፥
በጠላትም ኃይል
ሁሉ ላይ
ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ፥
የሚጐዳችሁም ምንም
የለም። የሉቃስ
ወንጌል 10፡18-19
ክርስቶስ ኢየሱስን አንደ አዳኝና ጌታችን የተቀበልን
ሁላችን ከጨለማው ግዛት ድነን ወደፍቅሩ ልጅ መንግስት ተሻግረናል፡፡
እርሱ
ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን። ወደ ቆላስይስ ሰዎች 1፡13-14
ሰይጣን ደግሞ እንደገና በባርነት ውስጥ ሊከተን
ይጥራል፡፡ በሰይጣን ጥቃት ውስጥ ላለመውደቅ ሰይጣንን አጥብቀን መቃወም ይኖርብናል፡፡
መስረቅ ማረድና ማጥፋት ብቸኛው የሆነው ሰይጣን
ዲያቢሎስን በልጅነት ስልጣናችን በቀጣይነት ልንቃወመው ይገባል፡፡
የልጅነት ስልጣናችንን ተጠቅመን ከእኛና እግዚአብሄር
የእኛ ከሆኑት ነገሮች ሁሉ ላይ ካልተቃወምነው እርሱ ራሱ አውቆ ይሄዳል ብለን መጠበቅ ሞኝነት ነው፡፡
በህይወታችን ለእግዚአብሄር በመገዛት ዲያቢሎስን
ከህይወታችን ከአገልግሎታችን ሁሉ መቃወም ግድ ይላል፡፡
እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ የያዕቆብ መልእክት 4፡7
ሰይጣን በክርስቶስ የመስቀል ላይ ስራ የተሸነፈ
ጠላት በመሆኑ በሚገባ ስንቃወምው መሸሽ አንጂ ሌላ ምንም እድል የለውም፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/
ለቪዲዮ መልእክቶች
https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ስልጣን #ስልጣን #መቀመጥ
#ሰማያዊ #በክርስቶስ
#በጌታ #እምነት
#መደገፍ #ሰንበት
#በመንፈሴ #በሃይል
#በብርታት #ፀጥታ
#መመለስ #ማረፍ
#ፅድቁን #ኢየሱስ
#ክርስቶስ #ጌታ
#ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ፀጥታ #መፅሃፍቅዱስ
#መንፈስቅዱስ #መታመን
#ፌስቡክ #አቢይዋቁማ
#አቢይዋቁማዲንሳ
Tuesday, April 20, 2021
የልጅነት ስልጣን ክፍል አንድ
የልጅነት ስልጣን ክፍል አንድ
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ የዮሐንስ ወንጌል 1፡12
እንዲህም አላቸው ሰይጣንን እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ አየሁ። እነሆ፥ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ፥ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ፥ የሚጐዳችሁም ምንም የለም። የሉቃስ ወንጌል 10፡18-19
የሰው ልጅ በእግዚአብሄር መልክና አምሳል የተፈጠረው እንዲገዛ ነበር፡፡
እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ። ኦሪት ዘፍጥረት 1፡26
ሰው ይገዛ የነበረው ለእግዚአብሄር በመገዛት ስለነበረ ሰው ለእግዚአብሄር መገዛት ሲያቆም እና በሃጢያት በእግዚአብሄር ላይ ሲያምፅ ከእግዚአብሄር ጋር የነበረውን የልጅነት የመግዛት ስልጣኑን አጣው፡፡
ሰው በሃጢያት ምክኒያት ከእግዚአብሄር ስለተለያየ በሃጢያት በሚመላለስበት ጊዜ ሁሉ በሰይጣን ስልጣን ስር ወደቀ፡፡ በዚህ ምክኒያት ሰይጣን በእግዚአብሄር ላይ ባመፁ ልጆች ሁሉ ላይ ስልጣን ነበረው፡፡
በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም፥ በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፡1-2
የጠላት ዲያቢሎስ ስራ ደግሞ መስረቅ ማረድና ማጥፋት ብቻ ነው፡፡
ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። የዮሐንስ ወንጌል 10፡10
ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ ወደምድር የመጣው የዲያቢሎስን ስራ ለማፍረስ ነው፡፡
ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 3፡9
ክርስቶስ ኢየሱስ ሰይጣንን በመስቀል ላይ አሸንፎታል፡፡
አለቅነትንና ሥልጣናትን ገፎ፥ ድል በመንሣት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሳያቸው። ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2፡15
ኢየሱስ ሰይጣንን በመስቀል ላይ ያሸነፈው ለራሱ አይደለም፡፡ ኢየሱስ ሰይጣንን በመስቀል ላይ ያሸነፈው እኛን ወክሎ በእኛ ፋንታ ለእኛ ነው፡፡
ክርስቶስ ኢየሱስን የተቀበልን ሁላችንን ከሰይጣን ስልጣን ድነናል፡፡
እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን። ወደ ቆላስይስ ሰዎች 1፡13-14
ኢየሱስ ክርስቶስን እንደአዳኙና ጌታው የተቀበለ ሰው ሁሉ የእግዚአብሄር ልጅነት ስልጣን አለው፡፡ ከእግዚአብሄር የተወለደ ሁሉ አለምን የሚያሸንፍበት ስልጣንን ተቀብሎዋል፡፡
እንዲህም አላቸው ሰይጣንን እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ አየሁ። እነሆ፥ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ፥ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ፥ የሚጐዳችሁም ምንም የለም። የሉቃስ ወንጌል 10፡18-19
እግዚአብሄር በጠላት ምድር ላይ ክርስቶስን እንድንከተል እና በምድር ላይ እንድናገለግለው ሲያዘን ካለስልጣን አይደለም፡፡ የምንኖረው ሰይጣን አስኮናኞች ኑሩ ብሎ ስለፈቀደልን አይደለም፡፡ የምንኖረው በሰይጣን ችሮታና ምህረት አይደለም፡፡ ሰይጣን ወደደም ጠላም የምንንኖረው በስልጣን ነው፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ስልጣን #ስልጣን #መቀመጥ #ሰማያዊ #በክርስቶስ #በጌታ #እምነት #መደገፍ #ሰንበት #በመንፈሴ #በሃይል #በብርታት #ፀጥታ #መመለስ #ማረፍ #ፅድቁን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ፀጥታ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መታመን #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ