Popular Posts

Wednesday, May 23, 2018

ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት

እነርሱንም ባይሰማ፥ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፥ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ። ማቴዎስ 18፡17
የእግዚአብሄር ቃል ከጊዜ ጋር አይለወጥም፡፡ የእግዚአብሄር ቃል እንደዘመኑ አይለዋወጠም፡፡ የእግዚአብሄር ቃል በዘመናት የፀና ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል አያረጅም፡፡ የእግዚአብሄር ቃል አያልፍም፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ከሚያልፍ ሰማይና ምድር ቢያልፉ ይቀላል፡፡
የእግዚአብሄር ቃል ስለቤተክርስያን የሚለውን ማወቅ ከብዙ ስህተት ያድናል፡፡
ሰውን ክርስትያን አይደለህም እስከማለት ትልቅ ስልጣን ያላት ቤተክርስትያን ብቻ ነች፡፡ ቤተክርስትያን በምድር ላይ የእግዚአብሄርን መንግስት የምትወክል እንደ መሆንዋ መጠን በመሪዎችዋ አማካኝነት የምታስተላልፈው ውሳኔ የፀና ነው፡፡ 
ቤተክርስትያን በምድር የእግዚአብሄር መንግስት ተወካይ ነች፡፡ ቤተክርስታን የምትኖረው በክርስቶ ኢየሱስ ሙሉ ክብር ነው፡፡ ቤተክርስትያን ያላት ስልጣን ራስዋ ኢየሱስ ያው ስልጣን ነው፡፡
ኢየሱስ በምድር ላይ ስልጣኑን የሚለማመደው በቤተክርስትያን በኩል ነው፡፡
ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛለት ከሁሉ በላይም ራስ እንዲሆን ለቤተ ክርስቲያን ሰጠው። እርስዋም አካሉና ሁሉን በሁሉ የሚሞላ የእርሱ ሙላቱ ናት። ኤፌሶን ሰዎች 1፡22-23
ቤተክርስትያን በምድር የምታስረው በሰማይ የታሰረ ይሆናል፡፡ ቤተክርስትያን በምድር የምትፈታው በሰማይ የተፈታ ይሆናል፡፡
እውነት እላችኋለሁ፥ በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል። ማቴዎስ 18፡18
ቤተክርስትያን ጉባኤ ወይም በተወካይ መሪዎችዋ በኩል የምትወስነውን ውሳኔ እግዚአብሄር ይፈፅመዋል፡፡
እኔ ምንም እንኳ በሥጋ ከእናንተ ጋር ባልሆን፥ በመንፈስ ከእናንተ ጋር ነኝ፥ ከእናንተም ጋር እንዳለሁ ሆኜ ይህን እንደዚህ በሠራው ላይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሁን ፈርጄበታለሁ፤ እናንተና መንፈሴም ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን፥ መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው። 1ኛ ቆሮንቶስ 5፡3-5
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #መሪ #ሽማግሌ #ሰይጣን #ፍርድ #ውሳኔ #በምድርየምታስሩት #በሰማይየታሰረ #በምድርምየምትፈቱት #በሰማይየተፈታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት

No comments:

Post a Comment