Popular Posts

Sunday, May 31, 2020

የነፍስ ብቻ ሳይሆን የስጋ ፈውስ ያስፈልገናል




ስለዚህ ወደ ዓለም ሲገባ፦ መሥዋዕትንና መባን አልወደድህም ሥጋን ግን አዘጋጀህልኝ፤ ወደ ዕብራውያን 10፡5
በመድር ላይ ለመኖር ለመንቀሳቀስ ለመውጣትና ለመግባት ስጋ ያስፈልጋል፡፡ ኢየሱስ እኛን ከሃጢያት የማዳን ስራ ለመስራት ስጋ አስፈልጎት ነበር፡፡
ኢየሱስ ምንም ሙሉ መንፈሳዊነት ቢኖረው በስጋ ውስጥ ባይኖር ኖሮ ግን የማዳንን አላማ ማስፈፀም አይችልም ነበር፡፡
የነፍስ መዳን በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ በምድር ላይ የምንፈፅመው የተለየ አላማ ባይኖረን ኖሮ ነፍሳችን እንደዳነ ወዲያው ወደጌታ እንወሰድ ነበር፡፡
እግዚአብሄር በምድር ላይ እንድንፈፅም የሰጠንን ራእይና አላማ ለመፈፀም ደግሞ በምድር ላይ መኖር አለብን፡፡ በጠንካራ እና በጤነኛ አካል በምድር ላይ ካልኖርን እና ሰይጣን በፈለገው ጊዜ የፈለገውን በሽታ የሚያደርግብን ከሆነ የእግዚአብሄርን ፈቃድ መፈጸም ያቅተናል፡፡
እነሆም፥ ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባት ሴት ነበረች፥ እርስዋም ጐባጣ ነበረች ቀንታም ልትቆም ከቶ አልተቻላትም። ኢየሱስም ባያት ጊዜ ጠራትና። አንቺ ሴት፥ ከድካምሽ ተፈትተሻል አላት፥ እጁንም ጫነባት፤ ያን ጊዜም ቀጥ አለች፥ እግዚአብሔርንም አመሰገነች። ይህችም የአብርሃም ልጅ ሆና ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ ሰይጣን ያሰራት በሰንበት ቀን ከዚህ እስራት ልትፈታ አይገባምን? አለው። የሉቃስ ወንጌል 13፡11-13፣16
እግዚአብሄር በክርስቶስ በኩል የነፍሳችንን መዳኛ መንገድ ብቻ ፈጽሞ ቢሄድ ሰይጣን በስጋችን ላይ የፈለገውን ቢያደርግ የእግዚአብሄርን ፈቃድ በምድር ላይ መፈፀም እንችልም ነበር፡፡
እግዚአብሄር ግን ለነፍሳችን ብቻ ሳይሆን ነፍሳችን ስለሚኖርበት ስለስጋችን ሙሉ ዋጋን ከፍሏል፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ በመገረፉ ቁስል እንደተፈወስን የሚናገረው በምድር ላይ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለመፈፀም የነፍሳችን መዳን ብቻ ሳይሆን የስጋችን ብርታት አስፈላጊ ስለሆነ ነው፡፡    
ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2፡24
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ጊዜ ስለሰዎች ነፍስ መዳን መስበክ ብቻ ሳይሆን ስለስጋቸውም ፈውስ በትጋት እና በቅናት ይፀልይ የነበረው ስለዚህ ነው፡፡
እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤ የሐዋርያት ሥራ 10፡38
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Tuesday, May 26, 2020

ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 53

ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 53
1፤ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል?
2፤ በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።
3፤ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።
4፤ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው።
5፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
6፤ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።
7፤ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።
8፤ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?
9፤ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገንበትም ነበር።
10፤ እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈከደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።
11፤ ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሰከማል።
12፤ ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና፤ እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።

Monday, May 25, 2020

የደስታ ያለህ

ክርስቲያናዊ ደስታን አፈላለግ በሚቀጥሉት አምስት እምነቶች ላይ የተገነባ የህይወት መረዳት ነው፡፡

l. ደስተኛ ለመሆን መጓጓት አለም አቀፋዊ ሁለንተናዊ የሰዎች ምኞት ነው፡፡ ደስተኛ ለመሆን የመመኘት ልምምድ መልካም እና ምንም ክፋት የሌለበት ነገር ነው፡፡

2. መጥፎ ስሜት ይመስል ደስተኛ የመሆን ምኞታችንን ለመካድ ወይም ለመቃወም በፍጹም መሞከር የለብንም፡፡ ይልቁን ጥልቅ እና በጣም ዘላቂ እርካታን ለማግኘት ይህንን ምኞት ማጠንከር እና ማዳበር አለብን፡፡

3. እጅግ ጥልቅ እና ዘላቂ ደስታ የሚገኘው በእግዚአብሄር ውስጥ ብቻ ነው፡፡

4. በእግዚአብሔር የምናገኘው ደስታ ከሌሎች ጋር በፍቅር ሲጋራ ወደ ደስታ ፍጻሜ ይደርሳል፡፡

5. የራሳችንን ደስታ ለማሳደድን እስከሞከርን ጊዜ ድረስ ግን እግዚአብሄርን ማክበርና ሰውን መውደድ ያቅተናል፡፡ 

በሌላ አነጋገር የሰው ልጅ ዋናው ፍፃሜ በእግዚአብሄር ለዘላለም ደስ በመሰኘት እርሱን ማክበር ነው፡፡ 

From the Book Desiring God by John Piper Page 16.


Wednesday, May 13, 2020

ስጡ


ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል። የሉቃስ ወንጌል 638

ይህ የኢየሱስ ንግግር ስለመስጠት እንጂ ስለ መቀበል የተደረገ ንግግር አይደለም፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ይህን ክፍል ስለመቀበል ይሰብኩታል፡፡ የዚህ የመስጠት ትምህርት አላማ ግን መስጠት እንጂ በፍፁም መቀበል አይደለም፡፡

ሰው ሲሰጥ ወደ አእምሮው የሚመጣ ጥያቄ አለ፡፡ ስሰጥ እኔስ ቢጎድልብኝ የሚል ጥያቄ በሁላችንም አእምሮ ውስጥ ይመላለሳል፡፡

ሰጥቼ እኔስ ቢጎድልብኝ የሚለው ጥያቄ የሚፈጠርብን ምክኒያት ገንዘብ ጊዜያዊም ቢሆን የመተማመን ስሜትን ስለሚሰጠን ነው፡፡  

በአጠቃላይ አለምን የሚያንቀሳቅሰው የእግዚአብሄር ፍቅር ወይም የገንዘብ ማጣት ፍርሃት ነው፡፡ ሰው እንዳያጣ ብዙ ነገሮችን ያደርጋል፡፡

እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። የማቴዎስ ወንጌል 6፡31-32

ሰው ገንዘቡን ለመስጠት የሚገዳደረው ምክኒያት ገንዘብ የመተማመን ስሜትን በሰው ውስጥ ስለሚፈጥር ነው፡፡  

ታዲያ ገንዘባችንን ስንሰጥ የምንሰጠው መተማመኛችንን ነው፡፡ ገንዘባችንን ለመስጠት ከገንዘብ በላይ የምንተማመንበት እግዚአብሄርን ማመን ይጠይቃል፡፡ ገንዘብ ለመስጠት ከሚታየው ያለፈ የእግዚአብሄርን መንግስት አሰራር በእምነት አይን ማየት ይጠይቃል፡፡ ገንዘብን ለመስጠት የእግዚአብሄርን ቃል ማመን ይጠይቃል፡፡  

ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱም የምትዘሩትን ዘር ይሰጣችኋል ያበረክትላችሁማል፥ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያሳድጋል፤ 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡10

ስጡ ብሎ ኢየሱስ ይሰጣችኋል ያለበት ምክኒያት በሰው ውስጥ የሚነሳውን ሰጥቼ ቢጎድልብኝስ? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ነው፡፡ ስጡ ብሎ መልሱ ባጣስ ለሚለው ጥያቄ መልሱ ስለሰጣችሁ አይጎድልባችሁም የሚለው ነው፡፡ ስለሰጣችሁ አታጡም ስለሰጣችሁ አትከስሩም፡፡

ይህንም እላለሁ፦ በጥቂት የሚዘራ በጥቂት ደግሞ ያጭዳል፥ በበረከትም የሚዘራ በበረከት ደግሞ ያጭዳል። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡6

ስትሰጡ ይሰጣችሁዋል፡፡ ስትሰጡ ይጨመርላችሁዋል፡፡ ስትሰጡ ይበልጥ ይሰጣችሁዋል፡፡

ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል። የሉቃስ ወንጌል 6፡38

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እረፍት #ቅድሚያ #እምነት #መደገፍ #ሰንበት #መዝራት #ማጨድ #ፅድቁን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ምህረት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ


Thursday, May 7, 2020

Blessed


Blessed are those who can say like Caleb “I am just as vigorous to go out to battle now as I was then”.

I am still as strong today as the day Moses sent me out; I am just as vigorous to go out to battle now as I was then. Joshua 14:11

Caleb is a good example of perseverance. He is a good example of not giving up. He is a good example of not being affected by different life situations.

He has seen in the lows and the highs. He has seen the yes's and the no's. He has seen success and failure. He has seen progress and setbacks.

Those life situations were not good enough to make him quit. He just continued.

All the life situations were not good excuses to give up.

Instead, all life situations taught him that they don't really matter. The more he passes through the life situations he came across, he could put them in their right places.

I know what it is to be in need, and I know what it is to have plenty. I have learned the secret of being content in any and every situation, whether well-fed or hungry, whether living in plenty or in want. Philippians 4:12

Instead of all the life challenges makes him loses his passion to achieve more. They taught him that the only thing that matters is God himself.

Blessed are those who can say like Caleb “I am just as vigorous to go out to battle now as I was then”.
Abiy Wakuma Dinsa
For More Articles https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
#God #Jesus #knowledge #rejoice # perseverance #trustgod #grace #salvation #church #testimony #rejoice #preaching #Bible #theword #Abiydinsa #scriptures #abiywakumadinsa