Popular Posts

Sunday, October 2, 2022

ርህራሔ የሌለበት የኢሬቻ አስተያየት

 

ርህራሔ የሌለበት የኢሬቻ አስተያየት
ሰሞኑን የኢሬቻ በአል እየተከበረ ይገኛል:: ስለ ኢሬቻ በአል ብዙ አይነት አስተያየቶችን ሰምቻለሁ እንብቤያለው::
አንድ የታዘብኩት ነገር ግን የኢሬቻን በአል ተቃውመው የሚናገሩ አንዳንድ ሰዎች ፍቅርና ትህትና በጎደለው ሁኔታ የበአሉን ታዳሚዎች ሲወቅሱ ማየቴ ነው፡፡  
በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:15
የበፊቱን አላውቅም በአሁኑ ዘመን ከማየው ስነሳ የኢሬቻ በአል ከሀይማኖትነቱ ይልቅ ብሔራዊ ባህልነቱ ያመዝንብኛ፡፡ 
ሀይማኖት ቢኖረንም ባህልም ያለን ባህላዊ ሰዎች ነን:: ሃይማኖትን በማይነካ መልኩ የምናስተናግዳቸው ብዙ ባህሎች አሉን፡፡ ባህል በሃይማኖታችን ላይ ምንም ያህል ተፅእኖ እንዳያደርግ እና የሀይማኖት ህይወታችንን እንዳያዘገይ ወይም እንዳያቆም በኑሮዋችን መጠንቀቅ የእለት ተእለት ሃላፊነታችን ነው:: 
ማንኛውም ባህል እምነታችንን የሚቃወም ከሆነ የትኛውንም ባህል አውጥተን እንጥላለን እንተወዋለን:: ስለ እምነታችን ከእግዚአሔር ቃል ጋር ከማይሄድውን ባህላችንን በደስታ እንተዋለን:: 
እኔን በተመለከተ ስለሀጢያቴ በመስቀል ላይ የሞተውን ሞትን ድል አድርጎ በሶስተኛው ቀን የተነሳውን ኢየሱን ክርስቶስን አዳኝና ጌታ አድርጌ እከተላለው:: ኢየሱስን ለማይከተል ሰው ከዚህ ታላቅ በረከት ስለጎደለ በቅንነት አዝንለታለሁ:: 
ነገር ግን የኢሬቻን በአል በሚያከብር ሰው ላይ ላለመፍረድ እጠነቀቃለው:: የምናገረው ንግግር የዋህነትና ትህትናን ካጣ ከጥቅሙ በላይ ጉዳቱ ያመዝናል:: በፍቅር ያልተደረገ ነገር ከንቱ ነው ምንም አይጠቅምም:: 
በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ። ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል፥ ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም። 1ኛ ቆሮንጦስ 13:1-3 
የማንወደውን ሰው ልናገለግለው እንችልም:: እንደ እግዚአብሔር ቃል ያልሆነ ባህል እምነታችንን እንዳይጎዳ መጠንቀቅ ፣ ሌሎችን በየዋህነት እና በትህትና መምከር እንጂ ርህራሔ ያጣ አስተያየት መስጠት ምንም ለምንም አይጠቅምም::
 በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:15
አቢይ ዋቁማዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


Saturday, October 1, 2022

የአዲሱ ኪዳን ፀሎት ትኩረት

 

ክርስቶስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ ከሞተ እና በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳ በኋላ የምንኖርበት ኪዳን በኢየሱስ የተደረገው አዲስ ኪዳን ነው፡፡

ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት በሃጢያታችን ምክኒያት ከእግዚአብሄር ጋር ጠላቶች ነበርን፡፡ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ስለሃጢያታችን በመሞት ከእግዚአብሄር ጋር አስታርቆናል፡፡ አሁን ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም ነን፡፡

ኢየሱስ በመስቀል ላይ በመሞት በብሉይ ኪዳን ለጥቂት ለተመረጡ ሰዎች ይሰጥ የነበረውንም መንፈስ ቅዱስን እርሱን ለተቀበልን ለሁላችንም እንዲሰጠን እና መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን አንዲኖር አስችሎናል፡፡

ከእግዚአብሄር ጋር ጥል በነበሩበትና በክርስቶስ ደም ባልታረቁበት ጊዜ የሚፀለየውን ፀሎቶች በዚህ በአዲሱ ኪዳን ብንፀልይ ውጤታማ አንሆንም፡፡

በአዲሱ ኪዳን የተፀለየውን አንዱን ፀሎት ለምሳሌ ብንወስድ ፀሎቱ የሚያተኩረው ክርስቶስ በመስቀል ላይ የሰራልንን ስራ በመረዳት ላይ ነው፡፡

የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19

ይህ አይነቱን ፀሎት ፍሬያማ የሚያደርገው በመስቀል ላይ የተሰራውን ስራ እውቅና መስጠቱ ነው፡፡ እንዲሁም ይህን ተሰርቶ የተጠናቀቀውን ስራ በሚገባ እንድንረዳ አይናችን እንዲከፈት እግዚአብሄርን መለመኑ ነው፡፡ እንደዚህ አይነቱ የአዲስ ኪዳን ፀሎት እግዚአብሄርን በማወቅ የጥበብ እና የመገለጥ መንፈስ እንዲሰጠን ይጠይቃል፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa  


 

አእምሮን የሚያልፍ
በእርሱ ከታመንን ከአካባቢያችን ጩኽትና ረብሻ ከፍ ያለ አእምሮን የሚያልፍ ሰላም እንደምናገኝ መፅሀፍ ቅዱስ ይናገራል:: ህይወታችን ሁልጊዜ ጥርት ያለ ቀጥታ መስመር እይደለም:: በህይወታችን ያለውን ነገር ሁሉ አንረዳውም:: ህይወታችን በአእምሮ መርምረን የምንጨርሰው አይደለም:: አእምሮን የሚያልፍ ሰላም ልባችንንና አሳባችንን
መጠበቅ ያለበት ህይወታችን ሁሉንም ጠንቅቀን ከምንረዳው በላይ አእምሮን  የሚያልፍ በመሆኑ ነው:: 
አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።  ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች  4:7
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa