I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
እነሆ፥ እኔና እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች ለእስራኤል በጽዮን ተራራ ከሚኖረው ከሠራዊት ጌታ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምልክትና ተአምራት ነን። ኢሳያስ 8፡18 ለእግዚአብሄር ክብር ተፈጥረናል፡፡ የእ...
-
እኛ የተፈጠርነው ለእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡ የተፈጠርነው ሌሎችን ለማገልገል ነው፡፡ ገንዘብን መስጠት ገንዘብን እንደመስራት በጣም ወሳኝ የሆነ ልምምድ ነው፡፡ እግዚአብሄር የሚሰጠን ገንዘብ የምንበላውና የምንዘራው ...
-
ምስክርነት በህይወታችን የቀመስነውን የኢየሱስ ክርስቶስን ነፃነት ለሌሎች የምናካፍልበት መንገድ ነው፡፡ ምስክርነት እጅግ ታላቅ ሃይል ያለው ስራ ነው፡፡ ምስክርነት ወይም ወንጌልን መስበክ ምን እንደሆነ ከመፅሃፍ ቅዱስ ...
-
እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ። 1ኛ ጢሞቴዎስ 3፡16...
-
ንጉሥሽ ሕፃን የሆነ፥ መኳንንቶችሽም ማልደው የሚበሉ፥ አንቺ አገር ሆይ፥ ወዮልሽ ! ንጉሥሽ የከበረ ልጅ የሆነ፥ ለብርታት እንጂ ለስካር ያይደለ በጊዜ የሚበሉ መኳንንት ያሉሽ፥ አንቺ አ...
-
የተፈጠርነውና በምድር ያለነው ለእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡ በምድር ያለነው ያለንበት ዋነኛው ምክኒያት ለመብላት ለመጠጣትና ለመልበስ አይደለም፡፡ በምድር ያለነው የእግዚአብሄርን ስራ ለመስራት ነው ፡፡ በምድር ያለነው ስ...
-
የሆነው ነገር እርሱ የሚሆን ነው፥ የተደረገውም ነገር እርሱ የሚደረግ ነው፤ ከፀሐይም በታች አዲስ ነገር የለም። መክብብ 1፡9 በምድር ላይ ቢሆንልኝ ብለን እጅግ ስንመኘው የነበረ ስናገኘው ለ...
-
አዲሱን አመት በእውነት አዲስ የሚያደርገው በአዲሱ የእግዚአብሔር በተሰብ ውስጥ መሆናችን ነው። ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ አዳኝ ካልተቀበልን በስተቀር የእግዚአብሔር ልጆች መሆን በፍጹም አንችልም። እውነት ነው ሰይጣን የፈጠር...
Wednesday, October 12, 2022
Sunday, October 2, 2022
ርህራሔ የሌለበት የኢሬቻ አስተያየት
የአዲሱ ኪዳን ፀሎት ትኩረት
ክርስቶስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ ከሞተ እና በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳ በኋላ የምንኖርበት ኪዳን በኢየሱስ የተደረገው አዲስ ኪዳን ነው፡፡
ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት በሃጢያታችን ምክኒያት
ከእግዚአብሄር ጋር ጠላቶች ነበርን፡፡ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ስለሃጢያታችን በመሞት ከእግዚአብሄር ጋር አስታርቆናል፡፡ አሁን ከእግዚአብሔር
ጋር ሰላም ነን፡፡
ኢየሱስ በመስቀል ላይ በመሞት በብሉይ ኪዳን ለጥቂት
ለተመረጡ ሰዎች ይሰጥ የነበረውንም መንፈስ ቅዱስን እርሱን ለተቀበልን ለሁላችንም እንዲሰጠን እና መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን አንዲኖር
አስችሎናል፡፡
ከእግዚአብሄር ጋር ጥል በነበሩበትና በክርስቶስ
ደም ባልታረቁበት ጊዜ የሚፀለየውን ፀሎቶች በዚህ በአዲሱ ኪዳን ብንፀልይ ውጤታማ አንሆንም፡፡
በአዲሱ ኪዳን የተፀለየውን አንዱን ፀሎት ለምሳሌ
ብንወስድ ፀሎቱ የሚያተኩረው ክርስቶስ በመስቀል ላይ የሰራልንን ስራ በመረዳት ላይ ነው፡፡
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19
ይህ አይነቱን ፀሎት ፍሬያማ የሚያደርገው በመስቀል
ላይ የተሰራውን ስራ እውቅና መስጠቱ ነው፡፡ እንዲሁም ይህን ተሰርቶ የተጠናቀቀውን ስራ በሚገባ እንድንረዳ አይናችን እንዲከፈት
እግዚአብሄርን መለመኑ ነው፡፡ እንደዚህ አይነቱ የአዲስ ኪዳን ፀሎት እግዚአብሄርን በማወቅ የጥበብ እና የመገለጥ መንፈስ እንዲሰጠን
ይጠይቃል፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma
Dinsa
Saturday, October 1, 2022



