Popular Posts

Thursday, May 3, 2018

እምነቱም እግዚአብሔር የሆነ

በእግዚአብሔር የታመነ እምነቱም እግዚአብሔር የሆነ ሰው ቡሩክ ነው። በውኃ አጠገብ እንደ ተተከለ፥ በወንዝም ዳር ሥሩን እንደሚዘረጋ ሙቀትም ሲመጣ እንደማይፈራ ቅጠሉም እንደሚለመልም፥ በድርቅ ዓመትም እንደማይሠጋ ፍሬውንም እንደማያቋርጥ ዛፍ ይሆናል። ኤርምያስ 17፡7-8
በእግዚአብሄር የታመኑ ሰዎች አይታወኩም፡፡
በእግዚአብሔር የታመኑ እንደማይታወክ ለዘላለም እንደሚኖር እንደ ጽዮን ተራራ ናቸው። መዝሙር 125፡1
በእግዚአብሄር የሚታመን ሰው አያፍርም፡፡
ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ በጽዮን ድንጋይን ለመሠረት አስቀምጣለሁ፤ የተፈተነውን፥ የከበረውን፥ መሠረቱ የጸናውን የማዕዘን ድንጋይ የሚያምን አያፍርም። ኢሳያስ 28፡16
እግዚአብሄርን የሚያውቁት በእርሱ ይታመናሉ፡፡
ስምህን የሚያውቁ ሁሉ በአንተ ይታመናሉ፥ አቤቱ፥ የሚሹህን አትተዋቸውምና። መዝሙር 9፡10
ስለዚህ በእግዚአብሄር ታመኑ እርሱ ረዳት ነው፡፡
የሕዝብ ማኅበር ሁላችሁ፥ በእርሱ ታመኑ፥ ልባችሁንም በፊቱ አፍስሱ፤ እግዚአብሔር ረዳታችን ነው። መዝሙር 62፡8
በእግዚአብሄር የሚታመን ምስጉን ነው፡፡
የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ በአንተ የታመነ ሰው ምስጉን ነው። መዝሙር 84፡12
በእግዚአብሄር የታመነ ሰው ከእግዚአብሄር ውጭ የሚያስፈነድቀውም የሚያስፈራውም ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር በሁሉ ፍሬያማ እንደሆነ በእግዚአብሄር የታመነ በምንም ሁኔታ ውስጥ ፍሬያማ ነው፡፡ በእግዚአብሄር እንደሚታመን ሰው ፍሬያማ የተሳካለትና የተከናወነለት ሰው የለም፡፡
በእግዚአብሔር የታመነ እምነቱም እግዚአብሔር የሆነ ሰው ቡሩክ ነው። በውኃ አጠገብ እንደ ተተከለ፥ በወንዝም ዳር ሥሩን እንደሚዘረጋ ሙቀትም ሲመጣ እንደማይፈራ ቅጠሉም እንደሚለመልም፥ በድርቅ ዓመትም እንደማይሠጋ ፍሬውንም እንደማያቋርጥ ዛፍ ይሆናል። ኤርምያስ 177-8
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መደገፍ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መታመን #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment