Popular Posts

Showing posts with label How to Receive from God. Show all posts
Showing posts with label How to Receive from God. Show all posts

Wednesday, August 12, 2020

አንተን ካገኘሁ ጀምሮ ህይወቴ በአንተ አምሮ

 

አንተን ካገኘሁ ጀምሮ
ህይወቴ በአንተ አምሮ
የምህረትን ብዛት አልችልም ልገልጣት
የፍቅርህን ብዛት አልችልም ልገልጣት
ዘማሪ አገኘሁ ይደግ

Sunday, June 21, 2020

ሰው ደስ ከሚለውና በሕይወቱ ሳለ መልካምን ነገር ከሚያደርግ በቀር መልካም ነገር እንደሌለ አወቅሁ። ደግሞም ሰው ሁሉ ይበላና ይጠጣ ዘንድ በድካሙም ሁሉ ደስ ይለው ዘንድ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው። ከሚበላውና ከሚጠጣው ደስም ከሚለው በቀር ለሰው ከፀሐይ በታች ሌላ መልካም ነገር የለውምና እኔ ደስታን አመሰገንሁ፤ ከፀሐይም በታች ከድካሙ እግዚአብሔር በሰጠው በሕይወቱ ዘመን ይህ ደስታው ከእርሱ ጋር ይኖራል። መጽሐፈ መክብብ 3፡12-13 ፣ 8፡5

ሰው ደስ ከሚለውና በሕይወቱ ሳለ መልካምን ነገር ከሚያደርግ በቀር መልካም ነገር እንደሌለ አወቅሁ። ደግሞም ሰው ሁሉ ይበላና ይጠጣ ዘንድ በድካሙም ሁሉ ደስ ይለው ዘንድ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው። ከሚበላውና ከሚጠጣው ደስም ከሚለው በቀር ለሰው ከፀሐይ በታች ሌላ መልካም ነገር የለውምና እኔ ደስታን አመሰገንሁ፤ ከፀሐይም በታች ከድካሙ እግዚአብሔር በሰጠው በሕይወቱ ዘመን ይህ ደስታው ከእርሱ ጋር ይኖራል። መጽሐፈ መክብብ 3፡12-13 ፣ 8፡5

Sunday, April 26, 2020

በምድር ያለነው


በተለያየ ጊዜ በህይወታችን የተለያዩ ተግዳሮቶች ይመጣሉ፡፡ ታዲያ ይህን አልፈው ይሆን ብለን የምናስብበት ውጥረት በህይወታችን ይመጣል፡፡ እንደዚህ አይነት ውጥረት በህይወታችን ሲገጥመን "በምድር ላይ ያለሁት ለምንድነው?" ብለን ይህን ጥያቄ ከልባችን እንጠይቃለን፡፡
በምድር ላይ ያለሁት ለምንድነው? የሚለው ጥያቄ ሁል ጊዜ መጠየቅና በትክክል መመለስ ያለበት ጥያቄ ነው፡፡
እውነት ግን በምድር ላይ ያለነው ለምንድነው?
የማንሞተው ለምንድነው ? ወይም መሞት የማንፈልገው ለምንድነው ?
በምድር ላይ ያለነው ስላልሞትን ነው ? ወይስ በምድር ላይ ስለመኖራችን ሌላ አለማ አለ?
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው አስቦና አቅዶና በአላማ ነው፡፡
እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ። እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። ኦሪት ዘፍጥረት 1፡26-27
ወደምድር ከመምጣታችን በፊት ወደምድር የመጣንበት ልዩ አላማ ነበር፡፡
ማንም ሰው በድንገት ውይም በአጋጣሚ በምድር ላይ የተወለደ ሰው የለም፡፡ ሰው በምድር ላይ የመወለዱ ምልክት ከመወለዱ በፊት የተወለደበት ልዩ አላማ የመኖሩ ምልክት ነው፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ኤርሚያስ 29፡11
እኛ በምድር ላይ ለመኖር ከምንፈልገው በላይ እግዚአብሄር በምድር ላይ እንድንኖር ይፈልጋል፡፡ በምድር ላይ ለመኖር ካለን ፍላጎት በላይ በምድር ላይ እንድንኖር የተፈለገበት የእግዚአብሄር አላማ ይበልጣል፡፡
በሰው ልብ ብዙ አሳብ አለ፤ የእግዚአብሔር ምክር ግን እርሱ ይጸናል። ምሳሌ 19፡21
በመጀመሪያ መጨረሻውን፥ ከጥንትም ያልተደረገውን እነግራለሁ፤ ምክሬ ትጸናለች ፈቃዴንም ሁሉ እፈጽማለሁ እላለሁ። ኢሳያስ 46፡10
ይህን በህይወታችን ላይ ያለውን የእግዚአብሄርን አላማ ስንረዳ እናርፋለን፡፡
እግዚአብሄር እንዴት እንደሚወደን ስንረዳ እና በህይወት ለመኖራችን ልዩ አላማ እንዳለው ስንረዳ ከፍርሃት ነፃ እንወጣለን፡፡
እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን። ኤፌሶን 2፡10
ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፥ ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም አይደለም። እርሱ አስቀድሞ ወዶናልና እኛ እንወደዋለን። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፡18-19
ፍርሃት የእግዚአብሄርን ፍቅር የመረዳታችንን ደረጃ ያመለክታል፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ያለውን የፍቅር አላማ በተረዳን መጠን ፍርሃት ከህይወታችን ቦታ እያጣ ይሄዳል፡፡  
የእግዚአብሄርን ፍቅር በተረዳን መጠን ከፍርሃት ነፃ እንወጣለን፡፡ እግዚአብሄር እንዴት በፍቅር እንደሚያየን በህይወታች ላይ ያለውን የእግዚአብሄርን የፍቅር አላማ እየተረዳን ስንመጣ በፍርሃት ሳይሆን በፍቅር እንንቀሳቀሳለን፡፡
የእግዚአብሄርን የፍቅር አለማ ስንረዳ የሚያንቃቅሰን ፍርሃት ሳይሆን ፍቅር ብቻ ይሆናል፡፡
በእኔ ላይ ያለው ዓላማውም ፍቅር ነው። መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 2፡4
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #እይታ #አላማ #ተስፋ #ፍፃሜ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ተስፋ #ፍፃሜ #የእግዚአብሄርሃሳብ #የእግዚአብሄርእቅድ #የእግዚአብሄርፈቃድ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Wednesday, February 12, 2020

ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም



ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም። መጽሐፈ መክብብ 11፡4
ህይወት የእምነት ጉዞ ነው፡፡ ህይወትን በሚገባ ማጣጣም ከፈለግክ በእምነት መኖር መጀመር አለብህ፡፡ በእምነት መራመድ ካልጀመርክ የህይወትን እውነተኛውን ጣእም በፍፁም አታገኘውም፡፡ ሰው መኖር የሚጀምረው በእምነት መራመድ ሲጀምር ብቻ ነው፡፡ የሰው እውነተኛ መኖሪያ የእግዚአብሄር ቃል እምነት ነው፡፡
እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። የማቴዎስ ወንጌል 4፡4
ሰው ዲዛይን የተደረገው ለእምነት ኑሮ ነው፡፡ ሰው የሚኖረው በእምነት ነው፡፡
እነሆ፥ ነፍሱ ኰርታለች፥ በውስጡም ቅን አይደለችም፤ ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል። ትንቢተ ዕንባቆም 2፡4
እምነት የሚመጣው ከእግዚአብሄር ቃል ነው፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡17
በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ለተፈጠረው ክቡር ለሆነው ሰው ለሰው ልጅ ከእግዚአብሄ ቃል ያነሰ ኑሮ አይገባውም፡፡
እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። የማቴዎስ ወንጌል 4፡4
የሰው እውነተኛ እርካታ በእምነት ሲኖር ነው፡፡
ነገሮች ሆነው ከማየትህ በፊት የእግዚአብሄርን ቃል አምነህ እርምጃ ካለወሰድክ ከእግዚአብሄር ጋር መኖር አትችልም፡፡
ከእግዚአብሄር ጋር የምትገናኘው በስጋ አይን የማይታየውን መንፈስ የሆነውን እግዚአብሄርን የምትሰማው ፣ እግዚአብሄርን የምትነካው ፣ እግዚአብሄርን የምታየው ሁሉ በእምነት ነው፡፡ የእግዚአብሄር ነገር ሁሉ በእምነት ነው፡፡
የእግዚአብሔር ቃል ቅን ነውና ሥራውም ሁሉ በእምነት ነውና። መዝሙረ ዳዊት 334
ነገሮች ተለውጠው ደስ ለመሰኘት የምትጠብቅ ከሆነ ደስ መሰኘቱን እርሳው፡፡ ነገሩን የሚለውጠው በእምነት እርምጃ በመውሰድ ደስ በመሰኘትህ ብቻ ነው፡፡
የምትፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ ኪስህ ከገቡ በኋላ እፎይ ለማለት እየጠበቅክ ከሆነ የማይፈፀም ተስፋ እየጠበክ ነው፡፡
ለማመን ፀሎትህ እስኪመለስ እየጠበቅክ ከሆነ ፀሎትህ ለመፈፀም የአንተን እምነት እየጠበቀ ነው፡፡
እውነት እላችኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል። ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል። የማርቆስ ወንጌል 11፡23-24
ሁሉ ደህና ነው ለማለት ነገሮች ሁሉ ተስተካክለው እስክታይ አየጠበቅክ ከሆነ በከንቱ ትጠብቃለህ፡፡   
ከመዝራትህ በፊት ሁኔታዎችን እየጠበቅክ ከሆነ መቼም አታጭድም፡፡
ምልክት ከማየትህ በፊት ማመን አለብህ፡፡ እምነትንም የሚያመጣው የእግዚአብሄር ቃል እንጂ ምልክት እምነትን አያመጣም፡፡ ምልክቱን የሚያመጣው እምነትህ ነው፡፡  
ከውጤት እና ከምልክት በፊት የእምነት እርምጃ ይቀድማል፡፡
እንጀራህን በውኃ ፊት ላይ ጣለው፥ ከብዙ ቀን በኋላ ታገኛዋለህና። መጽሐፈ መክብብ 11፡1
አስቀድመው ምልክትን የሚፈልጉ ካላየሁ አላምንም የሚሉ ሰዎች እግዚአብሄርን የማይፈልጉ አሿፊ ሰዎች ናቸው፡፡
ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያንም ቀርበው ሲፈትኑት ከሰማይ ምልክት እንዲያሳያቸው ለመኑት። ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፥ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም። ትቶአቸውም ሄደ። የማቴዎስ ወንጌል 16፡1፣4
ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም። መጽሐፈ መክብብ 11፡4
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እምነት #ወንጌል #ስብከት #ቃል #ዝራ #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ 

Monday, July 2, 2018

ብታምኚስ

ኢየሱስ፦ ድንጋዩን አንሡ አለ። የሞተውም እኅት ማርታ፦ ጌታ ሆይ፥ ከሞተ አራት ቀን ሆኖታልና አሁን ይሸታል አለችው። ኢየሱስ፦ ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርሁሽምን? አላት። የዮሐንስ ወንጌል 11፡39-40
የእግዚአብሄርን ክብር ማየት የማይፈልግ ሰው የለም፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት መመዘኛ አለው፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር በህይወታችን ለመለማመድ መመዘኛው ደግሞ ሊደረስበት የማይችል ረቂቅ ነገር አይደለም፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት የሚጠይቀው እምነት ብቻ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት እምነት ወሳኝ ነው፡፡ እግዚአብሄርን ለማስደሰትና የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት ሌላ መንገድ የለውም፡፡
ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ወደ ዕብራውያን 11፡6
የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት ሌላ መንገድ ቢኖር ኖሮ ያንን መንገድ እንከተል ነበር፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት ሌላ መንገድ የለውም፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት ብቸኛው መንገድ እምነት ብቻ ነው፡፡ ኢየሱስ ለማርታ አልነገርሁሽምን? የሚላት በፊትም የእግዚአብሄርን ክብር የምታይው ስታምኚ እንደሆነ ነግሬሻለሁ ዛሬም አልተለወጠም የእግዚአብሄን ክብር ማየት ከፈለግሽ ማመን ወሳኝ ነው እያላት ነው፡፡
የእግዚአብሄን ክብር እንድናይ የሚያስችለን እምነት ደግሞ የሚመጣው የእግዚአብሄርን ቃል ከመስማት ነው፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡17
የእግዚአብሄር ክብር ከሰዎች የራቀ እጅግ ረቂቅ ነገር አይደለም፡፡ እግዚአብሄር ቸር አምላክ ነው፡፡ ምድር በእግዚአብሄር ከብር ተሞልታለች፡፡
ነገር ግን እኔ ሕያው ነኝና በእውነት የእግዚአብሔር ክብር ምድርን ሁሉ ይሞላል።  ኦሪት ዘኍልቍ 14፡21
የእግዚአብሄር ክብር የሚያይ ሰው በእግዚአብሄር ቃል መስማት እምነትን ያገኘ ሰው ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር በህይወቱ የሚለማመድ ሰው በእግዚአብሄር ቃል እምነትን ያገኘ ሰው ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ክብርና ሃይል በህይወቱ የሚለማድ ሰው የእግዚአብሄርን ቃል የሚያምን ሰው ነው፡፡
እግዚአብሔር ልቡ በእርሱ ዘንድ ፍጹም የሆነውን ያጸና ዘንድ ዓይኖቹ በምድር ሁሉ ይመለከታሉና። መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 16፡9
የእግዚአብሄርን ቃል የሰማ ሰው የእግዚአብሄርን ክብርና በጎነት በህይወቱ ይለማመዳል፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር ማየት ይቻላል፡፡ የሞተ ሲነሳ ማየት ይቻላል፡፡ የደከመ ሲበረታ ማየት ይቻላል፡፡ የሌለን ወደመኖር ሲመጣ ማየት ይቻላል፡፡
ስለዚህ ከሕግ ብቻ ሳይሆን ከአብርሃም እምነት ደግሞ ለሆነ ለዘሩ ሁሉ የተስፋው ቃል እንዲጸና እንደ ጸጋ ይሆን ዘንድ በእምነት ነው፤ እርሱም፦ ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት የሁላችን አባት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 4፡16-17
በእምነት የእግዚአብሄርን ክብር ማየት ይቻላል፡፡ ለሚያምን ሁሉ ይቻለዋል፡፡ ለማያምን የእግዚአብሄርን ክብር ሃይልና በጎነት ማየት ይቻለዋል፡፡
ኢየሱስ፦ ድንጋዩን አንሡ አለ። የሞተውም እኅት ማርታ፦ ጌታ ሆይ፥ ከሞተ አራት ቀን ሆኖታልና አሁን ይሸታል አለችው። ኢየሱስ፦ ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርሁሽምን? አላት። የዮሐንስ ወንጌል 1139-40
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #እግዚአብሔር #ክብር #መልክ #አምሳል #ሃይል #ብፅእና #በረከት #ቃል #ፀሎት #አምልኮ #በጎነት #መጠማት #መራብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

ድሆች ስንሆን

በክፉ ወሬና በመልካም ወሬ ራሳችንን እናማጥናለን፤ አሳቾች ስንባል እውነተኞች ነን፤ ያልታወቁ ስንባል የታወቅን ነን፤ የምንሞት ስንመስል እነሆ ሕያዋን ነን፤ የተቀጣን ስንሆን አንገደልም፤ ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6፡7-9
ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ለጻድቃን አይደለም፡፡ ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ለበሽተኞች ነው፡፡ ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ለሃያላን አይደለም ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ለደካሞችነው፡፡ ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ምንም አያስፈልገንም ለሚሉ አይደለም፡፡ ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ለድሆች ነው፡፡
የነቢዩንም የኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጡት፥ መጽሐፉንም በተረተረ ጊዜ፦ የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ለታሰሩትም መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፥ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል ተብሎ የተጻፈበትን ስፍራ አገኘ። የሉቃስ ወንጌል 4፡17-19
የአገልጋይ ክብሩ ደሃን ባለጠጋ ማድረግ ነው፡፡ እውነተኛ አገልጋይ የሚፈልገው ደሃን ነው፡፡ እውነመተኛ አገልጋይ ድሃን ባለጠጋ ያደርጋል፡፡
ዳዊትን የተከተሉት ሰዎች እጅግ የተጣሉ የተጨነቁና የተከፉትን ሰዎች ነበር፡፡
የተጨነቀውም ሁሉ፥ ብድርም ያለበት ሁሉ፥ የተከፋም ሁሉ ወደ እርሱ ተከማቸ፤ እርሱም በላያቸው አለቃ ሆነ፤ ከእርሱም ጋር አራት መቶ የሚያህሉ ሰዎች ነበሩ። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 22፡2
ዳዊትን የተከተለውን የተጨነቀውም ሁሉ፥ ብድርም ያለበት ሁሉ፥ የተከፋም ሁሉ የምድሪቱ ሃያላን አደረገው፡፡
ሦስቱም ኃያላን የፍልስጥኤማውያንን ሠራዊት ቀድደው ሄዱ፥ በበሩም አጠገብ ካለችው ከቤተ ልሔም ምንጭ ውኃ ቀዱ፥ ይዘውም ለዳዊት አመጡለት፤ እርሱ ግን ሊጠጣ አልወደደም፥ ነገር ግን ለእግዚአብሔር አፍስሶ፦ መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ 23፡16
የአገልጋይ ክብር ምንም ያልሆነውንና ምንም የሌለውን ሰው አጥቦና አሸላልሞ ባለጠጋ ማድረግ ነው፡፡
ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6፡9
የአገልጋይ ክብር ድሆችን በነገር ሁሉ ባለጠጋ ማድረግ ነው፡፡
ለክርስቶስ መመስከሬ በእናንተ ዘንድ እንደ ጸና፥ በነገር ሁሉ በቃልም ሁሉ በእውቀትም ሁሉ በእርሱ ባለ ጠጎች እንድትሆኑ ተደርጋችኋልና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፡5-6
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ abiy Wakuma dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ያልታወቁ #የታወቅን #የምንሞት #ሕያዋን #የተቀጣን #አንገደልም  #ኀዘንተኞች #ደስ #ድሆች #ባለጠጎች #የሌለን  #ሁሉየእኛነው #ጭንቀት #የባለጠግነትማታለል #የኑሮሃሳብ #የእለትእንጀራ #የባለግነትምቾት #ዘር #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Sunday, July 1, 2018

Don’t Bang At the Door of Your Last Season

There are different seasons in our lives. There is a season to live with others there is a season to go our way.
Seasons definitely change. But season change shouldn’t be a cause of contention.
Some people don’t feel the season is changed unless they create havoc in their way out. Some people bang the door of the last season. They don’t learn how to quietly close the last season and move on.
That is the reason that one of the qualifications of a church leader is to be "not violent but gentle, not quarrelsome,"
Now the overseer is to . . . not given to drunkenness, not violent but gentle, not quarrelsome, not a lover of money. 1 Timothy 3:2-3
Your banging at the door of your last season doesn’t add anything good for you. It will definitely hurt others and you a lot. It shouldn’t be.  
Everything should be peaceful. You can win without starting any fight.
If it is possible, as far as it depends on you, live at peace with everyone. Romans 12:18
Make peace with everyone. Don’t be a part of any problem. Be a part of every solution.
Blessed are the peacemakers, for they will be called children of God. Matthew 5:9
Abiy Wakuma Dinsa
For More Articles https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#Jesus #God #Trust #praise #livelife #betrayal #peace #season #faith #enjoylife #faithfulness #church #door #bang #preaching #salvation #bible #countingthecost #peace #discipline #morale #abiy #facebook #abiywakuma #abiywakumadinsa

ራእይ ለምን

ለተሳካ ህይወትና ለአገልግሎት ራእይ ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ራእይ ከየት እንደመጣን ወዴት እንደምንሄድ ይጠቁመናል፡፡
አንዳንድ ሰዎች ራእይ ሊጨበጥ የማይችል ሃይማኖታዊ ሃሳብ ብቻ ይመስላቸዋል፡፡ ስለዚህ አንዳንድ ሰዎች ስለህይወትህ ፣ ስለቤተሰብህ ፣ ስለአገልግሎትህና ስለስራህ ራእይ አለህ? ተብለው ሲጠየቁ ህይወታቸውን የሚያወሳሰብ ሊደረስበት የማይችል ረቂቅ ጥያቄ የተጠየቁ ይመስላቸዋል፡፡ ራእይ ውስብስብ ሊረዱት የማይችሉት ረቂቅ ነገር ይመስላቸዋል፡፡ ስለራእያቸው የሚጠይቃቸው ሰው የሚያካብድና ህይወታቸውን ማወሳሰብ የፈለገ ሰው ይመስላቸዋል፡፡
ራእይ በአጭሩ ምሪት ማለት ነው፡፡ ራእይ ማለት እግዚአብሄር በህይወታችን ፣ በአገልግሎታችን ፣ በስራችንና በትዳራችን ሊሰራ ያለውን ነገር አስቀድሞ የገለጠልን ምሪት ማለት ነው፡፡ ራእይ ማለት መገለጥ ማለት ነው፡፡ ራእይ አለን ማለት የምንሄድበትን ቦታ እናውቃለን ማለት ነው፡፡ ራእይ ማለት በህይወት የምንከተለውን አቅጣጫ መረዳት ማለት ነው፡፡
ራእይ አለን ማለት እንዳመጣልን አንኖርም ማለት ነው፡፡ ራእይ አለን ማለት ወደነፈሰበት አቅጣጫ እንሄደም ማለት ነው፡፡ ራአየ አለን ማለት ውሃ ላይ እንሚንሳሰፈፍ ቀላል ነገር ውሃው በተንቀሳቀሰበት አቅጣጫ እንንሳፈፍም ማለት ነው፡፡
ራእይ በጣም አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ እግዚአብሄር ለክብሩ ነው የፈጠረን፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረን የራሳችንን ነገር አድርገን እንድናልፍ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረን የልጅነት ምኞታችንን እንድንፈፅም አይደለም፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረን እርሱ በህይወታችን ያለውን አላማ እንድንከተል ነው፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረን በራእይ እንድንኖር ነው፡፡
ራእይ በጣም አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ራእይ ለምን እንዳስፈለገ እንመልከት
በግምት ስለማይሳካልን
በክርስትና የእግዚአብሄርን መሪት ካልተከተልን በግምት አይሳካልንም፡፡ ክርስትና ሰፊ መንገድ አይደለም፡፡ ክርስትና ጥንቃቄን የሚፈልግ ጠባብ መንገድ ነው፡፡ በራእይ መንገድ እንጂ እንደፈለግን ኖረን እግዚአብሄርን አናስደስተውም፡፡
በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው። የማቴዎስ ወንጌል 7፡13-14
ለምን እንዳልተጠራን ማወቅ ስላለብን፡፡
በአለም ላይ ብዙ ድምፆች አሉ፡፡ በአለም ላይ ተከተለኝ ይሳካልሃል የሚሉ ብዙ መንገዶች አሉ፡፡ በአለም ላይ ብዙ አማራጮች አሉ፡፡ እኛ ማድረግ የምንችለው ደግሞ አንድ ነገርን ብቻ ነው፡፡ በህይወትም የሚሳካልን በብዙ አማራጮች ሳይሆን በአንድ መንገድ ብቻ ነው፡፡ በህይወት ያለን ጊዜና ጉልበት የሚበቃው እግዚአብሄር ለጠራን ስራ ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር ያለጠራንን ለማድረግ የሚበቃ ምንም ትርፍ ነገር የለንም፡፡ ራእይ አስፈላጊ የሆነበት ምክኒያት ለምን እንደተጠራን ብቻ ሳይሆን ለምን እንዳልተጠራን ማወቅ ስላለብን ነው፡፡ ለዚህ እግዚአብሄር ጠርቶኛል እንደምንል ሁሉ ለዚህ እግዚአብሄር አልጠራኝም የምንለው ነገር መኖር አለበት፡፡ ራአይ ያለው ሰው አግዚአብሄር ብሎኛል እንደሚል ሁሉ እግዚአብሄር አላለኝም የሚለውና ምንም መንፈሳዊ ነገር ቢሆን የማያደርገው ነገር አለ፡፡ ራእይ ያለው ሰው ያልተጠራበት ነገር ላይ ጉልበቱን ከማባከን ያርፋል፡፡
ኢየሱስ ሊያደርግ ስላለው ነገር ሁሉ ራእይ ስለነበረው ለዚህ አልተጠራሁም ይል ነበር፡፡  
ከሕዝቡም አንድ ሰው፦ መምህር ሆይ፥ ርስቱን ከእኔ ጋር እንዲካፈል ለወንድሜ ንገረው አለው። እርሱም፦ አንተ ሰው፥ ፈራጅና አካፋይ በላያችሁ አንድሆን ማን ሾመኝ? አለው። የሉቃስ ወንጌል 12፡13-14
መንፈሳዊ አገልግሎትም ቢሆን እግዚአብሄር እንድንሰራው የጠራን አገልግሎት አለ እንዳንሰራው የሚፈልገው አገልግሎት ደግሞ አለ፡፡ ያንን መረዳት ባልተጠራንበት ፀጋው በሌለን ቦታ ህይወታችንን እንዳናቃጥል ያደርገናል፡፡
ለማጥመቅ ክርስቶስ አልላከኝምና፥ ወንጌልን ልሰብክ እንጂ፤ የክርስቶስ መስቀል ከንቱ እንዳይሆን በቃል ጥበብ አይደለም። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፡17
ራእትይ በጣም ወሳኝ የሆነበት ምክንያት ግባችን ስንደርስ እንድናውቅ ነው
ራእይ የሌለው ሰው ወደግቡ አነጣጠሮ ከመወርወር ይልቅ ከወረወረ በኋላ ይህ ነበር ግቤ ብሎ ያከብበታል፡፡ ራእይ የምንሄድበትን መንገስ ያሳያል ራእይ የህይወት ግብን ይሰጠናል፡፡ ራእይ የሌለው ሰው እና የሚሄደበትን የማያውቅ ሰው ሲደርስ አያውቅም፡፡ ራእይ የሌለው ሰው እንደደረሰ ስለማያውቅ እርካታ የለውም፡፡
በመሥዋዕት እንደሚደረግ፥ የእኔ ሕይወት ይሠዋልና፥ የምሄድበትም ጊዜ ደርሶአል። መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4፡6-7
ራእይ የሌለው ሰው ሁኔታዎች ሲቃረኑ ራእዩን ያያል
ራእይ ያለው ሰው ሁኔታዎች እንደተፈለገው በማይሄዱት ጊዜ ተስፋ እንዳይቆርጥ ራእዩ ተስፋ ይሆነዋል፡፡ ሁኔታው ተስፋ ሲያስቆርጥ በራእዪ ተስፋ ያደርጋል፡፡ ወደ ሮሜ ሰዎች 4፡18
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ራዕይ #ምሪት #የእግዚአብሄርአጀንዳ #የእግዚአብሄርፈቃድ #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Saturday, June 30, 2018

The Moral Lesson from Argentina Vs. France Match

I was watching the world cup final knock out stage match between Argentina and France. France went through by defeating Argentina 4 to 2.
Some of the most important France players picked up yellow cards. The yellow cards they pick were unreasonable. Sometimes you may be tempted to commit foul when an attacker is about to score goals and It is sometimes worth the yellow card warning.
But when you just pick a yellow card in the middle of the field or just starting a fight doesn’t worth it at all.
France is through to the quarter-final but with some yellow cards that prevent them from playing the next match. Some of the players miss the next match because it is their second consequent yellow cards.
Some of them picked a yellow card not believing that they will be through to the next stage. Others were not cautious.
The moral lesson I got from the match is live your life in such a very careful way that doesn’t spoil your next stage. Don’t lose your next game focusing only on winning the current one.
God prevented David from building his house saying “You are not to build a house for my Name, because you are a warrior and have shed blood"
But God said to me, 'You are not to build a house for my Name, because you are a warrior and have shed blood.' 1 Chronicles 28:3
It takes discipline not to go overboard to win the current game at the cost of the next one.
Abiy Wakuma Dinsa
For More Articles https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#Jesus #God #Trust #praise #livelife #betrayal #blessed #rejoice #faith #enjoylife #faithfulness #church #achievement #celebration #preaching #salvation #bible #countingthecost #Argentina # France #worldcup #discipline #morale #abiy #facebook #abiywakuma #abiywakumadinsa  

በህይወቴ የምጠላው

በህይወቴ የምፈራው ሞትን አይደለም፡፡ ሞት የተሸነፈ ጠላት ነው፡፡ ሞት የሚያስፈራው የጌታ ኢየሱስን አዳኝነት ላልተቀበለ ሰው ለዘላለም ከእግዚአብሄር መለያያ መንገድ ስለሆነ ያስፈራል፡፡ ሞት የሚያስፈራው ከሞት ፍርሃት ነፃ ላልወጣ ላልዳነ ሰው ነው፡፡   
እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። ወደ ዕብራውያን 2፡14-15
የስጋ ሞት ከምድራዊ ህይወት ወደ መንፈሳዊ ህይወት የምንሸጋገርበት መተላለፊያ በር ነው፡፡ በእውነት ካሰብነው እግዚአብሄር በሰማይ ያዘጋጀልንን ክብር ካየነው መሞት ያስደስታል እንጂ አያስፈራም፡፡ መሞት እንዲያውም እረፍትና ጥቅም ነው፡፡ በምድር የምንኖረው የእግዚአብሄርን መንግስት ለመስራት እንጂ ለእግዚአብሄር ስራ ባይሆን ኖሮ መሞት እረፍት ነው፡፡
ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነውና። ነገር ግን በስጋ መኖር ለእኔ የሥራ ፍሬ ቢሆን፥ ምን እንድመርጥ ኣላስታውቅም። በእነዚህም በሁለቱ እጨነቃለሁ፤ ልሄድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ፥ ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻል ነውና፤ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 1፡21-23
በህይወቴ የምፈራው ማጣትን አይደለም፡፡
ማጣት እንደማይገድል አይቸዋለሁ፡፡ ማጣት ሊፈራ የሚገባ እንዳይደለ አይቼዋለሁ፡፡ ማጣት ማንንም መንከስ እንደማይችል እንደታሰረ ውሻ ባዶ ጩኸት መሆኑን በህይወቴ አይቼዋለሁ፡፡ ማጣት የእግዚአብሄርን ፈቃድ መፈፀም እንደማያግድ አይቼቸዋለሁ፡፡ ዋናው ነገር ማጣት ወይም ማግኘትን ሳይሆን ሁሉንም የሚያስችለን ክርስቶስ በእኛ ውስጥ መሆኑ ነው፡፡ ክርስቶስ ካለ ተጨማሪ ነገር አያስፈልገንም፡፡ ክርስቶስ ካለ ማጣት አያቆመንም፡፡ የሚያስችለን ማግኘት ሳይሆን ክርስቶስ ነው፡፡ በክርስቶስ ሁሉን እንችላለን፡፡
ይህን ስል ስለ ጉድለት አልልም፤ የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል ማለትን ተምሬአለሁና። መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ። ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ። ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 4፡11-13
በህይወቴ የምፈራው ድካምን አይደለም፡፡
ስንደክም ስንዋረድ በድካምና በመዋረድ ውስጥ ክብር አለ፡፡ በራሳችን ስንደክም ያን ጊዜ በክርስቶስ ሃይል ሃይለኛ ነኝ፡፡ የእግዚአብሄር ጉልበት በድካሜ ስለሚታይበት በድካሜ ደስ ይለኛል፡፡
እርሱም፦ ጸጋዬ ይበቃሃል፥ ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና አለኝ። እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ። ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም በመንገላታትም በችግርም በስደትም በጭንቀትም ደስ ይለኛል፤ ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 12፡9-10
በህይወቴ የምፈራው ሃዘንን አይደለም
ሃዘንተኛን በማፅናናት የተካነ የመፅናናት አምላክ እግዚአብሄር አባቴ ነው፡፡ አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ ሰላም የሚሰጥ እገዚአብሄ አብሮን ነው፡፡
የርኅራኄ አባት የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፡3
በህይወቴ የምፈራው መከራን አይደለም
ፈተና እኛን አሻሽሎን አበርትቶን ከፊት ይልቅ አሳድጎን ነው የሚያልፈው፡፡ ከምንችለው በላይ እንድንፈትን የማይፈቅድ ታማኝ እግዚአብሄር ስላለ መከራን አያስፈራንም፡፡ መከራ የሚያገኘው በእኛ ላይ ያለን የማያስፈልግ ስጋዊነትነ ብቻ ነው፡፡ መከራ የሚያራግፈው ክርስቶስን የማይመስለውን የስጋ ምኞታችንን ብቻ ነው፡፡ ስጋዊነትን በሰዎች ህይወት ስናይ እንደሚቀፈን ሁሉ ለእግዚአብሄር የማይመቸው በመከራ የሚራገፈውን ስጋዊነትን ስናይ እግዚአብሄር ይመስገን ልንል ይገባል፡፡
ሰላም ለእናንተ ይሁን። ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት ትዕግሥትም ምንም የሚጎድላችሁ ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም። የያዕቆብ መልእክት 1፡2-4
መውጫውን ያዘጋጀው እግዚአብሄር ከእኛ ጋር ስላለ ፈተና አያስፈራም፡፡
ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10፡13
የሚያስፈራው የእግዚአብሄርን ሃሳብ መጣስ ነው፡፡ የሚያስፈራው የምድር ህይወታችንን ለጊዜያዊ ለግል ጥቅማችን ማሳለፍ ነው፡፡ የሚያስፈራው ዋጋቸውን በምድር ተቀብለዋል መባል ነው፡፡ የሚያስፈራው በህይወታችን ዘመን ሁሉ እግዚአብሄር ያላለንን ነገር ሲያደርጉ በመኖር ህይወትን ማባከን ነው፡፡ የሚያስፈራው እግዚአብሄር ያዘዘንን ትተን እግዚአብሄር ያላዘዘንን ነገር ማድረግ ነው፡፡ የሚያስፈራው እግዚአብሄር ያልጠራንን ነገር በማድረግ አንዱን ህይወታችንን ማባከን ነው፡፡ የሞያስፈራው እግዚአብሄር ሳያዘን አንድ እርምጃን መራመድ ነው፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ልብ #መዳን #እምነት #ማስተዋል #አላማ #ግብ #የምፈራው #የምጠላው #ማጣት #ሃዘን #ፈተና #ሞት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ፅናት #ማሰብ #መሪ

የጴጥሮስ ክህደት

ብዙ ጊዜ ስለክህደት ሲነሳ ስሙ የሚነሳው ይሁዳ ነው፡፡ እንዲያውም የክህደት ሌላ ስሙ እስኪመስል ድረስ ይሁዳ ከክህደት ጋር አብሮ ይነሳል፡፡
ኢየሱስን ከካዱት ሁለት ሰዎች መካከል ይሁዳና ጴጥሮስ በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ጴጥሮስም ይህን ሰው አላውቀውም ብሎ ክዶዋል፡፡
ጴጥሮስም ከቤት ውጭ በአጥሩ ግቢ ተቀምጦ ነበር፤ አንዲት ገረድም ወደ እርሱ ቀርባ፦ አንተ ደግሞ ከገሊላው ከኢየሱስ ጋር ነበርህ አለችው። እርሱ ግን፦ የምትዪውን አላውቀውም ብሎ በሁሉ ፊት ካደ። ወደ በሩም ሲወጣ ሌላይቱ አየችውና በዚያ ላሉት፦ ይህ ደግሞ ከናዝሬቱ ከኢየሱስ ጋር ነበረ አለች። ዳግመኛም ሲምል፦ ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ካደ። የማቴዎስ ወንጌል 26፡69-72
ኢየሱስ ሰውን ሊክደው እንደሚችል ያውቃል፡፡ ሰው ሊክደኝ አይችልም ማለት አደገኛ አመለካከት ነው፡፡ ሰው የሚክደን በራሱ ችግር እንጂ እኛ ስላጠፋንም አይደለም፡፡ ሃጢያት የሌለበት ኢየሱስ ተክዷል፡፡
ልካድ እችላለሁ ብሎ ልብን ማስፋት ብንካድ ጉልበት ሊሰጠን የሚችል ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ሰው ሊካድ ቢችልም ሰውን ማመን ታላቅ ልብ ነው፡፡ ሰው ሊክደኝ ይችላል በሚል ፍርሃት ሰውን ማመን የሚያቆም ሰው ብቻውን ይቀራል፡፡ ሊክድ የሚችል እንዳለ የታመነ የማይክድ ሰውም ደግሞ አለ፡፡ ሊክድ በሚችለው ፍርሃት የታመነውን ሰው ማጣት ጥበብ አይደለም፡፡  
ፍቅር . . . ሁሉን ይታገሣል፥ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡7
ይሁዳ ሊክደው እንደሚችል ኢየሱስ አውቆ ነበር፡፡ ኢየሱስ እንደሚክደው አውቆ ከይሁዳ ጋር አብሮት ኖሮዋል አብሮት አገልግሏል፡፡
ኢየሱስም፦ እኔ እናንተን አሥራ ሁለታችሁን የመረጥኋችሁ አይደለምን? ከእናንተም አንዱ ዲያብሎስ ነው ብሎ መለሰላቸው። ስለ ስምዖንም ልጅ ስለ አስቆሮቱ ይሁዳ ተናገረ፤ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ የሆነ እርሱ አሳልፎ ይሰጠው ዘንድ አለውና። የዮሐንስ ወንጌል 6፡70-71
ኢየሱስ ጴጥሮስ እንደሚክደውም ሁሉ አስቀድሞ አውቆዋል፡፡
እርሱም፦ ጌታ ሆይ፥ ወደ ወኅኒም ወደ ሞትም ከአንተ ጋር ለመሄድ የተዘጋጀሁ ነኝ አለው። እርሱ ግን፦ ጴጥሮስ ሆይ፥ እልሃለሁ፥ እንዳታውቀኝ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዛሬ ዶሮ አይጮኽም አለው። የሉቃስ ወንጌል 22፡33-34
ይሁዳ በክህደቱ አገልግሎቱንም ህይወቱንም አጣ፡፡
በመዝሙር መጽሐፍ፦ መኖሪያው ምድረ በዳ ትሁን የሚኖርባትም አይኑር፤ ደግሞም፦ ሹመቱን ሌላ ይውሰዳት ተብሎ ተጽፎአልና። የሐዋርያት ሥራ 1፡20
ማንም ሰው ሊወድቅ ይችላል፡፡ ሰው በክህደቱ ከቀጠለ ህይወቱንና አገልግሎቱን ያጣል፡፡ ሰው ግን በክህደቱ ካዘነና ከተመለሰ እንዳልወደቀ ሆኖ እግዚአብሄር እንደገና በሃይል ይጠቀምበታል፡፡
እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን ጸጸት የሌለበትን፥ ወደ መዳንም የሚያደርሰውን ንስሐ ያደርጋልና፤ የዓለም ኀዘን ግን ሞትን ያመጣል። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7፡10
ከይሁዳ የሚለየው ጴጥሮስ የሚመለስ ልብ ነበረው፡፡ አንዳንዴ ካልሆነ የጴጥሮስ ክህደት አይነሳም፡፡ የጴጥሮስ ክህደት ከመረሳቱ የተነሳ ጴጥሮስን የምናስታውስበት ብዙ መልካም ነገሮች አሉ፡፡ ኢየሱስ የጴጥሮስን ከውድቀቱ ባሻገር መነሳቱን አይቶ ነበር፡፡ ኢየሱስ ከክህደቱ ባሻገር የጴጥሮስን ጠቃሚነቱን አይቶ ነበር፡፡
ጴጥሮስ የሚሰበር በጥፋቱ የሚያዝን ልብ ስልነበረው እግዚአብሄር ሁለተኛ እድል ሰጠው፡፡ ኢየሱስ ጴጥሮስ ወደፊት የማይክድበትን መንገድ ቀየሰ፡፡ ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ እንዲሞላና እንዲክድ ያደረገውንና ያሸነፈውን የፍርሃት መንፈስን የሚያሸንፍበት መንፈስ ቅዱስ ተሞላ፡፡
ጴጥሮስ በንስሃ ከተመለሰ በኋላ መንፈስ ቅዱስን በመሞላት ያሸነፈውን የፍርሃትን መንፈስ አሸነፈው፡፡
ነገር ግን ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ፥ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ሲል ተናገራቸው፦ አይሁድ በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፥ ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፥ ቃሎቼንም አድምጡ። የሐዋርያት ሥራ 2፡14
ጴጥሮስ ሲመለስ እግዚአብሄር በመንፈስ ቅዱስ ሙላት የሃይል የፍቅር ራስን የመግዛት መንፈስ ሰጠው፡፡
እግዚአብሔር የኃይልና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሃት መንፈስ አልሰጠንምና። 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1፡7
ማንም ሰው በክህደት ሊወድቅ ይችላል፡፡ የሚነሳውና እንደገና የእግዚአብሄር መጠቀሚያ የሚሆነው ሰው ግን በንስሃ በእግዚአብሄር ፊት የሚመለሰው ሰው ብቻ ነው፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መካድ #መታለል #ታማኝነት #ክህደት #ንስሃ #ሃዘን #መመለስ መጣል #መሰደድ #መገፋት #መውደቅ #አለመመረጥ #ተቀባይነትማጣት #ዋጋአሰጣጥ #አእምሮ #ልብ #ኢየሱስ #ጌታ #መፅሃፍቅዱስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አምልኮ #እምነት #መከተል