Popular Posts

Monday, July 31, 2017

የፍቅራችሁንም ድካም

በጸሎታችን ጊዜ ስለ እናንተ ስናሳስብ፥ የእምነታችሁን ስራ የፍቅራችሁንም ድካም በጌታችንም በኢየሱስ ክርስቶስ ያለውን የተስፋችሁን መጽናት በአምላካችንና በአባታችን ፊት ሳናቋርጥ እያሰብን፥ እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ በሁላችሁ ምክንያት እናመሰግናለን፤ 1 ተሰሎንቄ 1፡2-3
ፍቅር ስሜት አይደለም፡፡ ፍቅር ከእኛ ቁጥጥር ውጭ የሆነ በፈለገው ጊዜ የሚይዘን በፈለገው ጊዜ ደግሞ የሚለቀን ምትሃት ወይም ስሜት አይደለም፡፡ እውነተኛ ፍቅር የውሳኔ ድርጊት ነው፡፡ እውነተኛ ፍቅር የመረዳት እርምጃ ነው፡፡ እውነተኛ ፍቅር የማስተዋል ስራ ነው፡፡
ፍቅር የሚታየው በስራ ነው፡፡ ፍቅር የሚታየው በድርጊት ነው፡፡ ፍቅር የሚገለፀው በድካም ነው፡፡
ሃዋሪያው ጳውሎስ እግዚአብሄርን የሚያመሰግነው የፍቅራቸውን ድካም አይቶ ነው፡፡ የተሰሎንቄ ሰዎች ፍቅራቸው የተገለፀው በስራቸው ነው፡፡ ፍቅራቸውን የገለጠው ትጋታቸው ነው፡፡ እንዲሰሩ እንዲደክሙ ያደረጋቸው ፍቅር ነው፡፡ እነዚህ የተሰሎንቄ ሰዎች ፍቅር ስላላቸው ለሚወዱት ይሰራሉ ፣ ለሚወዱት ይተጋሉ ብሎም ለሚወዱት ይደክማሉ፡፡
ለፍቅር እንድከም እንጂ ቢደክመን ችግር የለውም፡፡ በፍቅር ትጋት ይጠበቃል፡፡ በፍቅር ስራ ግዴታ ነው፡፡ እንዲያውም በልባችን ያለው ፍቅር ወጥቶ የሚታየው በድርጊትና በስራ ነው፡፡
በጸሎታችን ጊዜ ስለ እናንተ ስናሳስብ፥ የእምነታችሁን ስራ የፍቅራችሁንም ድካም በጌታችንም በኢየሱስ ክርስቶስ ያለውን የተስፋችሁን መጽናት በአምላካችንና በአባታችን ፊት ሳናቋርጥ እያሰብን፥ እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ በሁላችሁ ምክንያት እናመሰግናለን፤ 1ኛ ተሰሎንቄ 1፡2-3
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ፍቅር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #ፍርሃት #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #መውደድ #ትግስት #መሪ


Sunday, July 30, 2017

እግዚአብሔርን የሚመስሉ የሚሰደዱበት ምክኒያት

በእውነትም በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ። 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡12
እግዚአብሔርን መስለው ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ፡፡ የስደቱን ምክኒያት ማወቅ በስደት እንድንፀና ያስችለናል፡፡ 
ህይወታችን እንግዳ ስለሚሆን ነው፡፡
እግዚአብሔርን መምሰላችን የሚታወቀው አስተሳሰባችን ፣ አነጋገራችን ፣ ፍቅራችንና ኑሮዋችን ለአለም እንግዳ በመሆኑ ነው፡፡ እግዚአብሔርን የማያውቁ ሰዎች የለመዱት ስለስጋ ማሰብን ነው፡፡ ከጠዋት እስከማታ ስጋቸውን እንዴት እንደሚያስደስቱ ያስባሉ፡፡ እኛ ደግሞ እግዚአብሄርን በኑሮዋችን እንዴት እንደምናስደስተው የመንፈስን ነገር እናስባለን፡፡ የእነርሱ ፍላጎትና የእኛ ፍላጎት እጅግ ይለያያል፡፡ እነርሱ ዋጋ የሚሰጡትን ነገር እኛ እንንቀዋልን፡፡ ስለዚህ ይቃወሙናል ያሳድዱናል፡፡   
እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ። ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው። ሮሜ 8፡5-6
አለምን ስለማንመስል ከአለም ስለምንለይ ነው፡፡
በአለም ያለው ባህል በስጋ ምኞት መመራት ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚመስል ሰው የሚመራው በመንፈስ ፍቃድ ነው፡፡ አለምን ስለማንመስል በዚህም ከሰዎች ስለምንለይ ከሌላ አለም እንደመጡ ሰዎች እንደ እንግዳና መጤ በመታየታችን እንሰደዳለን፡፡
ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም። 1ኛ ዮሃንስ 2፡15-16
ብርሃናችን ጨለማውን ስለሚገልጠው ነው
በብርሃን ስንኖር ጨለማውን እንገልጠዋለን፡፡ ሃጢያትን የሚወዱ ሰዎች ደግሞ ጨለማቸው ሲገለጥ ደስ አይላቸውም፡፡ ስለዚህ ይቃወሙናል ያሳድዱናል፡፡
ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው። ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፤ ዮሃንስ 3፡19-20
ከፍ ያለው ህይወታችን ሲያዩ ስለሚሳቀቁ ነው፡፡
እግዚአብሔር የሚመስሉ ሰዎች የሚሰደዱት ከፍ ያለ የህይወት ደረጃ ስለሚኖሩ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በሃጢተያት ውስጥ የሚኖሩትን ሰዎች ውርደት ያጋልጣል፡፡ ክርስትና ምንም የሚወጣለት ነገር የለም ፡፡ እግዚአብሔርን መምሰል ምንም አይወጣለትም፡፡ እግዚአብሔርን በመምሰል በንፅህና የሚኖር ሰው ሲያዩ አለማዊያን ጉድለታቸ ይታያቸዋል፡፡ ንስሃ ገብተው ተዋርደው እነርሱም እግዚአብሔርን ለመምሰል እስካልወሰኑ ድረስ በቅናት እግዚአብሔርን የሚመስሉትን ይቃወማሉ ያሳድዳሉ፡፡
የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና። በዚህም ነገር ወደዚያ መዳራት ብዛት ከእነርሱ ጋር ስለማትሮጡ እየተሳደቡ ይደነቃሉ፤ 1 ጴጥሮስ 4፡3-4
ወደመንግስተሰማያት አትሄዱም የሚል መልክት ስለሚሰጣቸው ነው፡፡
እግዚአብሄርን መፍራታችን እነርሱ አለመፍራታቸው ያስፈራቸዋል፡፡ በንፅህና መኖራችን እነርሱ በንፅህና አለመኖራቸው ያሳቅቃቸዋል፡፡ የኑሮዋችን ንፅህናን አይተውና የእነርሱን ኑሮ አይተው በራሳቸው እኔስ ወደ መንግስተሰማያት አልሄድም ብለው በራሳቸው ይፈርዳሉ፡፡ ኑሮዋችን ተመልሱ በእንደዚህ አይነት ኑሮ ወደ መንግስተሰማያት አትሄዱም ብሎ በዝምታ ይወቅሳቸዋል፡፡
በመጥፎና በጠማማ ትውልድ መካከል ያለ ነቀፋ የዋሆችም ነውርም የሌለባቸው የእግዚአብሔር ልጆች እንድትሆኑ ሳታንጐራጉሩ ክፉም ሳታስቡ ሁሉን አድርጉ፤ በእነርሱም መካከል የሕይወትን ቃል እያቀረባችሁ በዓለም እንደ ብርሃን ትታያላችሁ፥ ስለዚህም በከንቱ እንዳልሮጥሁ በከንቱም እንዳልደከምሁ በክርስቶስ ቀን የምመካበት ይሆንልኛል። ፊልጵስዩስ ሰዎች 2፡14-16
ሰይጣን ስለማይታገሰን ነው፡፡
ሰይጣን የእግዚአብሔር ጠላት የህይወት ጠላት የእኛ ጠላት ስለሆነ የእግዚአብሔርንመለክ በምድር ከላይት ማየት አይፈልግም፡፡  ሃብታም ብንሆን ወይም ዝነኛ ብንሆን ሰይጣን አይደንቀውም እግዚአብሔርን መምሰላችን ግን እረፍት አይሰጠውም፡፡ ሃብታችንን ግን እግዚአብሔርን መምሰል ላይ ካዋልነው አይታገሰውም፡፡
ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን። 1ኛ ዮሃንስ 5፡19
እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና። እኔ ግን እውነትን የምናገር ስለ ሆንሁ አታምኑኝም። ዮሃንስ 8፡ 44-45
ያም ሆነ ይህ ሰይጣን ስለፈቀድል "አስኮናኞች ኑሩ" ስላለን ሳይሆን የምንኖረው በግድ ነው፡፡ ሰይጣን ወደደም ጠላም በአሸናፊነት እንኖራለን፡፡
ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው። 1ኛ ዮሐንስ 5፡4
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እግዚአብሔር #ጌታ #መከተል #መከተል #ስደት #መከራ #ብርሃን #ጨለማ #ንፅህና #መምሰል #እግዚአብሔርንመምሰል #ቃል #ተማሪ #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #ደቀመዝሙር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ነፍስንመካድ #መፅሃፍቅዱስ #ተከታይ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Saturday, July 29, 2017

በተግባር እግዚአብሔርን መምሰል

እግዚአብሔርን መምሰል እንደ እግዚአብሔር ማሰብ ነው
አንድ ሰው ሲናገር የእግዚአብሔርን ቃል የሚያስብና የሚያሰላስል ሰው እንደእግዚአብሔር ያስባል በማለት የእግዚአብሔርን ቃል ማሰብ እግዚአብሔርን እንደምንመስል እንዴት እንደሚረዳን ተናገረ፡፡
የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ሮሜ 12፡2
በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ። ኤፌሶን 4፡23-24
እግዚአብሔርን መምሰል እግዚአብሔር እንደሚያየው ማየት ነው
እግዚአብሔርን የምንመስለው በእይታችን ነው፡፡ አግዚአብሔር የሚያየውን ካየን እግዚአብሔርን እንደምሳለን፡፡ የእግዚአብሔር እይታ በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ ተቀምጧል፡፡ የእግዚአብሔር እይታ የእግዚአብሔር ቃል እይታ ነው፡፡ ነገሮችን እንደእግዚአብሔር ቃል ካየን እግዚአብሔር የሚየየውን በማየት እግዚአብሔርን እንመስላለን፡፡ እግዚአብሔር እንደሚያየው ካላየን እግዚአብሔርን መምሰል በፍጹም አንችልም፡፡
እንግዲህ ሁልጊዜ ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና በሥጋ ስናድር ከጌታ ተለይተን በስደት እንዳለን የምናውቅ ከሆንን፥ 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡6-7
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ሮሜ 10፡17
እግዚአብሔርን መምሰል እግዚአብሔር እንደሚወደው መውደድ ነው
የእግዚአብሔር ፍቅር የእንካ በእንካ ፍቅር አይደለም፡፡ የእግዚአብሔር ፍቅር የሚሰጥ የሚያካፍል የሚራራ ጠላቶቹን የሚወድ ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለመምሰል በፍቅሩ እርሱን መምሰል አለብን፡፡
የሚወዱአችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ? አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተ ፍጹማን ሁኑ። ማቴዎስ 5፡46-48
ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል። እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም፤ እርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ሆኖአል። 1ኛ ዮሃንስ 4፡11-12
እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥ ኤፌሶን 5፡1
እግዚአብሔርን መምሰል እግዚአብሔር እንደሚናገረው መናገር ነው፡፡
ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር፤ . . . ክብርና ሥልጣን እስከ ዘላለም ድረስ ለእርሱ በሚሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን። 1ኛ ጴጥሮስ 4፡11
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እግዚአብሔር #ጌታ #መከተል #መከተል #መምሰል #እግዚአብሔርንመምሰል #ቃል #ተማሪ #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #ደቀመዝሙር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ነፍስንመካድ #መፅሃፍቅዱስ #ተከታይ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Friday, July 28, 2017

እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር

እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ። 1ኛ ጢሞቴዎስ 3፡16
ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ነው፡፡
እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ። እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። ዘፍጥረት 1፡26-27
ሰው በሃጢያት ምክኒያት ያጣው በጣም ወሳኝና አስፈላጊ ነገር የእግዚአብሄርን መልክና ክብር ነው፡፡
ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ ሮሜ 3፡23
ኢየሱስ ወደ ምድር የመጣው በሃጢያት ምክኒያት የጠፋውን የእግዚአብሄርን መልክ ለመመለስ ነው፡፡
ኢየሱስን የተቀበልን ሁላችን ከሁሉም ነገር በላይ አላማችን እና ግባችን እግዚአብሄርን መምሰል መሆን አለበት፡፡
የእግዚአብሄር ፀጋ ለሁላችን የተዘጋጀው እግዚአብሄርን እንድንመስል ነው፡፡
ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤ ቲቶ 2፡11-13
እግዚአብሄርን እንድንመስል የሚያስፈልገን ሁሉ ተሰጥቶናል፡፡
የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። 2ኛ ጴጥሮስ 1፡2-3
የማንኛውም አገልጋይ ተልእኮ ሰዎች እግዚአብሄርን እንዲመስሉ ማስተማርና መርዳት ነው፡፡ ሐዋሪያው ጳውሎስ የተላከው ሰዎችን እግዚአብሄርን ወደ መምሰል እንዲመራ መሆኑን ስለአገልግሎቱ ይመሰክራል፡፡
የእግዚአብሔር ባሪያና የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ፥ በእግዚአብሔር ለተመረጡት እምነት እንዲሆንላቸው በዘላለምም ሕይወት ተስፋ እንደ አምልኮት ያለውን እውነት እንዲያውቁ የተላከ፤ ቲቶ 1፡1
መፅሃፍ ቅዱስ የሚያስጠነቅቀው የአምልኮ መልክ ያላቸውን ሃይሉን ግን የካዱትን ነው፡፡
የአምልኮት መልክ አላቸው ኃይሉን ግን ክደዋል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ። 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡5
እግዚአብሄርን መስለው የሚኖሩ ሰዎች እንደሚሰደዱ መኝሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡ እግዚአብሄርን መሰለው ለሚኖሩ ሰዎች ነገሮች ቀላል አይሆኑም፡፡
በእውነትም በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ። 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡12
እግዚአብሄርን መምሰል ነገሮችን የማግኛ መንገድ አይደለም፡፡ እግዚአብሄርን መምሰል የመጠቀሚያ መንገድ አይደለም፡፡ እግዚአብሄርን መምሰል በራሱ ግብ ነው፡፡ እግዚአብሄርን መምሰል ወደ ጥቅም መሸጋገሪያ መንገድ ሳይሆን ራሱ ጥቅም ነው፡፡ እግዚአብሄርን መምሰል ወደ እድል መተላለፊያ መንገድ ሳይሆን ራሱ እድል ነው፡፡
ኑሮዬ ይበቃኛል ለሚለው ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፤ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡6
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እግዚአብሔር #ጌታ #መከተል #መከተል #መምሰል #እግዚአብሔርንመምሰል #ቃል #ተማሪ #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #ደቀመዝሙር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ነፍስንመካድ #መፅሃፍቅዱስ #ተከታይ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Wednesday, July 26, 2017

የአዲስ ኪዳን ነቢያት !

በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር መንፈስ የሚያርፈው በጥቂት ሰዎች ላይ ነበር፡፡ በብሉይ ኪዳን በእግዚአብሔር መንፈስ የሚቀቡት ነቢያት ፣ ነገስታትና በካህናት ብቻ ነበሩ፡፡ ሌላው የእግዚአብሔር ህዝብ ከእግዚአብሔር መጠየቅ ቢፈልግ ወደ እነዚህ ወደ ነቢያት ፣ ወደ ካህናትና ወደነገስታት ነበር የሚሔደው፡፡ ስለዚህ ነው የብሉይ ኪዳን ሰዎች ስለህይወት ጥያቄያቸው እግዚአብሔርን መጠየቅ ሲፈልጉ ነቢያትን የሚፈልጉት፡፡
. . . ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ። ዮሃንስ 14፡15-17
ኢየሱስ በመስቀል ላይ የሃጢያት እዳችንን ከከፈከና ወደሰማይ ካረገ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ወርዷል፡፡ ኢየሱስን እንደ አዳኝ እና ጌታ የተቀበሉት ሁሉ የእግዚአብሔርን መንፈስ ይቀበላሉ፡፡
ጴጥሮስም፦ ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ። የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ ጌታ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉ ሁሉ ነውና አላቸው። ሐዋርያት 2፡38-39
አሁን በአዲስ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን በተቀበሉ ሰዎች ሁሉ ውስጥ ይኖራል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን በተቀበሉ ሰዎች ሁሉ ውስጥ ስለሚኖር በአዲስ ኪዳን ሰዎች እግዚአብሔርን መጠየቅ ሲፈልጉ ሲፀልዩና መንፈስ ቅዱስን ሲሰሙ እንጂ ወደ ነቢያት ሲሔዱና እግዚአብሔር ስለእኔ ምን አለህ ብለው ነቢያትን ሲጠይቁ አንመለከትም፡፡ አሁን የእግዚአብሔር መንፈስ በሁላችን ውስጥ ይኖራል፡፡
የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን? 1ኛ ቆሮንቶስ 3፡16
በአዲስ ኪዳን ሁላችንም ተቀብተናል፡፡ በአዲስ ኪዳን ጌታን በተቀበልን በሁላችን ውስጥ የእግዚአብሔር ቅባት ይኖራል፡፡
እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም ታውቃላችሁ። እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ። 1ኛ ዮሐንስ 2፡20፣27
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የመንፈስፍሬ #ቅባት #መንፈስቅዱስ #የእግዚአብሔርመንፈስ #መሪ #ቤተመቅደስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #የእግዚአብሔርህይወት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Tuesday, July 25, 2017

የመንግስቱ ኢኮኖሚ - ኢንቨስትመንት

ኢንቨስትመንት ማለት በአንድ አትራፊ ነገር ላይ መዋእለ ኑዋይን ማፍሰስ ማለት ነው፡፡
በተለይ ገንዘባችንን ለእግዚአብሄር ቤት ሰጥተን ፣ መሰረታዊ ፍላጎታችንን አሟልተን የሚተርፈውን ገንዘብ መልሰን ኢንቨስት ብናደርገው ተጨማሪ ውጤት ይሰጠናል፡፡
ገንዘብን ጥሩ ወለድ በሚሰጥበት ባንክ በማስቀመጥ ጥሩ የወለድ ትርፍ ማግኘት ያቻላል፡፡
ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፥ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር። ማቴዎስ 25፡27
እኛን በግል የማይፈልገን እንደ አክሲዮን በመግዛት ገቢያችንን ማሳደግ እንችላለን፡፡ እንዲሁም ንብረት በመግዛትና በማከራየት በመሳሰሉት ላይ ኢንቨስት ብናደርገው ስራው እኛን በግል ሳይፈልገንና ተቀጣሪ ሳያደርገን ገቢያችንን ያሳድጋል፡፡ እንዲሁም እኛን በግል የማይፈልግ ኢንቨስትመንት ስራ መስራት ባልቻልንበት ጊዜ እንኳን ገንዘባችን ለእኛ ስለሚሰራ ገቢያችን አይቋረጥም፡፡    
ኢንቨስትመንት ተቀጥረን ከምንሰራበት ከምናገኘው ገንዘብ በተጨማሪ እኛን በግል የማይፈልገን ኢንቨስትመንትና ትርፍ ይኖረናል ማለት ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ የግል ስራችንን ብንሰራ እንኳን ከስራችን ጋር ተያያዥነት ያላቸው ስራዎች ላይ ኢንቨስት በማድረግ የገቢያችንን አይነትና መጠን ማብዛት እንችላለን፡፡
ለምሳሌ ጋራዥ ያለው ሰው ተጨማሪ ገንዘቡን የተበላሸ መኪና ገዝቶ በመጠገን መኪና በማሻሻጥ በመሳሰኩት ላይ ተጨማሪ ገንዘብ ኢንቨስት ቢያደርግ ተጨማሪ ትርፍ ያገኛል ለእግዚአብሄርም መንግስት የሚሰጠው ገንዘብ ይበዛል፡
የበጎችህን መልክ አስተውለህ እወቅ፥ በከብቶችህም ላይ ልብህን አኑር፤ ባለጠግነት ለዘላለም አይኖርምና፥ ዘውድም ለትውልድ ሁሉ አይጸናምና። ደረቅ ሣር በታጨደ ጊዜ፥ አዲስ ለምለም በታየ ጊዜ፥ ከተራራውም ቡቃያ በተሰበሰበ ጊዜ፥ በጎች ለልብስህ ፍየሎችም የእርሻ ዋጋ ይሆናሉ። ለሲሳይህ ለቤተ ሰቦችህም ሲሳይ ለገረዶችህም ምግብ የፍየል ወተት ይበቃል። ምሳሌ 2713
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ኢንቨስትመንት #ገቢ #ብልፅግና #የብልፅግናወንጌል #ስራ #ትጋት #በረከት #ስኬት #ስምረት #መሰረታዊፍላጎት #ጥበብ #ሁሉየእናንተነውና #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #የተትረፈረፈህይወት #መፅሃፍቅዱስ #መድከም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Monday, July 24, 2017

የመንግስቱ ኢኮኖሚ - ገንዘብን ማስቀመጥ

በምድር ስንኖር በጥበብ መኖር እጅግ ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ከገንዘብና ከሃብት በላይ እንዴት እንደምናስተዳደረው ማወቅ ገንዘቡን ለሚገባው አላማ እንድናውለው ይረዳል፡፡ ጥበብ ከብዙ ውጣ ውረዶች ይጠብቀናል፡፡
በወርቅና በብር ከመነገድ ይልቅ በእርስዋ መነገድ ይሻላልና። ምሳሌ 3፡14
ገንዘብን ማጠራቀም ወይም መጠባበቂያ ገንዘብን ማስቀመጥ በጣም ጠቃሚ በመሆኑ ካላስፈላጊ ውጣ ውረዶች ያድነናል፡፡ አንዳንድ ወር ወጭው ይበዛል፡፡ ሌላው ወር ደግሞ ወጭው ያንሳል፡፡ በዚህ መሰረታዊ ፍላጎታችንን ካሟላን በኋላ የግዴታ የቀረውን ገንዘብ ሁሉ በቅንጦት ላይ ማዋልና መጨረስ የለብንም፡፡ ከመሰረታዊ ፍላጎት ተረፍ ያለ ገንዘብ በሚመጣ ጊዜ ወደፊት ፍላጎት እንዳለ አውቀን የተረፈውን ገንዘብ አጥፍቶ አለመጨረስና መያዝ ያስፈልጋል፡፡
ያለንን ገንዘብ ሁሉ አጥፍቶ አለመጨረስ መፅሃፍ ቅዱሳዊ ጥበብ ነው፡፡
የከበረ መዝገብና ዘይት በጠቢብ ሰው ቤት ይኖራል፤ አእምሮ የሌለው ሰው ግን ይውጠዋል። ምሳሌ 21፡20
ገቢዎች ይለዋወጣሉ፡፡ ገቢ ሲለዋወጥ ኑሮዋችንም አብሮ ከፍና ዝቅ እንዳይል ገንዘብ ተረፍ ብሎ በሚለመጣበት ጊዜ ለወደፊት ማስቀመጥ ይጠቅማል፡፡    
በበጋ የሚያከማች ልጅ አስተዋይ ነው፤ በመከር የሚተኛ ግን እርሱ ራሱን ያስነውራል። ምሳሌ 10፡5
ከመሰረታዊ ፍላጎት የተረፈውን ስናስቀምጠው ነው በተሻለ ነገር ላይ ማፍሰስ የምንችለው፡፡ ስናጠራቅም ብቻ ነው ገቢያችንን ለማስፋት በተለያዩ ነገሮች ላይ ኢንቨስት የምናደርገው፡፡  
የበጎችህን መልክ አስተውለህ እወቅ፥ በከብቶችህም ላይ ልብህን አኑር፤ ባለጠግነት ለዘላለም አይኖርምና፥ ዘውድም ለትውልድ ሁሉ አይጸናምና። ደረቅ ሣር በታጨደ ጊዜ፥ አዲስ ለምለም በታየ ጊዜ፥ ከተራራውም ቡቃያ በተሰበሰበ ጊዜ፥ በጎች ለልብስህ ፍየሎችም የእርሻ ዋጋ ይሆናሉ። ለሲሳይህ ለቤተ ሰቦችህም ሲሳይ ለገረዶችህም ምግብ የፍየል ወተት ይበቃል። ምሳሌ 27፡13
ኢየሱስ በምድር አገልግሎቱ ገንዘብ የሚጠራቀምበት ኮሮጆ ነበረው፡፡
ይሁዳ ከረጢቱን የያዘ ስለ ሆነ፥ ኢየሱስ፦ ለበዓሉ የሚያስፈልገንን ግዛ፥ ወይም ለድሆች ምጽዋት እንዲሰጥ ያለው ለአንዳንዱ መስሎአቸው ነበርና። ዮሃንስ 13፡29
ይብዛም ይነስም እንጂ ሊቆጥብ ሊያጠራቅም ሊያስቀምጥ የማይችል ሰው የለም፡፡
የከበረ መዝገብና ዘይት በጠቢብ ሰው ቤት ይኖራል፤ አእምሮ የሌለው ሰው ግን ይውጠዋል። ምሳሌ 21፡20
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ብልፅግና #የብልፅግናወንጌል #ስራ #ትጋት #በረከት #ስኬት #ስምረት #መሰረታዊፍላጎት #ጥበብ #ሁሉየእናንተነውና #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #የተትረፈረፈህይወት #መፅሃፍቅዱስ #መድከም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ