Popular Posts

Wednesday, May 30, 2018

በእምነቱ በሕይወት

እነሆ፥ ነፍሱ ኰርታለች፥ በውስጡም ቅን አይደለችም፤ ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል። ዕንባቆም 2፡4
መፅሃፍ ቅዱስ በእምነት ስለሚኖር ሰውና በእምነት ስለማይኖር ሰው እያነፃፀረ ያስተምራል፡፡ ሰዎች በምድር ላይ ወይ በእምነት ነው የሚኖሩት ወይም ደግሞ በእምነት አይደለም የሚኖሩት፡፡
በእምንት ስለመኖር ጥቅም ሲናገር በህይወት ያኖራል ይላል፡፡ በህይወት መኖር ማለት በሁሉ ነገር ህያው መሆን ማለት እንጂ በስጋ አለመሞት ማለት ብቻ አይደለም፡፡
ለምሳሌ ኢየሱስ ያለው ህይወት አለው ሲል የዘላለም ህይወትን ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሄር ህይወትን ስለማጣጣም ይናገራል፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ በእርሱ የማያምን ህይወትን አያይም ሲል በስጋ ይሞታል ማለት ሳይሆን የእግዚአብሄርን ህይወት አላማ ይስተዋል ማለት ነው፡፡ ህይወትን አያይም ማለት እግዚአብሄር በህይወት ውስጥ ያስቀመጠውን በረከት አያገኘውም ማለት ነው፡፡ ህይወትን አያይም ማለት የህይወትን እውነተኛ መልክና ጣእም አያገኘውም ማለት ነው፡፡
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ በደስታ ይኖራል ማለት ነው፡፡ በእምነት የሚኖሩ ሰዎች ለመደሰት የሆነ ነገር አይጠብቁም፡፡ በእምነት የሚኖሩ ሰዎች እነርሱን ለማስደሰት ጌታ ብቻውን በቂ ነው፡፡ በእምነት የሚኖሩ ሰዎች ለመደሰት ሌላ ሌላ ነገር መጨመር የለባቸውም፡፡
ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ። ፊልጵስዩስ 4፡4
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ ከጭንቀት በላይ ይኖራል ማለት ነው፡፡ በእምነት የሚኖር ሰው ለእርሱ የሚያስብለት እንዳለ ስለሚያምን ጭንቀት ከህይወቱ ይሞታል፡፡
እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት። 1ኛ ጴጥሮስ 5፡7
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ በሃይል ይኖራል ማለት ነው፡፡
ተስፋ የሰጠው የታመነ እንደ ሆነ ስለ ቈጠረች፥ ሣራ ራስዋ ደግሞ ዕድሜዋ እንኳ ካለፈ በኋላ ዘርን ለመፅነስ ኃይልን በእምነት አገኘች። ዕብራውያን 11፡11
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ በሃይል ይኖራል ማለት ነው፡፡ በእምነት የሚኖረ ሰው እግዚአብሄር እንዲሰራው የሰጠውን ስራ ለመስራት ምንም ሃይል አይጎድልበትም፡፡
የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።2 ጴጥሮስ 1፡2-3
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ ስኬት ይኖራል ማለት ነው፡፡ እምነት የሚመጣው የእግዚአብሄርን ቃል ከመስማት ነው፡፡ በእግዚአብሄ ቃል እምነት የሚኖር ሰው በስራው ሁሉ ፍሬያማ ይሆናል፡፡
ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል። መዝሙር 1፡2-3
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ ይድናል፤ ይገባል፤ ይወጣል፤ መሰማሪያም ያገኛል ማለት ነው፡፡  
ኢየሱስ እንዲህ አለ፤ “በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ በኩል የሚገባ ሁሉ ይድናል፤ ይገባል፤ ይወጣል፤ መሰማሪያም ያገኛል” ዮሐንስ 10፡1
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ ከጠላት ጥቃት በላይ ይኖራል ማለት ነው፡፡
በመጠን ኑሩ ንቁም፥ ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፤ በዓለም ያሉት ወንድሞቻችሁ ያን መከራ በሙሉ እንዲቀበሉ እያወቃችሁ በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት። 1ኛ ጴጥሮስ 5፡8-9
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ በክንውን ደስታ ይኖራል ማለት ነው፡፡
እኔም መልሼ፦። የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን፤ እናንተ ግን በኢየሩሳሌም እድል ፈንታና መብት መታሰቢያም የላችሁም አልኋቸው። ነህምያ 2፡20
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ በነፃነት ይኖራል ማለት ነው፡፡
በነፃነት ልንኖር ክርስቶስ ነፃነት አወጣን እንግዲህ ፀንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ! ገላትያ 5:1
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ ከሁኔታዎች በላይ ይኖራል ማለት ነው፡፡
እርሱም፦ ጸጋዬ ይበቃሃል፥ ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና አለኝ። እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ። 2ኛ ቆሮንቶስ 12፡9
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ በእርካታ ይኖራል ማለት ነው፡፡
ይህን ስል ስለ ጉድለት አልልም፤ የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል ማለትን ተምሬአለሁና። መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ። ፊልጵስዩስ 4፡11-12
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ በድፍረት ይኖራል ማለት ነው፡፡
ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም። እኛ ግን ነፍሳቸውን ሊያድኑ ከሚያምኑቱ ነን እንጂ ወደ ጥፋት ከሚያፈገፍጉ አይደለንም። ዕብራውያን 10፡38-39
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ በፍሬያማነት ይኖራል ማለት ነው፡፡ በእምነት የሚኖር ሰው የእግዚአብሄርን ቃል በየዋህነት በማድረግ ፍሬን ያፈራል፡፡
እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል። ዮሃንስ 15፡15
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ ከመቋጠር ይወጣል ፣ ረጋ ብሎ በስፋት ካለስጋት ይኖራል ማለት ነው፡፡
ወደ ሰፊ ስፍራም አወጣኝ፤ ወድዶኛልና አዳነኝ። መዝሙር 18፡19
አረማመዴን በበታቼ አሰፋህ፥ እግሮቼም አልተንሸራተቱም። መዝሙር 18፡36
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ አያፍርም አይዋረድም በእረፍት ይኖራል ማለት ነው፡፡
ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ በጽዮን ድንጋይን ለመሠረት አስቀምጣለሁ፤ የተፈተነውን፥ የከበረውን፥ መሠረቱ የጸናውን የማዕዘን ድንጋይ የሚያምን አያፍርም። ኢሳያስ 28፡16
ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል ሲል ጻድቅ ግን በእምነቱ በአሸናፊነት ይኖራል ማለት ነው፡፡
ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው። 1 ዮሐንስ 5፡4
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ስፋት #እርካታ #ፍሬያማነት #ክንውን #አሸናፊነት #በጎነት #ቅን #እምነት #ፅድቅ #ደስታ #ሰላም #ኢየሱስ #ጌታ #ሃይል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment