Popular Posts

Sunday, July 31, 2016

ከፊታችን ያሉ መልካም ቀኖች

እግዚአብሄር መልካም ነው፡፡ ለእኛ ለልጆቹ ሁል ጊዜ የተሻለ ነገር አለው፡፡ ከፊታችን እስከዛሬ ካየናቸው የተሻሉና መልካም ቀኖች እየመጡ ነው፡፡

እነዚህን መልካም ቀኖች ማየት የሚፈልግ ማድረግ ያለበት ነገሮች አሉ፡፡ መልካም ቀኖች ይመጣሉ ግን እነዚህን ቀኖች ማየትና አለማየት የእኛ ፋንታ ነው፡፡ በአንደበታችን የምናደርገው ነገር መልካሞቹን ቀኖች እንድናይ ወይም እንዳናይ ያደርጉናል፡፡

ህይወትን የሚወድና መልካሙንም ቀኖችን ማየት የሚፈልግ ሰው በንግግሩ መጠንቀቅ አለበት፡፡ ሰው እንደፈለገ እነደልቡ እየተናገረ መልካሞችን ቀኖች አያለው ማለት ዘበት ነው፡፡


ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤ 1ኛ ጴጥሮስ 3፡10

ምክኒያቱም አንደበት እሳት ነው ፡፡ ካላግባብ ከተጠቀምንበት የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፡፡

አንደበትም እሳት ነው። አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፥ ያዕቆብ 3፡6


አንደበታችንን የማንገታ ከሆንን ሊረዳን ወደ እውነት ሁሉ ሊመራን የተሰጠንን ቅዱሱን የእግዚአብሄርን መንፈስ እናሳዝናለን፡፡

ሰው ራሱን ከመልካም ቀኖች ውድቅ ላለማድረግ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ሊከለክል ግዴታ ነው፡፡


ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ። ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ። ኤፌሶን 4፡29-30

ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤ 1ኛ ጴጥሮስ 3፡10
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ


#ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #አንደበት #ምላስ #መልካምቀኖች #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Saturday, July 30, 2016

እንደ ንጽሕት ድንግል

በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና፤ ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ። 2ኛ ቆሮንቶስ 11፡2-3 
ሃሳብ በጣም ጥንቃቄ የሚፈልግ ነገር ነው፡፡ ሃሳብ ይነፃል ሃሳብ ይበላሻል፡፡ ሃሳብ ሲበላሽ ቅንነትና ንፅህና ይለወጣል፡፡ ቅን እና ንፁህ የነበረው ሰው ጠማማ እና የተጣመመ ሃሳብ ያለው ሰው ይሆናል፡፡
ሰው ሃሳቡ ሲበላሽና ቅንነቱ ሲለወጥ በእግዚአብሄር ማመኑን ያቆማል፡፡ ይህ በእግዚአብሄር ላይ ያለው እምነቱ መቀነሱ የሚታወቀው በአፉ ተናግሮት አይደለም፡፡ እግዚአብሄርን ማመን የከበደው ሰው በድርጊቱ ይታወቃል፡፡ 
ሰው ቅንነቱ ሲለወጥ ለመንፈሳዊ መሪዎች ያለው አክብሮት ይቀንሳል፡፡ ሰው ሃሳቡ ሲበላሽ ለቤተክርስቲያን ያለው መሰጠት ይቀንሳል፡፡ ለቤተክርስቲያን ገንዘቡን ሰጥቶ የማይጠግበው ሰው ቅንነቱ ሲበላሽ መጠራጠር ይጀምራል፡፡ ሰው ቅንነቱ ሲበላሽ የእግዚአብሄርን ህዝብ ማገልገል መፍራት ይጀምራል፡፡ የእግዚአብሄርን ህዝብ በትጋት በማገልገል የሚታወቀው ሰው ሃሳቡ ሲበላሽ ጊዜውንና ጉልበቱን መሰሰት ይጀምራል፡፡ ሰው ቅንነቱ ሲበላሽ ከእግዚአብሄር ህዝብ ጋር ህብረት ላለማድረግ ሰንካላ ምክኒያቶች ይበቁታል፡፡ ሰው ቅንነቱ ሲበላሽ ለሰዎች ስለጌታ ከሃጢያት አዳኝነት መናገር ይቀንሳል፡፡ ሰው ቅንነቱ ሲበላሽ ከፀሎት ይልቅ ሌሎች ነገሮች ያምሩታል፡፡ 
ጌታ እንዲነግዱና እንዲያተርፉ ንጉስ መክሊትን ስለሰጣቸው ምሳሌ ሲናገር አንድ መክሊት የተሰጠው ለንጉሱ ያለው ሃሳብ ስለተበላሸና ቅንነቱ ስለተለወጠ መክሊቱን ወስዶ ቀበረው፡፡ 
አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ። አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ። ማቴዎስ 25፡18, 24-25 
እንዲነግድ እንዲያተርፍና እንዲያድግ እንዲሾም የተሰጠውን መክሊት የቀበረው ምክኒያቱ የንጉሱን አላማ ስለተጠራጠረና ለንጉሱ ያለው ሃሳብ ሰለተበላሸ በዚያም ቅንነቱ ስለተለወጠ ነው፡፡
እግዚአብሄርን ማገልገል ታላቅ ጥቅም እና ታላቅ እድል ነው፡፡ ራሳችሁን ተመልከቱ ተመለሱም፡፡ ሃሳባችሁ እንዳይበላሽና ቅንነታችሁ እንዳይለወጥ ትጉ፡፡ ሃሳባችሁ እንዲለወጥ የሚመጣውን ማንኛውንም ሃሳብ አትቀበሉ፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ብቻ እመኑ፡፡ 
በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና፤ ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ። 2ኛ ቆሮንቶስ 11፡2-3 
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ 
#አተረፈ #ንፅህና #ቅንነት #ንጉስ #መክሊት #ኢየሱስ #ጌታ #መፅሃፍቅዱስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ስብከት #እምነት

Friday, July 29, 2016

ተቃወሙ!


የዲያቢሎስ አላማ አንድና አንድ ነው፡፡ ዲያቢሎስ ከመጣ ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ለሌላ ነገር አይመጣም፡፡   


ዲያቢሎስንብ የመጋዣው መንገድ ደግሞ በእግዚአብሄር ላይ ማመፅ ወደ እግዚአብሄር አለመጠጋትና ከሃጢያት ጋር መጫወት ነው፡፡ 


ዋነኛው ታዲያ ዲያቢሎስን የመቃወሚያው መንገድ ለእግዚአብሄር መገዛት ነው፡፡ ዲያቢሎስን የመቃወም ውጤታማው መንገድ ወደ እግዚአብሄር መቅረብ ነው፡፡ 


እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ። ያዕቆብ 4፡7-8


ልጆች ሆነን ሸንኮራ ስንመጥ የምንጥለው ምጣጭ ዝንብን ይስባል፡፡ ዝንብን መከላከያው ውጤታማው መንገድ የዝንብ ማባረሪያና መግደያ አይደለም፡፡ ምክኒያቱም ዝንብን የሚስበው ቆሻሻ ስለሆነ ቆሻሻው እስካለ ድረስ ሁሌ ዝንብ ይሳባል፡፡ ዝንብ ቆሻሻን ማሳደድ ተፈጥሮው ስለሆነ ቆሻሻን አስቀምጠን ዝንብ አይምጣ ማለት አንችልም፡፡ 


ነገር ግን ዝንብን የማባረሪያው መንገድ አካባቢን ማፅዳት ነው፡፡ አካባቢውን ከፀዳ ዝንብ ቢመጣ እንኳን የሚፈልገውን ስለማያገኝና እዚያ አካባቢ መቆየት ስራ መፍታትና ጊዜ ማባከን ስለሚሆንበት ዝንብ አይቆይም፡፡ 


እንዲሁ ሰይጣንን በህይወታችን እንዳይሰርቅ እንዳያርድና እንዳያጠፋ የምናደርግበት ዋነኛው መንገድ ሀጥያትን መፀየፍ ከክፉ የወጣትነት ምኞት መሸሽ ነው፡፡ 


ሰው ፍምን በብብቱ ታቅፎ አያቃጥለኝ ማለት እንደማይችል ሁሉ ሃጢያትን እየሰራ ሰይጣን አይስረቀኝ ማለት አይችልም፡፡ ሰው ለሰይጣን ተስማሚ ለም መሬት የሆነውን ጥላቻን በልቡ ይዞ ሰይጣን በህይወቴ አያጥፋ አይግደል የማለት አቅሙ አይኖረውም፡፡ 


ለሰይጣን ፍቱምን መድሃኒቱ እርሱን የሚስቡትን ነገሮች ሃጢያትንና ጥላቻን ከህይወት ማራቅ ነው፡፡ ሰይጣንን የመቃወሚያው መንገድ ለእግዚአብሄር እንደቃሉ መገዛትና ወደ እግዚአብሄር መቅረብ ነው፡፡ 


ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ማድረግ ቢወዱ 


ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes


#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Thursday, July 28, 2016

ሳታቋርጡ ፀልዩ



ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና። 1 ተሰሎንቄ 5፡16-18


በህይወት ማሸነፍ እንዴት ደስ የሚል ነገር ነው፡፡ ሰው በህይወቱ ሁል ጊዜ ካለማቋረጥ ማሸነፍ ይችላል፡፡
እኛ የእግዚአብሄር የክብሩ መገለጫ እቃዎች ነን፡፡ በራሳችን ምንም ማድረግ አንችልም፡፡ እግዚአብሄር ላይ በታመንን መጠን ሁሉ ግን ሁሌ እናሸንፋለን የሚሳነንም ነገር አይኖርም፡፡ 


ሳታቋርጡ ድል እንድታደርጉ ሳታቋርጡ ጸልዩ፡፡ 


መፀለይና ማሸነፍ ይቻላል፡፡ ነገር ግን ሁሌ ማሸነፍ ይቻላል? አንዳንድ ሰዎች ይህ ሊደረስበት የማይቻል ነገር እንደሆነ ያስቡታል፡፡ 


መልሱ  ግን አዎን ሳያቋርጡ በመፀለይ ሁሌ ማሸነፍ ይቻላል ነው፡፡ ማረጋገጫው ምንድነው ብሎ ለሚጠይቅ ሰው ሁሉ መልሱ እግዚአብሄር የማይቻል ነገር አያዝዝም ፡፡ እግዚአብሄር ካዘዘ ይቻላል ማለት ነው ፡፡


ሳያቋርጡ መፀለይ ማለት ሁሌ ተንበርክኮ መፀለይ ማለት ግን አይደለም፡፡ መፀለይ መንበርከክን ወይም በርን መዝጋትን ቢያጠቃልልም በእነዚህ ብቻ አይወሰንም፡፡ 


ሳያቋርጡ መፀለይ ማለት ካለማቋረጥ በእግዚአብሄር ላይ መደገፍ ፣ ካለማቋረጥ ልብን ለእርዳታ ወደ እግዚአብሄር ማንሳት እና ሌላም ስራ እየሰሩም ቢሆን ካለማቋረጥ በውስጥ ከእግዚአብሄር ጋር መነጋገር ማለት ነው፡፡ ፀሎት በውስጥ ለእርዳታ ወደ እግዚአብሄር መጮኽ ነው፡፡ 


እግዚአብሄር የልብን ጩኸት ይሰማል፡፡ 


እግዚአብሄር አንዳንዴ ብቻ ሳይሆን ሁሌ እንዲሳካልን ስለሚፈልግ ሳታቋርጡ ጸልዩ እያለ እየጋበዘን ነው፡፡
ሳናቋርጥ በመፀለይ ሳናቋርጥ እንከናወን፡፡ 


 ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ማድረግ ቢወዱ 


ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes


#ኢየሱስ #ጌታ  #ፀሎት #የእግዚአብሄርእርዳታ #የልብጩኸት #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አማርኛ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Wednesday, July 27, 2016

በምድር ተቀመጥ


በምድር ስንኖር የእግዚአብሄርን ፈቃድ በምድር እንዳንፈፅም ሊያስፈሩን የሚመጡ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡

አንዳንድ ሰው ወጥቶ ህይወትን መጋፈጥ ሲፈራ ተኝቶ መዋል ያምረዋል፡፡ ሌላው ደግሞ ቶሎ ወደ ሰማይ እንዲሄድ ይመኛል፡፡ የሆነ ቦታ ብቻ መሄድ ከምድር መውጣት ይፈልጋል፡፡

በጌታ በእየሱስ ያመነ ሰው ወደሰማይ የሚሄድበት ጊዜ አለው፡፡ ላሁን ግን የሚሰራ ስራ ስላለ በዚሁ በምድር ይቆያል፡፡

አንዳንዴ የሰዎችን ክፋት ስናይ ዘመኑ ያስፈራራናል፡፡ የፍርሃቱን ስሜት ከሰማነው ሽምድምድ አድርጎ ሊያስቀምጠን ነው የሚመጣው፡፡

የኑሮውን ውድነት ስታስብ እንዴት ነው የሚኖረው ትል ይሆናል፡፡ የእግዚአብሄር አምላካዊ መልስ ግን ይህ ሁሉ ችግሮች ባሉባት በዚችሁ ምድር ተቀመጥ ታምነህ ተሰማራ ነው፡፡

እግዚአብሄር ግን የሚፈልገው በዚህ በእንግድነት አገራችን በምድር ላይ ታምነን እንድኖር ነው፡፡

እዚሁ ጠላት ባለበት ምድር ላይ ኖረህ እንድታሸነፍ ነው እንጂ  ጌታ ከአለም እንድትወጣ አይደለም የሚፈልገው፡፡

እግዚአብሄርን ከማመናችን በፊት ምድር እየተሻሻለች መሄድ የለባትም፡፡ ከማሸነፋችን በፊት የሰዎች ባህሪ መሻሻል የለበት፡፡ እንዲሳካልን ሰዎች ሁሉ በእግዚአበሄር ማመን የለባቸውም፡፡

አለም ግን ወዴት እየሄደች ነው ብለን በሞራል መላሸቅ መገረማችንን እያለ እንዲያውም እየበዛ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል፡፡

በእግዚአብሔር ታመን፥ . . . በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ ነው የሚለው፡፡

·        እዚሁ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማ አህዛብን በሚሸፍንበት ነው ብርሃንህን ሊያወጣ የሚፈልገው፡፡

ብርሃን መቷልና የእግዚአብሄርም ክብር መቷልና ተነሽ አብሪ። እነሆ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማ አህዛብን ይሸፍናሉ ነገር ግን በአንች ላይ እግዚአብሄር ይወጣል ክብሩም በአንች ላይ ይታያል፡፡ መዝሙር 60፡1-2

·        በሞት ጥላ መካከል ነው አብሮህ መሆን የሚፈልገው፡፡

በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል። መዝሙር 23፡4

·        በጠላቶችህ ፊት ለፊት ነው ራስህን በዘይት መቀባት የሚፈልገው፡፡

በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ፤ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው። መዝሙር 23፡5

·        እዚሁ ደረቁ ምድር ላይ መቶ እጥፍ እንድታፈራ የሚፈልገው፡፡

ይስሐቅም በዚያች ምድር ዘርን ዘራ፥ በዚያች ዓመትም መቶ እጥፍ አገኘ እግዚአብሔርም ባረከው። ዘፍጥረት 26፡12

እግዚአብሄር ግን ታምነን እንድኖር ነው የሚፈልገው፡፡ ለዚህ ነው በምድር ተቀመጥ ታምነህ ተሰማራ የሚለው፡፡

በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ። መዝሙር 37፡3

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ማድረግ ቢወዱ


#ድፍረት #መተማመን  #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #አማርኛ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

በምድር ተቀመጥ


በምድር ስንኖር የእግዚአብሄርን ፈቃድ በምድር እንዳንፈፅም ሊያስፈሩን የሚመጡ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡

አንዳንድ ሰው ወጥቶ ህይወትን መጋፈጥ ሲፈራ ተኝቶ መዋል ያምረዋል፡፡ ሌላው ደግሞ ቶሎ ወደ ሰማይ እንዲሄድ ይመኛል፡፡ የሆነ ቦታ ብቻ መሄድ ከምድር መውጣት ይፈልጋል፡፡

በጌታ በእየሱስ ያመነ ሰው ወደሰማይ የሚሄድበት ጊዜ አለው፡፡ ላሁን ግን የሚሰራ ስራ ስላለ በዚሁ በምድር ይቆያል፡፡

አንዳንዴ የሰዎችን ክፋት ስናይ ዘመኑ ያስፈራራናል፡፡ የፍርሃቱን ስሜት ከሰማነው ሽምድምድ አድርጎ ሊያስቀምጠን ነው የሚመጣው፡፡

የኑሮውን ውድነት ስታስብ እንዴት ነው የሚኖረው ትል ይሆናል፡፡ የእግዚአብሄር አምላካዊ መልስ ግን ይህ ሁሉ ችግሮች ባሉባት በዚችሁ ምድር ተቀመጥ ታምነህ ተሰማራ ነው፡፡

እግዚአብሄር ግን የሚፈልገው በዚህ በእንግድነት አገራችን በምድር ላይ ታምነን እንድኖር ነው፡፡

እዚሁ ጠላት ባለበት ምድር ላይ ኖረህ እንድታሸነፍ ነው እንጂ  ጌታ ከአለም እንድትወጣ አይደለም የሚፈልገው፡፡

እግዚአብሄርን ከማመናችን በፊት ምድር እየተሻሻለች መሄድ የለባትም፡፡ ከማሸነፋችን በፊት የሰዎች ባህሪ መሻሻል የለበት፡፡ እንዲሳካልን ሰዎች ሁሉ በእግዚአበሄር ማመን የለባቸውም፡፡

አለም ግን ወዴት እየሄደች ነው ብለን በሞራል መላሸቅ መገረማችንን እያለ እንዲያውም እየበዛ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል፡፡

በእግዚአብሔር ታመን፥ . . . በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ ነው የሚለው፡፡

·        እዚሁ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማ አህዛብን በሚሸፍንበት ነው ብርሃንህን ሊያወጣ የሚፈልገው፡፡

ብርሃን መቷልና የእግዚአብሄርም ክብር መቷልና ተነሽ አብሪ። እነሆ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማ አህዛብን ይሸፍናሉ ነገር ግን በአንች ላይ እግዚአብሄር ይወጣል ክብሩም በአንች ላይ ይታያል፡፡ መዝሙር 60፡1-2

·        በሞት ጥላ መካከል ነው አብሮህ መሆን የሚፈልገው፡፡

በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል። መዝሙር 23፡4

·        በጠላቶችህ ፊት ለፊት ነው ራስህን በዘይት መቀባት የሚፈልገው፡፡

በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ፤ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው። መዝሙር 23፡5

·        እዚሁ ደረቁ ምድር ላይ መቶ እጥፍ እንድታፈራ የሚፈልገው፡፡

ይስሐቅም በዚያች ምድር ዘርን ዘራ፥ በዚያች ዓመትም መቶ እጥፍ አገኘ እግዚአብሔርም ባረከው። ዘፍጥረት 26፡12

እግዚአብሄር ግን ታምነን እንድኖር ነው የሚፈልገው፡፡ ለዚህ ነው በምድር ተቀመጥ ታምነህ ተሰማራ የሚለው፡፡

በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ። መዝሙር 37፡3

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ማድረግ ቢወዱ


#ድፍረት #መተማመን  #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #አማርኛ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

Tuesday, July 26, 2016

የኢየሱስ ስም

  • ከዘላለም ፍርድ የሚያድነው የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡
በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት እንዲቀበል ነቢያት ሁሉ ይመሰክሩለታል። ሐዋርያት 10:43 ከሃጢያት ሊያድን የሚችለው የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡ ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ። ማቴዎስ 1፡21 መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና። ሃዋሪያት 4፡12 በሰይጣን ላይ ስልጣን ያለው የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡
  • ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ዮሃንስ 1፡12 መሰበክ ያለበት የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡ በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ጽፎአል። ሉቃስ 24:47
በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ከስም ሁሉ በላይ ስልጣን ያለው የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ ፊልጵስዩስ 2፡9
  • ወደ እግዚአብሄር የምንቀርብት ብቸኛ ስም የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡
እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም፤ አብም በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ እንዲሰጣችሁ፥ ልትሄዱና ፍሬ ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ። ዮሃንስ 15፡16
  • ለሚጠሩት ሁሉ ባለጠጋ የሆነ ስም የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡
በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤ ሮሜ 10፡12 ጉልበት ሁሉ የሚንበረከክለት የኢየሱስ ስም ብቻ ነው፡፡ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥ ፊልጵስዩስ 2፡10
  • በመፅሃፍ ቅዱስ የታዘዝነው የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በእየሱስ ስም አድርጉት ተብለን ነው፡፡
በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት። ቈላስይስ 3:17
 ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ 
 

Monday, July 25, 2016

ብፁሃን የዋሆች

የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና። ማቴዎስ 5፡5 
የዋህ በአማርኛ መዝገበ ቃላት " ገር ፣ ቅን ፣ መሠሪነት የክፋት ብልጠት የሌለው " በማለት ተተርጉሟል፡፡ 
የዋህ ማለት በሰው ላይ ክፉ ለማድረግና ለግሉ አላግባብ ለመጠቀም አቅሙና ችሎታው እያለው ሰውን ላለመጉዳት የሚጠነቀቅ ሃይሉን ለክፋት የማይጠቀምና ከክፋት የሚከለከል ሰው ማለት ነው፡፡
የዋህነት ደካማነት አይደለም፡፡ የዋህነት እንዲያውም ብርታት ነው ፡፡ ጀግና የሚባለው ራሱን የማይገዛ ሰው ሳይሆን ክፋት ለማድረግ ሲፈተን ራሱን የሚገዛ ለክፋት እጅ የማይሰጥ ብርቱ ሰው ነው፡፡ 
የዋህነት ሞኝነት አይደለም፡፡ እንዲያውም የዋህነት ሁኔታውን ጥበበኛው እግዚአብሄር እንዲይዘው ለጌታ የመተው ብልጠት ነው፡፡ የዋህነት ራስ የመበቀልን ፈተና በማለፍ ብድራቱን ለሚመልሰው ለእግዚአብሄር እድሉን መስጠት ነው፡፡ 
ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና። ሮሜ 12:19 
የዋህነት የሰው ቁጣ የእግዚአብሔርን ፅድቅን እንደማይሰራ በመረዳት ለእግዚአብሄር ገዢነት እውቅና መስጠት ነው፡፡ የሰው ቍጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ አይሠራምና። ያዕቆብ 1፡20 
የዋህነት "ብትበደሉ አይሻልምን?" የሚለውን የእግዚአብሄርን ቃል አምኖ ሌላውን ከመበደል ይልቅ ራስ በመበደል ከእግዚአብሄር ሽልማት መቀበል ነው፡፡ እንግዲህ ፈጽሞ የእርስ በርስ ሙግት እንዳለባችሁ በእናንተ ጉድለት ነው። ብትበደሉ አይሻልምን? ብትታለሉስ አይሻልምን? 1ኛ ቆሮንቶስ 6፡7
የዋህነት ለእግዚአብሄር አምላክነት እውቅና መስጠት ነው፡፡ የዋህነት እግዚአብሄርን ምንጭ ማድረግ ነው፡፡ የዋህነት አላግባብ ከሰው አለመጠበቅ ነው፡፡ የዋህነት የስኬት ቁልፍ ያለው በምድር እንዳይደለ ማወቅ ነው፡፡ የዋህነት በጥበብ በሃይል በባለጠግነት አለመመካት ነው፡፡ ይልቁንም የዋህነት ፅድቅና ፍርድን ምህረትን የሚያደርግ እግዚአብሄር መሆኑን በማወቅ መመካት ነው፡፡ 
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ ነገር ግን የሚመካው። ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር፦ ኤርምያስ 9፡23-24 
የዋህነት እግዚአብሄርን ያስደስተዋል፡፡ በየዋህነት እግዚአብሄርን ካስደሰትነው ምድርን እንወርሳለን፡፡ የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና። ማቴዎስ 5፡5 
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ 
 

Sunday, July 24, 2016

ዘመኑን ግዙ


እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፤ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ። ኤፌሶን ሰዎች 5፡15-16 
ብዙ ሰዎች የሚሳሳቱትና ከስኬት የሚወድቁት ቀኖቹ ለእነርሱ እንደሚሰራላቸው ባለማስተዋል በማሰብ ነው፡፡ ሰዎች ዘመኑ መልካም እንደሆነ ነገር ዘና ሲሉና በማስተዋል ካልነቁ እግዚአብሄር ወዳየላቸው የክብር ደረጃ መድረስ ያቅታቸዋል፡፡ 
ቀኖቹ ክፉዎች ናቸው፡፡ በጥንቃቄ ሳንኖር ቀኖቹ በራሳቸው ዝም ብለው ለእኛ ይሰራሉ ብለን ከጠበቅን አንሳሳታለን፡፡ ቀኖቹ በራሳቸው ለእኛ በጎነት አይሰሩም፡፡ መልካሙ የምስራች ግን እነዚህን ክፉ ቀኖች ለእኛ እንዲሰሩ ማድረግ መቻላችን ነው፡፡ እነዚህን ክፉ ቀኖች መግዛት የሚቻልበትና ለእኛ ስኬት እንዲሰሩ የሚደረግበት መላ አለ፡፡ 
ክፉ ቀኖች ለእኛ እንዲሰሩ ብሎም እግዚአብሄር ወዳየልን የህይወት አላማ መድረስ የምንችለው በጥበብ ጥንቃቄ ስንመላለስ ነው፡፡ 
የእግዚአብሄር ቃል በሚሰጠን ጥበብ ከተመላለስን እነዚህን ክፉ ቀኖች ገልብጠን ለእኛ በጎነት እንዲሰሩ ማድረግ እንችላለን፡፡ በሚበልጥ በእግዚአብሄር ጥበብ ከኖርን ክፋታቸው በእኛ ላይ እንዳይሰራ አድርገን ከሁኔታዎች ሁሉ በላይ መኖር እንችላለን፡፡ 
ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል። 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡15 
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ 
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢነት #ጥበብ #አቢይዋቁማ

Saturday, July 23, 2016

ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ

የእግዚአብሄርን ፈቃድ መረዳት የመሰለ ነገር የለም፡፡የህይወታችን ጥማት ጌታን መከተልና እግዚአብሄርን ማስደሰት በመሆኑ የእግዚአብሄር ፈቃድን ስናገኝ እንደሰታለን፡፡ የእግዚአብሔር ፈቃድ በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነ ነው፡፡ ሮሜ 12፡2
 
ሁል ጊዜ ደስ ይበላችሁ የሚለው የእግዚአብሄ ፈቃድ በመፅሃፍ ቅዱስ በማያሻማ ሁኔታ ግልፅ ተደርጎ ተፅፎዋል፡፡ 
 
ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና። 1ኛ ተሰሎንቄ 5፡16-18
 
እውነት ነው ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ የሚለው ትእዛዝ ሁል ጊዜ ቀላል አይደለም፡፡ ቤጌታ ግን ሁል ጊዜ ደስ መሰኘት ይቻላል፡፡ ግን እንዴትና በምን ምክኒያት ነው ሁል ጊዜ በጌታ ደስ መሰኘት የሚቻለው?
ሁልጊዜ ደስ መሰኘት የሚቻለው እግዚአብሄር በታላቅ ዋጋ የገዛን የህይወታችን ባለቤት መሆኑን በማመን ነው፡፡ እግዚአብሄር ባለቤት ስለሆነ ደግሞ እኛ እንኳን ግድ ባይለን ስለ እያንዳንዱ የህይወታችን አቅጣጫ ዝርዝር ጉዳይ ግድ ይለዋል፡፡ 
 
በዋጋ ተገዝታችኋልና . . . ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 6፡19-20
 
ሁልጊዜ መደሰት የሚቻለው እግዚአብሄር በአላማ እንደወለደን ስንረዳና ኢየሱስን ለሃጢያታችን እስኪሰዋ ድረስ ለእግዚአብሄር በጣም አስፈላጊ ሰዎች እንደ ሆንን ስናስታወስ ነው፡፡ ፍቅር የሆነው እግዚአብሄር ወዶናል፡፡ 
 
እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤ 1ኛ ዮሐንስ 3፡16
 
ሁልጊዜ በእግዚአብሄር የምንደሰተው እርሱ እረኛችን ስለሆነና በሞት ጥላ መካከል እንኳን ብናልፍ እርሱ ከእኛ ጋር ስለሚሆን ነው፡፡ 
 
እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥. . . በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፡፡ መዝሙር 23፡1፣4
 
ሁል ጊዜ በጌታ ደስ የሚለን ለእኛ የሚያስባትን ሃሳብ እርሱ ስለሚያውቀው ነው፡፡ የህይወት እቅዳችን እርሱ ጋር ስላለና በጥንቃቄም እየፈፀመው ስለሆነ ነው፡፡ 
 
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ኤርሚያስ 29፡11
 
ሁልጊዜ ደስ የሚለን ለእኛ የሚያስብልን የተባለ ሁሉ በእጁ ሁሉ በደጁ የሆነ አባት በሰማይ ስላለን ነው፡፡ 
 
እርሱ ስለእናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት፡፡ 1ኛ ጴጥሮስ 5:7
 
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ 
 

Friday, July 22, 2016

ታላቅ ነው !

ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና። 1ኛ ዮሐንስ 4:4
በክርስትና ህይወታችን የትም አትሄድም ፣ በላሁህ ፣ ጣልኩህ ፣ አሁንስ አታመልጥም ብለው የሚያስፈራሩ ብዙ ነገሮች ይነሳሉ፡፡ በአካባቢያችን ያሉትን ሁኔታዎች በማሳየት እግዚአብሄር የተናገረን ነገር እንደማይሆንና ሊፈፀም እንደማይችል ሊያስረዱንና ሊያሳምኑን ይጥራሉ፡፡
ክርስትናን በሚገባ ለመኖር አቅም እንደሌለን የአለም ሃይል እንደሚያሸንፈን በብዙ ሊያሳምኑን የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡
ነገር ግን . . .
እግዚአብሄር በህይወታችን ያስቀመጠውን አላማ ሊቋቋም የሚችል ምንም ሃይል አልነበረም የለም ወደፊትም አይኖርም፡፡ እየሱስ በምድር ሲኖር አሸንፎ የእግዚአብሄርን ፈቃድ በሙላት እንደፈፀመ እኛንም ሊያሸንፈን የሚችል በፊታችን የሚቆም ምንም ሃይል የለም፡፡
በምድር ያለው ተግዳሮት እንደማናሸንፍ ማረጋገጫ ሊሆን በፍፁም አይችልም፡፡ እንዲያውም የተግዳሮት መኖር ወደአሸናፊነት እየገሰገስን እንደሆንንና ልናሸንፍ እንደምንችል ማረጋገጫው ነው፡፡
ከእኛ የተነሳ ሳይሆን በውስጣችን ካለው የተነሳ እንደምናሸንፍ ሳይታለም የተፈታ ነገር ነው፡፡
በእኛ ያለው በአለም ካለው ማንኛውም ተግዳሮትና ሃይል ሁሉ ይልቅ ታላቅ ነው፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር ቢያደርጉ

Thursday, July 21, 2016

የአእምሮ ገዳም

የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ሮሜ 12፡2
ሰዎች እግዚአብሄርን በመፈለጋቸውና ከዚህ አለም ነፃ ለመውጣት በመፈለጋቸው ከአለም መሸሽና ገዳም መግባት ይፈልጋሉ፡፡ ይህንንም ለማድረግ ገዳም ቢገቡም ጠልተውት የመጡት ክፉ የሃጢያት ሃሳብ ተከትሎዋቸው ይመጣል፡፡ በዚህም ምክኒያት ምንም ከከተማ ወጥተው ገዳም ቢገቡም የአለማዊነት አስተሳሰብ በአእምሮአቸው እስካለ ድረስ ከአለም መለየት ያቅታቸዋል፡፡ 
መፅሃፍ ቅዱስ አለምን ስለማንመስልበት ገዳም ይናገራል፡፡ ይህን አለም አለመምሰል የምንችለው ብቸኛው መንገድ አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል ሲታደስና የአለም ክፉ አስተሳሰብ በልባችን ቦታ ሳያገኝ ሲቀር ብቻ ነው ፡፡ 
አለማዊ የሚያደርገን ከተማ መኖራችን ወይም ከሰው ተለይተን አለመኖራችን ሳይሆን አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል አለመታደሱና ከሃጢያት ሃሳብ ጋር መኖራችን ነው፡፡ አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል ሲቃኝና ሲለወጥ በህይወታችን ለአለማዊነት ምንም ስፍራ አይኖርም፡፡
አለማዊ ከሚያደርገን ከሃጢያት ሃሳብ ጋር እስካለን ድረስ ከከተማ ወጥተን ከሰው ተለይተን ገዳምም ብንገባ ከሃጢያት ባርነት አናመልጥም፡፡ ምክኒያቱም አለማዊ ከሚያደርገን የሃጢያት ክፉ ሃሳብ አእምሮዋችን እስካልታደሰ ድረስ አለምን አለመምሰል አንችልም፡፡ 
ነገር ግን ባለንበት በስራችን በምንኖርበት ቦታ ሁሉ በእግዚአብሄር ቃል አእምሮአችንን ካደስነው ይህን አለም ሳንመስል እግዚአብሄርን እያስደሰትን መኖርና ማገልገል እንችላለን፡፡

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ! 

Wednesday, July 20, 2016

መሪዎች ያስፈልጉናል - መሪ እንሁን


በጋራ ወደ ውጤት ለመድረስ መሪ ወሳኝ ነው፡፡ ካለ መሪ ሰዎች አንድነትም ሆነ የጋራ ቅንጅት ብሎም ወደ ውጤትና ስኬት ሊደርሱ አይችሉም፡፡ 

 
በቤተሰብና በቤተክርስቲያን የእግዚአብሄር ሰዎች ካሉበት ቦታ አግዚአብሄር ወዳየላቸው የክብር ቦታ እንዲደርሱ መሪነት አማራጭ የሌለው ፍላጎት ነው፡፡ 


በራእይ የሚያስተባብር መሪ በሌለበት ህዝብ መረን ይወጣል፡፡ 


መሪነት ደግሞ ስልጣን ወይም ማዕረግ ሳይሆን ተፅእኖ ነው ፡፡ የመሪዎች ህይወታቸው ፡ መሰጠታቸው ፡ ቅናታቸውና  ትጋታቸው በተመሪዎች ላይ ተፅእኖ ያደርጋል ሰዎችም በደስታ ይከተሏቸዋል፡፡ 


መሪዎች ራእይ ያላቸው መንገዱን የሚያውቁ ሌሎችን በድፍረት በመምራት ወደ ውጤትና ስኬት የሚያደርሱ ናቸው፡፡ 


እንደ እነዚህ አይነት መሪዎች ያስፈልጉናል፡፡ እንደ እነዚህ አይነት መሪዎች እንሁን ፡፡ 


ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ያድርጉ!