Popular Posts

Wednesday, February 7, 2018

በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ

ከሰው ይልቅ የእግዚአብሔር ሞኝነት ይጠበባልና
ከሰው ይልቅ የእግዚአብሔር ሞኝነት ይጠበባልና፥ የእግዚአብሔርም ድካም ከሰው ይልቅ ይበረታልና። 1ኛ ቆሮንቶስ 1፡25
የሰው ጥበብ ሲጨርስ የእግዚአብሄር ጥበብ ይጀምራል፡፡ የእግዚአብሄር ሞኝነት የሰውን እጅግ ታላቅ ጥበብ ይበልጠዋል፡፡ የእግዚአብሄር ድካም ከሰውን እጅግ ታላቅ ሃይል ይበረታል፡፡
ከሰው እጅግ ታላቅ ጥበብ ይልቅ የእግዚአብሄር ሞኝነት ይሻላል፡፡ በሰው እጅግ ታላቅ ጥበብ ከመደገፍ ይልቅ በእግዚአብሄር ሞኝነት መደገፍ ይሻላል፡፡
የእግዚአብሄር ማስተዋል ጥልቅ ነው፡፡
አላወቅህምን? አልሰማህምን? እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው፤ አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም። ኢሳያስ 40፡28
ስለዚህ ነው ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም የሚለው፡፡
ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 8፡1
በራስ ማስተዋል እንደመደገፍ አደገኛ ነገር የለም፡፡ የእኛ ማስተዋል ልንደገፍበት የሚበቃ አይደለም፡፡ ሰው በሸንበቆ ላየ ዘና ብሎ እንደማይደገፍ ሁሉ የእኛ ማስተዋል ለመደገፍ የማይበቃ ደካማ ነው፡ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ በራስህ ማስተዋል አትደገፍ የሚለው፡፡ የትኛውም የእኛ ማስተዋል ልንደገፍበት በቂ አይደለም፡፡ የእኛ እጅግ ታላቁ ማስተዋል የእግዚአብሄርን ጥበብ አይደለም ሞኝነቱን አይደርስበትም፡፡
በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል። ምሳሌ 3፡5-6
ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ በመንገድህ ሁሉ አርሱን እወቅ የሚለው፡፡ በመንገድህ ሁሉ ለእርሱ አዋቂነት እውቅና ስጥ፡፡ በመንገድህ ሁሉ እኔ ለራሴ ከማውቀው በላይ እርሱ ለእኔ ያውቃል በል፡፡ በመንገድህ ሁሉ እኔ የማላውቀው ነገር አለ እርሱ ሁሉን ያውቃል በል፡፡ በመንገድህ ሁሉ እኔ ልሳሳት እችላሁ አርሱ ግን አይሳሳትም በል፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እውቀት #ጥበብ #ማስተዋል #ቃል #መልካም #መታመን #መደገፍ #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት  #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ  #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment