Popular Posts

Saturday, February 3, 2018

አዘነላቸው ድውዮቻቸውንም ፈወሰ

ብዙ ሕዝብም ባየ ጊዜ፥ እረኛ እንደ ሌላቸው በጎች ተጨንቀው ተጥለውም ነበርና አዘነላቸው። ማቴዎስ 9፡36
ኢየሱስ በምድር ላይ ያገለገለው ብዙዎችን ነፃ ያወጣው በአዘኔታና በርህራሄ ተመርቶ ነው፡፡ ርህራሄ ወደ ትክክለኛው አገልግሎት ይመራል፡፡ ርህራሄ ወደ እግዚአብሄር ሃሳብ ይመራል፡፡ ርህራሄ ወደፈውስ ወደነኛ ማውጣት ወደአገልግሎት ይመራል፡፡
እግዚአብሄር የሚሰራው በፍቅር ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚንቀሳቀሰው በርህራሄ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሲራራላችሁ ህይወታችሁን ይለውጣል፡፡ እግዚአብሄር ህይወታችሁን እንዲለወጥ ሲፈልግ ለሚያገለግላችሁ አገልጋይ ርህራሄውን ያካፍለዋል፡፡
እግዚአብሄር አገልጋዩን ለፈውስና ለነፃ ማውጣት ሊጠቀም ሲል ለአገልጋዩ ርህራሄ ይሰጣል፡፡ እግዚአብሄር እንዲጠቀምብህ ካስፈለገ ርህራሄ ያስፈልግሃል፡፡ ለምታገለግለው ህዝብ ርህራሄ ከሌለህ በከንቱ ትለፋለህ፡፡ የምታገለግለውን ህዝብ የምታገለገልው ካለፍቅርና ካለርህራሔ እንደስራ ከሆነ አገልግሎቱ ቢቀርብህ ይሻላል፡፡
በፍቅር የማይደረግ አገልግሎትም እንኳን ቢሆን አይጠቅምም፡፡ ካለ ምህረትና ርህራሄ የሚደረግ አገልግሎት ሁሉ ከንቱ ነው፡፡
በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ። ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል፥ ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም። 1ኛ  ቆሮንቶስ 13፡1-3
የምታገለግላቸውንና የምትጠቅማቸውን ሰዎች ለማገልገል ፍቅር ያስፈልግሃል፡፡ ፍቅር ከሌለህ እግዚአብሄር አይጠቀምብህም፡፡ ፍቅርና ርህራሄ ካልመራህ እግዚአብሄር አልመራህም፡፡ ፍቅር ሃይልህ ካልሆነ እግዚአብሄር ሃይል አይሆንም፡፡ በፍቅርና በርህራሄ ካልሆነ እግዚአብሄር ካንተ ጋር አይሆንም፡፡
አለምን የምናሸንፍበት እምነት የሚሰራው በፍቅር ነው፡፡ እምነት እንዲሰራና በእምነት ሰዎችን ለመጥቀምና ለማገለግል ፍቅር ይጠይቃል፡፡ እምነት ከፍቅር ተለይቶ አይሰራም፡፡
በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ፥ በፍቅር የሚሠራ እምነት እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና። ገላትያ 56
ወጥቶም ብዙ ሕዝብ አየና አዘነላቸው ድውዮቻቸውንም ፈወሰ። ማቴዎስ 14፡14
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ምህረት #ርህራሄ #ፍቅር #መውደድ  #አዘነላቸው #ነፃማውጣት #አገልግሎት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #ፍርሃት #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #መውደድ #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment