Popular Posts

Wednesday, February 28, 2018

በእምነት ስላልተዋሐደ አልጠቀማቸውም

ለእነዚያ ደግሞ እንደ ተነገረ ለእኛ የምስራች ተሰብኮልናልና፤ ዳሩ ግን የሰሙት ቃል ከሰሚዎቹ ጋር በእምነት ስላልተዋሐደ አልጠቀማቸውም። ዕብራውያን 4፡2
እግዚአብሄር የእኩል እድል አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር የሰውን ፊት አይቶ አያዳላም፡፡ እግዚአብሄር ለእያንዳንዱ ሰው እኩል እድል ይሰጣል፡፡ ያለተሳካለት ሰው እግዚአብሄርን ጥፋተኛ ማድረግ አይችልም፡፡ ያልተሳካለት ሰው ራሱን መመርመር አለበት፡፡
ወደእግዚአብሄር እረፍት ለመግባት ስላልተሳካላቸው እስራኤላዊያን መፅሃፍ ሲናገር የምስራቹ ቃል ለእነርሱም እንደተሰበከላቸው ይናገራል፡፡ ነገር ግን ልዩነት ያመጣው የሰሙት ቃል ከሰሚዎችቹ ጋር በእመነት መዋሃዱ እና አለመዋሃዱ ነው፡፡ ሁለት ክርስትያኖች የእግዚአብሄርን ቃል እኩል ሊሰሙ ይችላሉ ነገር ግን በሁለቱ ላየ የሚያመጣው ውጤት ይለያል፡፡
የእግዚአብሄር ቃል ሁሉ በማንኛውም ሰው ላይ በማንኛውም ሁኔተያ ላይ የሚሰራ ነው፡፡
ልዩነቱ የእግዚአብሄር ቃል ሳይሆን ልዩነቱ የእግዚአብሄርን ቃል አሰማም ነው፡፡ እስራኤላዊያን የእምነቱ ቃል ከሰሚዎቹ ጋረ አልተወቃሃደም ስለዚህ አልጠቀማቸወም፡፡ የእግዚአብሄር ቃል የሚጠቅመን የእግዚአብሀዌር ቃል ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ከሰሚዎቹ ጋረ ሲዋሃድ ብቻ ነው፡፡
የእግዚአብሄር ቃል ከሰሚዎቹ ጋር እንዳይዋሃድ የሚያደርጉ አምስት እንቅፋቶች
1.      ከልብ አለመሆን
እግዚአብሄር ንጉስ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ስንሰማ እንደእግዚአብሄር ቃል ካልተቀበልነው አይጠቅመንም፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ስንሰማ እንደታሪክ ከሰማነው አይጠቅመንም፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ስንሰማ እንደ ንጉስ ቃል ከልባችን ልንሰማው ይገባል፡፡ ሱነማዊትየዋ ሴት ኢየሱስ ልጅዋን እስኪፈውስላት አልለቀቀችውም፡፡ ሱነማይትዋ ሴት ወደ ኢየሱስ ስትመጣ ከልብዋ ነበር፡፡  
የመንግሥትን ቃል ሰምቶ በማያስተውል ሁሉ፥ ክፉው ይመጣል፥ በልቡ የተዘራውንም ይነጥቃል፤ በመንገድ ዳር የተዘራው ይህ ነው። ማቴዎስ 13፡19
እነሆም፥ ከነናዊት ሴት ከዚያ አገር ወጥታ፦ ጌታ ሆይ፥ የዳዊት ልጅ፥ ማረኝ፤ ልጄን ጋኔን ክፉኛ ይዞአታል ብላ ጮኸች። እርሱ ግን አንዳች አልመለሰላትም። ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው፦ በኋላችን ትጮኻለችና አሰናብታት እያሉ ለመኑት። እርሱም መልሶ፦ ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ። እርስዋ ግን መጥታ፦ ጌታ ሆይ፥ እርዳኝ እያለች ሰገደችለት። እርሱ ግን መልሶ፦ የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም አለ። እርስዋም፦ አዎን ጌታ ሆይ፤ ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ አለች። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ፦ አንቺ ሴት፥ እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች። ማቴዎስ 15፡22-28
2.     የኑሮ ጭንቀት
የእግዚአብሄር ቃል በህይወታችን የእረፍት ፍሬ እንዳያፈራ የሚያደርገው የኑሮ ጭንቀት ነው፡፡ የኑሮ ጭንቀት ከሰማነው በቁማችን ሊውጠንና ከንቱ ሊያፈደርገን የሚችል ትልቅ ሃይል ያለው እንቅፋት ነው፡፡ ብዙ ሰዎች እግዚአብሄርን ከማገልገል የተመለሱት በኑሮ ፍርሃት ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች ጌታን ቢያገለግሉም ያን ያህል ውጤታማ እንዳይሆኑ ያደረጋቸው የኑሮ ሃሳብና የባለጠግነት ምቾት ነው፡፡  
በእሾህ መካከልም የወደቀ እነዚህ የሚሰሙት ናቸው፤ መንገዳቸውንም ሄደው በሕይወት ዘመን በአሳብና በባለ ጠግነት ምቾት ይታነቃሉ፥ ሙሉ ፍሬም አያፈሩም። ሉቃስ 8፡14
3.     እንደ ሌላ አማራጭ መስማት
ሌላ አማራጭ ይዞ የእግዚአብሄርን ቃል እንደባጣ ቆየኝ መፈለግ በእምነት እነዳይዋሃደንና እንዳይጠቅመን ወደእረፍትም እንዳንገባ ያደርጋል፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል እንደመጨረሻ አማራጭ ካየነው አይጠቅመንም፡፡ የእግዚአብሄር ቃል እንደመጀመሪያ አማራጭ ሊታይ ይገባዋል፡፡
ያው የሚሰራው የእግዚአብሄር ቃል በእምነት እንዳይዋሃደን የሚሆንበት ምክኒያት ቃሉን በሁለት ሀሳብ መስማት ነው፡፡ ቃሉን እንደ ሌላ አማራጭ መስማት ቃሉ በእምነት ከእኛ ጋር እንዳይዋሃድ ያደርጋል፡፡ ቃ በእምነት ካልተዋሃደን ወደእረፍት አንገባም፡፡  
ነገር ግን በምንም ሳይጠራጠር በእምነት ይለምን፤ የሚጠራጠር ሰው በነፋስ የተገፋና የተነቃነቀ የባሕርን ማዕበል ይመስላልና። ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው። ያዕቆብ 1፡6-8
4.     የእግዚአብሄር ቃል ለአእምሮ እውቀት ብቻ መስማት መፈለግ
የእግዚአብሄርን ቃል እንደሚሰራ ቃል ካለሰማነው ለአእምሮ ማስፊያ  እንደሰው ቃል እና እንደ ታሪክ ከሰማነው ለአእምሮዋችን ይጠቅማል አእምሮዋችንን ያሰፋል ነገር ግን በቃሉ ውስጥ ወደ ተቀመጠው እረፍት መግባት በፍፁም እንችልም፡፡ በዩኒቨርስቲዎች መፅሃፍ ቅዱስን እንደ ፊዚክስና እንደ ሂሳብ የሚያጠኑ ነገር ግን ከሚሰጠው ቃሉ ከሚሰጠው የህይወት እረፍት የራቁ ብዙ ሰዎች ይገኛሉ፡፡
ስለዚህም የመልእክትን ቃል እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ከእኛ በተቀበላችሁ ጊዜ፥ በእውነት እንዳለ በእናንተ በምታምኑ ደግሞ እንደሚሠራ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንጂ እንደ ሰው ቃል አድርጋችሁ ስላልተቀበላችሁት፥ እኛ ደግሞ እግዚአብሔርን ሳናቋርጥ እናመሰግናለን። 1ኛ ተሰሎንቄ 2፡13
5.     የእግዚአብሄርን ቃል ለመታዘዝ አለመስማት
የእግዚአብሄርን ቃል ስንሰማ ለመታዘዝ ተዘጋጅተን መሆን አለበት፡፡ ነገር ግን ለመታዘዝ በሆነ በተጠንቀቅ ካልሰማነ እስከምንታዘዘው አይዋሃደንም አይጠቅመንም፡፡ ወደ እረፍቱ ለመግባት የእግዚአብሄር ቃል በህይወታችን ውስጥ ገብቶ ተዋህዶ ሊጠቅመን ያስፈልጋል፡፡
ይህን ብቻ ከእናንተ እንድማር እወዳለሁ፤ በሕግ ሥራ ወይም ከእምነት ጋር በሆነ መስማት መንፈስን ተቀበላችሁን? እንግዲህ መንፈስን የሚሰጣችሁ በእናንተም ዘንድ ተአምራት የሚያደርግ፥ በሕግ ሥራ ነውን ወይስ ከእምነት ጋር በሆነ መስማት ነው? ገላትያ 3፡2-3
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ጭንቀት #ከልብ #አማራጭ #መታዘዝ #የኑሮሃሳብ #ብልፅግና #የባለግነትምቾት #ዘር #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment