Popular Posts

Tuesday, February 27, 2018

በእግዚአብሔር እመኑ

ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ በእግዚአብሔር እመኑ። ማርቆስ 11፡22
በእግዚአብሔር እመኑ
ጌታን ለሚያውቅ ሰው በእግዚአብሄር እመን የሚለው ምክር ከንቱ ምክር ሊመስል ይችላል፡፡ ነገር ግን ጌታን የሚያውቅ ሰው ስለመዳኑ ኢየሱሰን እንደአዳኙ ተቀበለ ማለት እምነት ሁሉ አለው ማለት አይደለም፡፡ ለመዳን ከእግዚአብሄር ጋር ለመታረቅ ብቻ ሳይሆን ለእያንዳንዱ እርምጃችን እምነት ያስፈልገናል፡፡
በእግዚአብሔር እመኑ
ክርስትያን ነን ማለት ከመቀፅበት ለሁሉም ነገር እምነት ይኖረናል ማለት አይደለም፡፡ በህይወታችን ክፍሎች እምነት እየኖረን የምንሄደው የእግዚአብሄርን ቃል ስለዚያ የህይወታችን ክፍል የሚናገረውን ሰምተን ስናምንና በቃሉ እውነት ላይ ስንቆም እግዚአብሄር በቃሉ ያለን ነገር ሁሉ ይሆናል፡፡ ስለአገልግሎታችን ስለቤተሰባችን ስለስራችን ስለትዳራችን ስለጤናችን የእግዚአብሄር ቃል ምን እንደሚል ፈልገን ካገኘንና እምነት ከመጣልን በእምነት የማይቻለን ነገር አይኖርም፡፡  
በእግዚአብሔር እመኑ
በአንዱ የክርስትና ህይወቱ ክፍል እምነት ያለው ሰው ስለዚያ ነገር የእግዚአብሄርን ቃል በመስናት እምነት ካልመጣለት በስተቀር በሌላው የክርስትና የህይወት ክፍሉ እምነት ሊጎድለው ይችላል፡፡
በእግዚአብሔር እመኑ
ክርስትያኖች ሆነን በተለይ በሳይንስና የቴክኖሎጂ ዘመን ነገሮችን ቴክኒካዊ እናደርጋቸዋለን፡፡ ከማመን ይልቅ ነገሮችን በአእምሮዋችን ለመፍታት እንሞክራለን፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ትእዛዝ ግን በእግዚአብሄር እመኑ የሚል ነው፡፡
በእግዚአብሔር እመኑ
እግዚአብሄርን ማመንን የሚተካው ምንም ነገር የለም፡፡
ከምናስበው በላይ ብዙ ነገሮች መንፈሳዊ ናቸው፡፡ ከምናስበው በላየ ብዙ ነገሮች እምነት ይጠይቃሉ፡፡ ከምናስበው በላይ ብዙ ነገሮች ቁልፋቸው መንፈሳዊ ነው፡፡ የምድር የስኬት ቁልፍ ማንም ባለጠጋ ጋር ማንም ሃያል ጋር ማንም ጠቢብ ጋር የለም፡፡ የስኬት ቁልፉ ያለው እግዚአብሄር እጅ ነው፡፡ በህይወት መልስ የሌለው ጥያቄ የለም ነገር ግን በእግዚአብሄር ማመን ይጠይቃል፡፡
በእግዚአብሔር እመኑ
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው፦ ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ኤርሚያስ 9፡23-24
ካለ እምነት እግዚአብሄርን ማስደሰት አይቻልም፡፡ ከእግዚአብሄር እጅ ስኬትን ለመቀበል እምነት ይጠይቃል፡፡ እግዚአብሄርን ፈልጎ ዋጋን ለመቀበል እምነት ይጠይቃል፡፡
ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ዕብራውያን 11፡6
ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ። ዮሐንስ 14፡1
በእግዚአብሔር እመኑ
 ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ልብ #ማመን #ቃል #መናገር #ስሜት #ሁኔታ #አካባቢ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አለማመን #ጥርጥር #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment