Popular Posts

Sunday, February 4, 2018

በእኔ ላይ ያለው ዓላማውም ፍቅር ነው

በእኔ ላይ ያለው ዓላማውም ፍቅር ነው። መኃልየ መኃልይ  24
እግዚአብሄር ፍቅር ነው፡፡ እግዚአብሄር መልካም አምላክ ነው፡፡
እግዚአብሔር ፍቅር ነውና። 1ኛ ዮሐንስ 4፡8
እግዚአብሄር ሰውን በመልኩና በአምሳሉ የፈጠረው እርሱን የሚመስል ሊያናግረውና ሊረዳው የሚችል ስለፈለገ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው በፍቅር ነው፡፡
እግዚአብሄር ለሰው ያለው አላማ ፍቅር ነው፡፡ እግዚአብሄር ለሰው ያለው እቅድ የሰላም እቅድ ነው፡፡ እግዚአብሄር ፍቅር ስለሆነ እግዚአብሄር ለሰው ያለው አላማ ፍፃሜና ተስፋ ያለው እቅድ ነው፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ኤርሚያስ 29፡11
እግዚአብሄር የሚያየን በፍቅር አይን ነው፡፡
የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ ከክብሩ በኋላ ወደ በዘበዙአችሁ አሕዛብ ልኮኛል፤ የሚነካችሁ የዓይኑን ብሌን የሚነካ ነውና። ዘካርያስ 2፡8
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #እይታ #አላማ #ተስፋ #ፍፃሜ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ተሰፋ #ፍፃሜ #የእግዚአብሄርሃሳብ #የእግዚአብሄርእቅድ #የእግዚአብሄርፈቃድ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment