Popular Posts

Monday, February 26, 2018

ለሚጠፋ መብል አትስሩ

ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፤ እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና። ዮሐንስ 6፡27
በምድር ላይ ለሚጠፋ መብል የሚሰራ ሰው አለ፡፡ በምድር ላይ ለማይጠፋ መብል የሚሰራ ሰው አለ፡፡
ለሚጠፋ መብል የሚሰራ ሰው የሚያስበው የምድሩን ብቻ ነው፡፡ ለሚጠፋ መብል የሚሰራ ሰው ቅድሚያ የሚሰጠው የምድሩን ኑሮ ምቾት ብቻ ነው፡፡ ለሚጠፋ መብል የሚሰራ ሰው እይታው አጭር ነው፡፡ ለሚጠፋ መብል የሚሰራ ሰው ከምድር ኑሮ ያለፈ የሰማዩን ማየት አይችልም፡፡
ሰው ለሚጠፋ መብል የሚሰራው እምነት ሲያጣ ነው፡፡ ሰው ለሚጠፋው መብል የሚሰራው መንፈሳዊውን ማየት ሲሳነው ነው፡፡
ለማይጠፋ መብል ለመስራት እምነት ይጠይቃል፡፡ ለማይጠፋ መብል ለመስራት ራስን መካድ ይጠይቃል፡፡ ለማይጠፋ መብል ለመስራት ነፍስን መካድ ይታወቃል፡፡ ለማይጠፋው መብል ለመስራት የሚታየውን አለማየት ይጠይቃል፡፡ ለማይጠፋው መብል ለመስራት የማይታየውንም ማየት ይጠይቃል፡፡
የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። 2ኛ ቆሮንቶስ 4፡17-18
የሚጠፋ መብል አለ፡፡ የማይጠፋ መብል አለ፡፡ የሚጠፋው መብል ይጠፋል፡፡ ምክኒያቱም መብል ለሆድ ነው፡፡ ሆድም ለመብል ነው፡፡ ሁለቱም ጊዜያዊ ናቸው ይጠፋሉ፡፡
መብል ለሆድ ነው፥ ሆድም ለመብል ነው፤ እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥13
አንዳንድ ሰዎች ሰርተው ለፍተው ዋጋቸውን በምድር ይቀበላሉ፡፡ የልፋታቸውና የስራቸው ዋጋ በምድር ላይ ብቻ ይቀራል፡፡ ለምድር ክብርና ለምድር ጥቅም የሚሰሩ ሰዎች ሁሉ ዋጋቸውን በምድር ተቀብለው አወራርደው ጨርሰው ነው ከምድር የሚለቁት፡፡ ለሚጠፋ መብል የሚሰሩ ሰዎች ከምድር የሚሄዱት የሰጡትን እያንዳንዷን ተቆጣጥረው መልሰው ተቀብለው ነው፡፡   
እንግዲህ ምጽዋት ስታደርግ፥ ግብዞች በሰው ዘንድ ሊከበሩ በምኩራብ በመንገድም እንደሚያደርጉ በፊትህ መለከት አታስነፋ፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል። ማቴዎስ 6፡2
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #የሚጠፋመብል #የባለጠግነትማታለል #የኑሮሃሳብ #የማይጠፋ #መብል #የምድርክብር #ሆድ #እምነት #የባለግነትምቾት #ራስንመካድ #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment