Popular Posts

Thursday, February 1, 2018

ማትረፊያ ነው

ኑሮዬ ይበቃኛል ለሚለው ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፤ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡6
እግዚአብሄርን መምሰል ክብር ነው፡፡ እግዚአብሄርን መምሰል በራሱ የከበረ ግብ ነው፡፡ ጌታን መከተል ምንም ምንም ሳይጨምር በረከት ነው፡፡
ለጌታ መኖራችን ሙሉ እንዲሆን በዚያ ምክኒያት የምናገኘው ጥቅም መኖር የለበትም፡፡ ጌታን መከተላችን ትክክል መሆኑን ለማሳየት ብዙ ገንዘብ አያስፈልገንም፡፡ ለጌታ መኖራችን በብዙ ሃብትና ሃይል አይደገፍም አይታወቀም፡፡ እግዚአብሄርን መምሰል ጥሩ ሆኖ እንዲታይ የሚጣፍበት ምንም ዝና አያስፈልገውም፡፡ እግዚአብሄርን መምሰል በራ ሙሉ ከመሆኑ የተነሳ በየትም ሃብትና ዝና አይሟላም፡፡
እግዚአብሄርን መምሰል የመጨረሻ ግብ ነው፡፡ እግዚአብሄርን መምሰልን የሚበልጠው ሌላ ከፍ ያል ግብ የለም፡፡ እግዚአብሄርን መምሰል የክብር ጥግ ነው፡፡
ሰይጣን ይህንን ያውቀዋል፡፡ ሰይጣን ጌታን መከተላችን ብቻ የክብር ጣራ መሆኑን ያውቀዋል፡፡ ሰይጣን ውሸታም ስለሆነ እኛ ጋር ሲመጣ ግን ጌታን ብለሽ ምን አገኘሽ በማለት እግዚአብሄርን መምሰል በራሱ ማትረፊያ እንዳልሆነ ሌላ ትርፍ እንደሚያስፈልገው ይዋሻል፡፡ ሰይጣን ከእግዚአብሄርን መምሰል በላይ የክብር ደረጃ እንደሌላ ያውቃል እኛ ጋር ግን ሲመጣ እግዚአብሄርን መምሰል የማትረፊያ መንገድ እንጂ በራሱ ትርፍ እንዳልሆነ በክፋት ሊያሳምነን ይሞክራል፡፡ ሰይጣን እግዚአብሄርን ከመምሰላችን በላይ የሚረብሸው ነገር የለም ነገር ግን ወደእኛ ሲመጣ እግዚአብሄርን መምሰል ያጣጥለዋል፡፡ ሰይጣን ወደ እኛ ሲመጣ ግን እግዚአብሄርን መምሰል በራሱ ግብ እንዳይደለ ግን ወደግብ መድረሻ መንገድ ብቻ እንደሆነ ሊያሳምነን የማይፈነቅለው ድንጋይ የለም፡፡
በመፅሃፈ አስቴር ውስጥ ሃማ ለቤተሰቦቹ እንዴት ንጉሱ እንዳከበረው ዘርዝሮ ነገራቸው፡፡ ነገር ግን አለ መርዶኪዮስ ሳይሰግድለይት ባለመናወጥ ተቀምጦ ባየ ጊዜ ያ መርዶኪየፐስ እያለ ምን ክብር ይሆንልኛል ብሎ ተናገረ፡፡
በዚያም ቀን ሐማ ደስ ብሎት በልቡም ተደስቶ ወጣ፤ ነገር ግን መርዶክዮስ በንጉሡ በር ያለ መነሣትና ያለ መናወጥ ተቀምጦ ባየ ጊዜ ሐማ በመርዶክዮስ ላይ እጅግ ተቈጣ። ሐማ ግን ታግሦ ወደ ቤቱ ሄደ፤ ልኮም ወዳጆቹንና ሚስቱን ዞሳራን አስጠራ። ሐማም የሀብቱን ክብርና የልጆቹን ብዛት፥ ንጉሡም ያከበረበትን ክብር ሁሉ፥ በንጉሡም አዛውንትና ባሪያዎች ላይ ከፍ ከፍ እንዳደረገው አጫወታቸው። ሐማም፦ ንግሥቲቱ አስቴር ወዳዘጋጀችው ግብዣ ከእኔ በቀር ከንጉሡ ጋር ማንንም አልጠራችም፤ ደግሞ ነገ ከንጉሡ ጋር ወደ እርስዋ ተጠርቻለሁ። ነገር ግን አይሁዳዊው መርዶክዮስ በንጉሡ በር ተቀምጦ ካየሁ ይህ ሁሉ ለእኔ ምንምን አይጠቅምም አለ። አስቴር 5፡9-13
ሰይጣንም እንደዚሁ ነው አከሌን አስገዝቻለሁ እከሌ በእኔ ቁጥጥር ስር ነው ነገር ግን እከሌ ኢየሱስን እየተከተለ ምን ይጠቅመኛል ነው፡፡ ሰይጣን የእኛ እግዚአብሄርንም መምሰል ለእርሱ ፍፁም ሽንፈት እንደሆነ ያውቃዋል፡፡
ሰይጣን ግን ወደእኛ ሲመጣ ስለእኛ እግዚአብሄርን መምሰል የሆነ ተጨማሪ ጥቅም ካላስገኘልን እንደሳትን ነው የሚከሰን፡፡ ሰይጣን እኛጋ ሲመጣ እሺ ክርስትያን ሆነህ ምን አገኘህ ክርስትናህ ምን ጠቀመህ ነው የሚለው፡፡ መልሱ ግን ክርስትናዬ ራሱ ጥቅም ነው፡፡ ክርስትናዬ ሙሉ እንዲሆን በብዙ ገንዘብ እና በዝና መጣፍ የለበትም፡፡ እግዚአብሄርን መምሰል የመጨረሻ የክብር ጣራ ነው፡፡
የክርስትና የመጨረሻው ደረጃ ቢሊየነርነት ወይም ትሪሊየነርነት በመሰረታዊ ፍላጎት ረክቶና ራስን አማጥኖ ጌታን መከተል ነው፡፡
ኑሮዬ ይበቃኛል ለሚለው ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፤ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡6
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እግዚአብሔር #ጌታ #መከተል #መከተል #መምሰል #እግዚአብሔርንመምሰል #ቃል #ማትረፊያ #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #ደቀመዝሙር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ነፍስንመካድ #መፅሃፍቅዱስ #ተከታይ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment