Popular Posts

Saturday, July 22, 2017

የመንግስቱ ኢኮኖሚ - መስጠት

እኛ የተፈጠርነው ለእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡ የተፈጠርነው ሌሎችን ለማገልገል ነው፡፡ ገንዘብን መስጠት ገንዘብን እንደመስራት በጣም ወሳኝ የሆነ ልምምድ ነው፡፡
እግዚአብሄር የሚሰጠን ገንዘብ የምንበላውና የምንዘራው ነው፡፡
ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱም የምትዘሩትን ዘር ይሰጣችኋል ያበረክትላችሁማል፥ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያሳድጋል፤ 2ኛ ቆሮንቶስ 9፡10
እግዚአብሄር የሚሰጠን ገንዘብ ነፍሳችንንና ሌሎችን የምናገለግልበት ገንዘብ ነው፡፡ በእጃችን ያለው ገንዘብ የእኛ ብቻ አይደለም፡፡
በእጃቸን ያለው ገንዘብ ባለቤቶች ሳንሆን አስተዳዳሪዎች ነን፡፡ ለእግዚአብሄር ክብር እንደመፈጠራችን መጠን በእጃችን ያለው ገንዘብ እግዚአብሄር እንደወደደ እንደእግዚአብሄር ቃል ትእዛዝ የምናስረዳድር ደጋግ መጋቢዎች ነን፡፡
ልዩ ልዩን የእግዚአብሔርን ጸጋ ደጋግ መጋቢዎች እንደ መሆናችሁ፥ እያንዳንዳችሁ የጸጋን ስጦታ እንደ ተቀበላችሁ መጠን በዚያው ጸጋ እርስ በርሳችሁ አገልግሉ፤
እንደ ተሰጠንም ጸጋ ልዩ ልዩ ስጦታ አለን፤ . . .የሚሰጥ በልግስና ይስጥ፤ የሚገዛ በትጋት ይግዛ፤ የሚምር በደስታ ይማር። ሮሜ 12፡6፣8
በእጃችን ያለው ሁሉ የምንበላው አይደለም የምንሰጠውም እንጂ፡፡  
እግዚአብሔርን ከሀብትህ አክብር፥ ከፍሬህም ሁሉ በኵራት፤ ጐተራህም እህልን ይሞላል፥ መጥመቂያህም በወይን ጠጅ ሞልታ ትትረፈረፋለች። ምሳሌ 3፡9-10
ያለውን የሚበትን ሰው አለ፥ ይጨመርለታልም፤ ያለ ቅጥ የሚነፍግ ሰውም አለ፥ ይደኸያልም። ምሳሌ 11፡24
ሰው ደግሞ ብሰጥ ይጎድልብኛል ብሎ እንዳያስብ ስጥ ስለሰጠህ አይጎድልብህም ይሰጥሃል ተባለ፡፡
ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል። ሉቃስ 6፡38
ስለዚህ ነው ከሚቀበል ይበልጥ የሚሰጥ የተባረከ ነው የሚለው፡፡
እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ፦ ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ። ሐዋርያት 20፡35
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ብልፅግና #የብልፅግናወንጌል #ስራ #ትጋት #በረከት #ስኬት #ስምረት #መሰረታዊፍላጎት #ጥበብ #ሁሉየእናንተነውና #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #የተትረፈረፈህይወት #መፅሃፍቅዱስ #መድከም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment