Popular Posts

Saturday, May 13, 2017

ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው

እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። ዘፍጥረት 1፡27
እግዚአብሄር ሰውን ሲፈጥር ወንድና ሴት እንዲሆኑ ነው በቤተሰብ ውስጥ የፈጠረው፡፡
እግዚአብሄር ሰውን በመልኩ ፈጠረው፡፡ በቤተሰብ ውስጥ የእግዚአብሄር መልክ የሚታየው በወንድና በሴት ነው፡፡ በቤተሰብ ውስጥ ወንድ ብቻ እግዚአብሄርን መልክ ሙሉ ለሙሉ አይገልጠውም፡፡ በቤተሰብ ውስጥ የሴት መልክ ብቻ እግዚአብሄርን ሙሉ ለሙሉ አያንፀባርቀውም፡፡  
የእግዚአብሄርን ሙሉ መልክ እንዲያንፀባርቁ እግዚአብሄር ሰውን በመልኩ ፈጠረው ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፡፡
በቤተሰብ ውስጥ የእግዚአብሄርን መልክ ሙሉ ለሙሉ ለማንፀባረቅ የሴት የርህራሄ ፣ የምህረት ፣ የፍቅርና የደግነት ባህሪ ያስፈልጋል፡፡
ዕድሜዋን ሙሉ መልካም ታደርግለታለች፥ ክፉም አታደርግም። ምሳሌ 31፡12
እግዚአብሄር የፈጠራችሁን መልክ ለመኖር ለሁሉም ሰው ርህሩህ ፣ አፍቃሪ ፣ መሀሪ ፣ ደግ ይቅር ባይ የሆናችሁ ሴቶች ሁሉ መልካም የእናቶች ቀን ይሁንላችሁ፡፡ 
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እግዚአብሔር #ሴት #ጌታ #መከተል #ፍቅር #ርህራሄ #ይቅርታ #እግዚአብሔርንመምሰል #ቃል #ደግነት #ቸርነት #ቃሉንመስማት #ደቀመዝሙር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት  #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment