Popular Posts

Friday, June 29, 2018

በሰው የሚታመን

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹንም ክንዱ የሚያደርግ ልቡም ከእግዚአብሔር የሚመለስ ሰው ርጉም ነው። በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ ይሆናል፥ መልካምም በመጣ ጊዜ አያይም፤ ሰውም በሌለበት፥ ጨው ባለበት ምድር በምድረ በዳ በደርቅ ስፍራ ይቀመጣል። ትንቢተ ኤርምያስ 17፡5-6
እግዚአብሄር የፈጠረን በእርሱ እንድንደገፍ ነው፡፡ በእርሱ ስንደገፍ እግዚአብሄር ደስ ያሰኘዋል፡፡
ነገር ግን በእግዚአብሄር መታመን ትተን በሰዎች መታመን ስንጀምር እግዚአብሄር ያዝናል፡፡ የተፈጠርነው በእግዚአብሄር እንድንደገፍ ስለሆነ በሰው ስንደገፍ አይሳካልንም፡፡
እንኳን ለሌላ ሰው መገደፊያ ሊሆን ይቅርና ሰው ራሱ በእግዚአብሄር ላይ መገደፍ አለበት፡፡ ሰው ለሌላ ለማንም ሰው መደፊያ ሊሆን አይችልም፡፡
ብዙ ሰዎች በእግዚአብሄር መታመን ይጀምራሉ፡፡ በእግዚአብሄር በመታመን እንድንጀምር ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሄር በመታመን እንድንጨርስ እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡
በአስቸጋሪ ጊዜ እምነቱን ከእግዚአብሄር ላይ የማያነሳ ሰው ምስጉን ነው፡፡ በክፉ ጊዜ እምነቱን ከእግዚአብሄር ላይ የሚያነሳ ሰው እርጉም ነው፡፡
በመከራ ቀን ብትላላ ጉልበትህ ጥቂት ነው። መጽሐፈ ምሳሌ 24፡10
አስቸጋሪ ጊዜ አልፎ ደግሞ መልካም ዘመን ሲመጣ እምነቱ ከእግዚአብሄር ላይ ያነሳውና በሰው ላየ ያደረገው ሰው ይፀፀታል፡፡ መልካም ጊዜ መጥቶ የማይለወጥ የሚመስለው ነገር ሲለወጥ እምነቱን ከእግዚአብሄር ላይ እንስቶ ወደሰው ላይ ያደረገው ሰው ለሚያልፍ ነገር ምነው በእግዚአብሄር በታመንኩኝ ኖሮ ብሎ ይቆጫል፡፡ በአስቸጋሪ ጊዜ እምነቱን እግዚአብሄርን በሰው የለወጠ ሰው የእምነትን ገድል ደስታ አያገኘውም፡፡ በአስቸጋሪ ጊዜ እምነቱን ከእግዚአብሄር ላይ እንስቶ በሰው ላይ ያደረገ ሰው ለማይረባ ነገር እግዚአብሄርን ስለለወጠው ያፍራል፡፡
በአስቸጋሪ ጊዜ ሁሉ ከእግዚአብሄር ጋር የሙጥኝ ያለ ሰው በእግዚአብሄር በመታመኑና በማለፉ ብቻ እምነቱ ይጨምራል፡፡ በአስቸጋሪ ጊዜ እግዚአብሄርና ያመነና የጠበቀ ሰው እምነቱ ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ጠርቶና ከብሮ ይወጣል፡፡ በአስቸጋሪ ጊዜ እምነቱን በሰው ያልለወጠው ሰው ደስታው ይበዛል፡፡
በዚህም እጅግ ደስ ይላችኋል፥ ነገር ግን በእሳት ምንም ቢፈተን ከሚጠፋው ወርቅ ይልቅ አብልጦ የሚከብር የተፈተነ እምነታችሁ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ፥ ለምስጋናና ለክብር ለውዳሴም ይገኝ ዘንድ አሁን ለጥቂት ጊዜ ቢያስፈልግ በልዩ ልዩ ፈተና አዝናችኋል። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1፡6-7
እምነቱን ሲፈተን የወደቀ ሰው መልካም በመጣ ጊዜ አያይም፡፡ በሰው መደገፍን ያልናቀ ሰው በእግዚአብሄር በመደገፍ ያለውን ደስታ አያይም፡፡ በሰው በመደገፍ ክፉን ጊዜ ያሳለፈ ሰው ላነሰ ጥቅም ራሱን ስለሰጠ እውነተኛውን የእግዚአብሄርን በረከት አያየውም፡
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹንም ክንዱ የሚያደርግ ልቡም ከእግዚአብሔር የሚመለስ ሰው ርጉም ነው። በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ ይሆናል፥ መልካምም በመጣ ጊዜ አያይም፤ ሰውም በሌለበት፥ ጨው ባለበት ምድር በምድረ በዳ በደርቅ ስፍራ ይቀመጣል። ትንቢተ ኤርምያስ 17፡5-6
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ስጋለባሽ #መታመን #መደገፍ #ልብ #የሚመልስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ክንዱ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መታመን #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment