Popular Posts

Friday, June 22, 2018

ከጫጉላው መልስ

ብዙዎቻችን በአዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር ፍትሃዊ አመለካከት ሁላችንም ተደስተናል፡፡ ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር አብሮ መቆም ወሳኝ ነው፡፡
መሪን የምንከተለው እግዚአብሄር ይመራዋል ብለን በእግዚአብሄር አምነን እንጂ እያንዳንዱ እርምጃውን ተከታተልን አጣርትን ተስማምቶን አይደለም፡፡ መሪን የምንከተለው እያንዳንዱን የሚወስነውን ውሳኔ ሁሉ ወደነው ላይሆን ይችላል፡፡ እያንዳንዱ የምንፈልገውን ነገር ሁሉ ካደረገ እኛ እንጂ እርሱ መሪ አይደለም፡፡ ጠቅላይ ሚንስትሩ ነገ ከነገ ወዲያ ይህንን ባያደርግ ጥሩ ነበረ የምንለውን ውሳኔ ሊወስን ይችላል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአንድና በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ ፈቃድህ ቢሆን ይህችህ ፅዋ ከእኔ ትለፍ የምንልበት አንዳንድ ውሳኔዎች ሊወስን ይችላል ብለን ካልጠበቅን እና ልባችንን ካላዘጋጀን ብስለት የጎደለው ህዝብ እንሆናለን፡፡  
ታዲያ የህዝብ ብስለት የሚለካው በምንስማማበት ውሳኔዎቹ እየተደስትንበት በማንስማማው ውሳኔዎቹ ድምፃችንን እያሰማን በአጠቃላይ ግን መሪን መከተል ነው፡፡ የእያንዳንዳችንን ሃሳብ ሳይሆን መሪን በመከተል ብቻ ነው አገር ወደ አንድነት የሚመጣው፡፡
መሪን የምንከተለው እኛ የምንፈልገውን እንዳንዱን ነገር ያደርጋል ብለን አይደለም፡፡ መሪን የምንከተለው ከእኛ ይበልጥ ትልቁን ምስል ያያል ብለን ነው፡፡ መሪን የምንከተለው የአገሪቱን መሪነትን በተመለከተ እግዚአብሄር ከእኛ ይበልጥ መሪውን ይመራል ብለን ነው፡፡
የንጉሥ ልብ እንደ ውኃ ፈሳሾች በእግዚአብሔር እጅ ነው፤ ወደ ወደደውም ያዘነብለዋል። መጽሐፈ ምሳሌ 21፡1
ጠቅላይ ሚንስትሩ ነገ ከነገ ወዲያ ቅር የሚለንን ነገር ሊወስን ይችላል፡፡ ለዚያ ምን ያህል ተዘጋጅተናል፡፡ ይሄ ሰው አይሆንም ብለን እርግፍ አድርገን ትተን ሌላ ሰው ለመፈለግ እንሄዳለን? ወይስ የምንስማማበትን ዋና ነገር እየተደሰትንበት የማንስማማውን ነገር በማለፍ የአገር ሃላፊነታችንን እየተወጣን ለአገር ብልፅግና በአንድነት እንሰራለን፡፡
ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ሥልጣኖች ይገዛ። ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለ ሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው። ስለዚህ ባለ ሥልጣንን የሚቃወም የእግዚአብሔርን ሥርዓት ይቃወማል፤ የሚቃወሙትም በራሳቸው ላይ ፍርድን ይቀበላሉ። ገዥዎች ለክፉ አድራጊዎች እንጂ መልካም ለሚያደርጉ የሚያስፈሩ አይደሉምና። ባለ ሥልጣንን እንዳትፈራ ትወዳለህን? መልካሙን አድርግ ከእርሱም ምስጋና ይሆንልሃል፤ ለመልካም ነገር ለአንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና። በከንቱ ግን ሰይፍ አይታጠቅምና ክፉ ብታደርግ ፍራ፤ ቍጣውን ለማሳየት ክፉ አድራጊውን የሚበቀል የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና። ስለዚህ ስለ ቍጣው ብቻ አይደለም ነገር ግን ስለ ሕሊና ደግሞ መገዛት ግድ ነው። ስለዚህ ደግሞ ትገብራላችሁና፤ በዚህ ነገር የሚተጉ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸውና። ለሁሉ የሚገባውን አስረክቡ፤ ግብር ለሚገባው ግብርን፥ ቀረጥ ለሚገባው ቀረጥን፥ መፈራት ለሚገባው መፈራትን፥ ክብር ለሚገባው ክብርን ስጡ። ወደ ሮሜ ሰዎች 13፡1-7
ሰው እንኳን በሰው መሪነት በእግዚአብሄር መሪነት እንኳን እንዲህ ቢያደርግልፅ ኖሮ የሚለው ነገር አለ፡፡ ሰው እንኳን በሰው መሪነት በእግዚአብሄር መሪነት ፈቃድህ ቢሆን ይህች ፅዋ ከእኔ ትለፍ የሚለው ነገር ይኖራል፡፡
ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር። የሉቃስ ወንጌል 22፡42
ባል ከሚስቴ ጋር የማልስማበት ነገር አለ ቢል አያስገርምም፡፡ ሁለት ሰዎች የማይስማሙበት ነገር ቢኖር ይደንቃል? እንዲያውም ታእምር የሚሆነው የማይሳማሙበት ነገር ባይኖር ነው፡፡ ባል የሚስቴን ሁሉንም ነገር እወደዋለሁ እንድትለውጥ የምፈልገው ነገር የለም ቢል ይዋሻል፡፡ ሚስት ባልዋን የምትወድበት ዋና ምክኒያት አለ ሌላውን ግን ትታገሰዋለች፡፡ ሚስት ባልዋን በፍቅር የምትከተለው እግዚአብሄር ይመራዋል ብላ እግዚአብሄርን ታምና እንጂ እኔ የምፈልገውን ነገር ሁሉ ያደርጋል ብላ አይደለም፡፡
ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ። ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5፡21-22
ፓስተሩ የሚናገረው ነገር ሁሉ ይስማማኛል እኔ የማስበውን ነገር ሁሉ ነው የሚያስበው የሚል ሰው ካለ ከገሃዱ አለም የራቀ ሰው ነው፡፡ ፓስተሩ ባለው ዋና አቋም ከተስማማ ሌላውን ነገር ወደጎን በመተው ለቤተክርስትያን እንድነት ይሰራል፡፡
በክርስቶስም አንዳች ምክር ቢሆን፥ የፍቅር መጽናናት ቢሆን፥ የመንፈስ ኅብረት ቢሆን፥ ምሕረትና ርኅራኄ ቢሆኑ፥ ደስታዬን ፈጽሙልኝ፤ በአንድ አሳብ ተስማሙ፥ አንድ ፍቅር አንድም ልብ አንድም አሳብ ይሁንላችሁ፤ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2፡1-2
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ፍትህ #ፍርድ #አናሳ #አብላጫ #ዲሞክራሲ #ባል #አምባገነን #ሚስት #ድሃ #ኢትዮጲያ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ወንጌል #ዛሬ #ነገ #ትላንት #መሪ

No comments:

Post a Comment