Popular Posts

Thursday, June 28, 2018

በእምነትም ያልሆነ ሁሉ

የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 14፡23
ሰው የተፈጠረው ለእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡ እግዚአብሄርን የምናከብረው ቃሉን በመጠበቅና በቃሉ በመኖር ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሄርን የምናከብረውና የምናስደስተው በቃሉ በመኖር ፍሬ በማፍራት ብቻ ነው፡፡
በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል። ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራል። የዮሐንስ ወንጌል 15፡7-8
ካለ እምነት እግዚአብሄርን ደስ ማሰኘት አይቻልም፡፡
ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ወደ ዕብራውያን 11፡6
እግዚአብሄርን የምናስደስተው ከቃሉ በሆነ እምነት ኑሮ ብቻ ነው፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡17
ሰው የተፈጠረው ከቃሉ በሚገኝ እምነት እንዲኖር ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በእምነት ከእግዚአብሄር ጋር እንዲራመድ ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በእምነት በሚወስደው እርምጃ እግዚአብሄርን እንዲያስደስት ነው፡፡ ሰው በእምነት ሲኖር የተፈጠረበትን አላማ ግቡን ይመታል፡፡ ሰው ከእምነት ውጭ ሲኖር የተፈጠረበትን አላማ ይስተዋል፡፡ ከቃሉ በሚመጣ እምነት እንጂ በጥርጥር እግዚአብሄር አይከብርም፡፡ ጥርጥር የተፈጠሩበትን አላማን መሳት ነው፡፡ ጥርጥር አላማን መሳት ወይም ሃጢያት ነው፡፡
ስለዚህ ነው እምነት የሚገኝበትን የእግዚአብሄር ቃል ላይ የሙጥኝ ማለት ያለብንና በእምነት እርምጃን መውሰድ ያለብን፡፡
የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 14፡23
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ልብ #ማመን #ቃል #መናገር #ያለእምነት #ስሜት #ሁኔታ #አካባቢ #አላማ #መሳት #ሃጢያት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አለማመን #ጥርጥር #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment