Popular Posts

Monday, June 11, 2018

የክርስቶስም ሙላቱ ልክ እስክንደርስ

ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት፥ ሙሉ ሰውም ወደ መሆን፥ የክርስቶስም ሙላቱ ወደሚሆን ወደ ሙላቱ ልክ እስክንደርስ ድረስ፥ ቅዱሳን አገልግሎትን ለመሥራትና ለክርስቶስ አካል ሕንጻ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ። ኤፌሶን 4፡12-13
የክርስትና ጉዞ የእድገት ጉዞ ነው፡፡ የክርስትና ጉዞ መነሻ ያለው መድረሻም ያለው ጉዞ ነው፡፡
የክርስትና ጉዞ ሲጀመር የሚታወቅ ግቡም የሚታወቅ ጉዞ ነው፡፡ ክርስትና መነሻውም መድረሻውም የማይታወቅ የግምት ረቂቅ ጉዞ አይደለም፡፡ ክርስትና መነሻውም መድረሻውም የሚገመት ባዶ ሃይማኖት አይደለም፡፡ ክርስትና መነሻውም መድረሻውም የማይታወቅ የወግና የስርአት ብዛት አይደለም፡፡
ክርስትና የሚጀመረው በንስሃ ከአሮጌ ኑሮ ፍጹም ወደኋላ በመመለስ ነው፡፡ ክርስትና የሚጀመረው ዳግም ከመወለድ ነው፡፡ ዳግም የተወለደ ሰው ደግሞ ያድጋል፡፡
የክርስትና እድገት ወግና ስርአት መፈፀም አይደለም፡፡ የክርስትና እድገት የውጫዊ ስርአትን መጠበቅ አይደለም፡፡
ትሕትናንና የመላእክትን አምልኮ እየወደደ፥ ባላየውም ያለ ፈቃድ እየገባ፥ በሥጋዊም አእምሮ በከንቱ እየታበየ ማንም አይፍረድባችሁ። እንደዚህ ያለ ሰው ራስ ወደሚሆነው አይጠጋም፥ ከእርሱም አካል ሁሉ በጅማትና በማሰሪያ ምግብን እየተቀበለ እየተጋጠመም፥ እግዚአብሔር በሚሰጠው ማደግ ያድጋል። ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2፡18-19
የክርስትና እድገት ጣራው የክርስቶስ ሙላት ልክ ነው፡፡ የክርስትና መጨረሻው ክርስቶስን መምሰል ነው፡፡ የክርስትና መጨረሻው የክርስቶስ ሙላት ልክ ነው፡፡ የክርስትና ግቡ ክርስቶስን ሙሉ ለሙሉ መከተልና መምሰል ነው፡፡
ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት፥ ሙሉ ሰውም ወደ መሆን፥ የክርስቶስም ሙላቱ ወደሚሆን ወደ ሙላቱ ልክ እስክንደርስ ድረስ፥ ቅዱሳን አገልግሎትን ለመሥራትና ለክርስቶስ አካል ሕንጻ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4፡12-13
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እግዚአብሔር #ጌታ #መከተል #ክርስቶስእስኪሳል #መምሰል #ክርስቶስንመምሰል #ቃል #ተማሪ #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #ደቀመዝሙር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ነፍስንመካድ #መፅሃፍቅዱስ #ተከታይ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment