Popular Posts

Tuesday, March 27, 2018

ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች

ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ። ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ዮሃንስ 14፡15-18
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ደቀመዛሙርቱን ያስተምራቸውና ይመራቸው ነበር፡፡ ጥያቄ ሲኖርባቸው ጥያቄያውን በትክክል ይመልስላቸው ነበር፡፡ ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን እንደአባት ወደ እውነት ሁሉ ይመራቸው ነበር፡፡
ኢየሱስ የምድር አገልግሎቱን ጨርሶ በሚወሰድበት ጊዜ ግን ደቀመዛሙርቱ የኢየሱስን የአባትነት መሪነት ያጡታል፡፡ ኢየሱስ ወደሰማይ ሲወሰድ በግል እያንዳንዳቸውን አግኝቶ ሊመክራቸ ወደ እውነት ሁሉ ሊመራቸው አይችልም ነበር፡፡ ስለዚህ ነው ኢየሱስ ከምድር ከመሄዱ በፊት አባት እንደሌላቸው ልጆች ካለ ምሪትና ካለ ማፅናናት እንደማይተዋቸው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ተመልሶ እንደሚመጣ ለደቀመዛሙርቱ የሚነግራቸው፡፡
አሁን መንፈስ ቅዱስ በምድር ላይ አለ፡፡ አሁን መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን በሚከተሉ ሰዎች ውስጥ ያድራል፡፡ አሁን መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ያደርገው የነበረውን ማፅናትና ምሪት ሁሉ ይሰጣል፡፡
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ሊያፅናና ፣ ሊመክር ፣ ሊያስተምርና ወደ እውነት ሁሉ ሊመራ የሚችለው ጥቂት ሰዎችን ብቻ ነበር፡፡ ኢየሱስ በምደር ሲኖር በስጋ የተወሰነ ስለነበር የምድር ህዝብን ሁሉ በግል ሊያፅናናና ሊመራ አይችልም ነበር፡፡  
አሁን መንፈስ ቅዱስ ግን በስጋ ስለማይኖርና በስጋ ስለማይወሰን ኢየሱስን የተቀበሉት ሰዎች ሁሉ ውስጥ ይኖራል፡፡ ኢየሱስን በሚከተሉት ሰዎች ሁሉ ውስጥ በመኖር ወደ እውነት ሁሉ ይመራቸዋል፡፡
እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ። ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ዮሃንስ 14፡15-18
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #መንፈስቅዱስ #አፅናኝ #እውነት #በውስጣችሁ #መንፈስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ቅባት #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መውደድ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment