Popular Posts

Monday, July 2, 2018

ብታምኚስ

ኢየሱስ፦ ድንጋዩን አንሡ አለ። የሞተውም እኅት ማርታ፦ ጌታ ሆይ፥ ከሞተ አራት ቀን ሆኖታልና አሁን ይሸታል አለችው። ኢየሱስ፦ ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርሁሽምን? አላት። የዮሐንስ ወንጌል 11፡39-40
የእግዚአብሄርን ክብር ማየት የማይፈልግ ሰው የለም፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት መመዘኛ አለው፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር በህይወታችን ለመለማመድ መመዘኛው ደግሞ ሊደረስበት የማይችል ረቂቅ ነገር አይደለም፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት የሚጠይቀው እምነት ብቻ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት እምነት ወሳኝ ነው፡፡ እግዚአብሄርን ለማስደሰትና የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት ሌላ መንገድ የለውም፡፡
ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ወደ ዕብራውያን 11፡6
የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት ሌላ መንገድ ቢኖር ኖሮ ያንን መንገድ እንከተል ነበር፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት ሌላ መንገድ የለውም፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር ለማየት ብቸኛው መንገድ እምነት ብቻ ነው፡፡ ኢየሱስ ለማርታ አልነገርሁሽምን? የሚላት በፊትም የእግዚአብሄርን ክብር የምታይው ስታምኚ እንደሆነ ነግሬሻለሁ ዛሬም አልተለወጠም የእግዚአብሄን ክብር ማየት ከፈለግሽ ማመን ወሳኝ ነው እያላት ነው፡፡
የእግዚአብሄን ክብር እንድናይ የሚያስችለን እምነት ደግሞ የሚመጣው የእግዚአብሄርን ቃል ከመስማት ነው፡፡
እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 10፡17
የእግዚአብሄር ክብር ከሰዎች የራቀ እጅግ ረቂቅ ነገር አይደለም፡፡ እግዚአብሄር ቸር አምላክ ነው፡፡ ምድር በእግዚአብሄር ከብር ተሞልታለች፡፡
ነገር ግን እኔ ሕያው ነኝና በእውነት የእግዚአብሔር ክብር ምድርን ሁሉ ይሞላል።  ኦሪት ዘኍልቍ 14፡21
የእግዚአብሄር ክብር የሚያይ ሰው በእግዚአብሄር ቃል መስማት እምነትን ያገኘ ሰው ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር በህይወቱ የሚለማመድ ሰው በእግዚአብሄር ቃል እምነትን ያገኘ ሰው ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ክብርና ሃይል በህይወቱ የሚለማድ ሰው የእግዚአብሄርን ቃል የሚያምን ሰው ነው፡፡
እግዚአብሔር ልቡ በእርሱ ዘንድ ፍጹም የሆነውን ያጸና ዘንድ ዓይኖቹ በምድር ሁሉ ይመለከታሉና። መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 16፡9
የእግዚአብሄርን ቃል የሰማ ሰው የእግዚአብሄርን ክብርና በጎነት በህይወቱ ይለማመዳል፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር ማየት ይቻላል፡፡ የሞተ ሲነሳ ማየት ይቻላል፡፡ የደከመ ሲበረታ ማየት ይቻላል፡፡ የሌለን ወደመኖር ሲመጣ ማየት ይቻላል፡፡
ስለዚህ ከሕግ ብቻ ሳይሆን ከአብርሃም እምነት ደግሞ ለሆነ ለዘሩ ሁሉ የተስፋው ቃል እንዲጸና እንደ ጸጋ ይሆን ዘንድ በእምነት ነው፤ እርሱም፦ ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት የሁላችን አባት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 4፡16-17
በእምነት የእግዚአብሄርን ክብር ማየት ይቻላል፡፡ ለሚያምን ሁሉ ይቻለዋል፡፡ ለማያምን የእግዚአብሄርን ክብር ሃይልና በጎነት ማየት ይቻለዋል፡፡
ኢየሱስ፦ ድንጋዩን አንሡ አለ። የሞተውም እኅት ማርታ፦ ጌታ ሆይ፥ ከሞተ አራት ቀን ሆኖታልና አሁን ይሸታል አለችው። ኢየሱስ፦ ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርሁሽምን? አላት። የዮሐንስ ወንጌል 1139-40
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #እግዚአብሔር #ክብር #መልክ #አምሳል #ሃይል #ብፅእና #በረከት #ቃል #ፀሎት #አምልኮ #በጎነት #መጠማት #መራብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment