Popular Posts

Thursday, July 12, 2018

አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም

አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤ በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል። ወደ ገላትያ ሰዎች 6፡7-8
ሰው ሰው ላይ ቀልዶ ምን አልባት ሊያመልጥ ይችል ይሆናል፡፡ ሰው እግዚአብሄር ላይ ቀልዶ ሊያመለጥ ግን አይችልም፡፡
ሰው መጠንቀቅ ያለበት በሰላም ጊዜ ነው፡፡ ሰው መጠንቀቅ ያለበት በእለት ተእለት ኑሮው ነው፡፡ የሰውን ህይወት የሚሰራውም የሚያፈርሰውም የእለት ተእለት ውሳኔና እርምጃ ነው፡፡
ሰው መጠንቀቅ ያለበት በዘር ጊዜ ነው፡፡ ሰው ዘሩን የሚመርጠውና የሚያስተካክለው በዘር ጊዜ እንጂ በአጨዳ ጊዜ አይደለም፡፡ ሰው ይፍጠንም ይዘግይም የሚያጭደው የዘራውን ያንኑ ነው፡፡ አጨዳው ስለዘገየ ዘሩን አይለውጠውም፡፡ ሰው የሚያጭደው የዘራውን ያንኑ ነው፡፡  
ሰው መጠንቀቅ መዘገየት ያለበት ከመዝራቱ በፊት ነው፡፡ ሰው ከዘራ በኋላ ስለዘሩ ምንም ማደርግ ስለማይችል ሰው ከመዝራቱ በፊት ቢጠነቅቅ መልካም ነው፡፡ ሰው ከመዝራቱ በፊት ካለተጠነቀቀ ከዘራ በኋላ የዘሩን ውጤት መጠበቅ እንጂ ምንም ማድረግ አይችልም፡፡ ሰው ከዘራ በኋላ ዘሩን ሊለውጥ አይችልም፡፡
መጽሃፍ ቅዱስ ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው ይላል፡፡
እንግዲህ ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው፤ ሕግም ነቢያትም ይህ ነውና። የማቴዎስ ወንጌል 7፡12
በሌላ አነጋገር ሰዎች ሊያደርጉባችሁ የማትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አታድርጉባቸው ማለቱ ነው፡፡ ሰዎች እንዲያደርጉብን የማንፈልግውን ነገር ሰው ላይ ማድረግ የለብንም፡፡ ሰዎች ሊያደርጉባችሁ የማትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ ማድረግ በንግግር ሳይሆን በድርጊት እኔ እንዲህ እንዲደረግብኝ እፈልጋለሁ ማለት ነው፡፡
አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤ ወደ ገላትያ ሰዎች 6፡7
በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል። ወደ ገላትያ ሰዎች 6፡8
ከሃሳብ ጀምሮ ስለስጋ ማሰብ ሞት ነው፡፡
ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 8፡8
ሰው በስጋው ዘርቶ በመንፈስ አያጭድም፡፡ ሰው በስጋው የዘራውን መበስበስን ያጭዳል፡፡ ሰው በስጋው የዘራውን በሞት በመለየት በጥፋት ያጭዳል፡፡
ሰው በስጋው የስጋን ስራ ዘርቶ በመንፈስ ህይወትንና ሰላምን ሊያጭድ አይችልም፡፡ የስጋ ስራም አነዚህ ናቸው፡፡
የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵሰት፥ መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥ መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። ወደ ገላትያ ሰዎች 5፡19-21
አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤ በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል። ወደ ገላትያ ሰዎች 6፡7-8

#ክብር #ራእይ #ስጋ #ሃሳብ #የዘራወን #ያጭዳል #አትሳቱ #አይዘበትበትም #መበስበስ #ሰላም #ህይወት #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ብርሃን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መንገድ #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment