Popular Posts

Monday, July 2, 2018

ድሆች ስንሆን

በክፉ ወሬና በመልካም ወሬ ራሳችንን እናማጥናለን፤ አሳቾች ስንባል እውነተኞች ነን፤ ያልታወቁ ስንባል የታወቅን ነን፤ የምንሞት ስንመስል እነሆ ሕያዋን ነን፤ የተቀጣን ስንሆን አንገደልም፤ ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6፡7-9
ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ለጻድቃን አይደለም፡፡ ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ለበሽተኞች ነው፡፡ ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ለሃያላን አይደለም ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ለደካሞችነው፡፡ ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ምንም አያስፈልገንም ለሚሉ አይደለም፡፡ ኢየሱስ ወደምድር የመጣው ለድሆች ነው፡፡
የነቢዩንም የኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጡት፥ መጽሐፉንም በተረተረ ጊዜ፦ የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ለታሰሩትም መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፥ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል ተብሎ የተጻፈበትን ስፍራ አገኘ። የሉቃስ ወንጌል 4፡17-19
የአገልጋይ ክብሩ ደሃን ባለጠጋ ማድረግ ነው፡፡ እውነተኛ አገልጋይ የሚፈልገው ደሃን ነው፡፡ እውነመተኛ አገልጋይ ድሃን ባለጠጋ ያደርጋል፡፡
ዳዊትን የተከተሉት ሰዎች እጅግ የተጣሉ የተጨነቁና የተከፉትን ሰዎች ነበር፡፡
የተጨነቀውም ሁሉ፥ ብድርም ያለበት ሁሉ፥ የተከፋም ሁሉ ወደ እርሱ ተከማቸ፤ እርሱም በላያቸው አለቃ ሆነ፤ ከእርሱም ጋር አራት መቶ የሚያህሉ ሰዎች ነበሩ። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 22፡2
ዳዊትን የተከተለውን የተጨነቀውም ሁሉ፥ ብድርም ያለበት ሁሉ፥ የተከፋም ሁሉ የምድሪቱ ሃያላን አደረገው፡፡
ሦስቱም ኃያላን የፍልስጥኤማውያንን ሠራዊት ቀድደው ሄዱ፥ በበሩም አጠገብ ካለችው ከቤተ ልሔም ምንጭ ውኃ ቀዱ፥ ይዘውም ለዳዊት አመጡለት፤ እርሱ ግን ሊጠጣ አልወደደም፥ ነገር ግን ለእግዚአብሔር አፍስሶ፦ መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ 23፡16
የአገልጋይ ክብር ምንም ያልሆነውንና ምንም የሌለውን ሰው አጥቦና አሸላልሞ ባለጠጋ ማድረግ ነው፡፡
ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6፡9
የአገልጋይ ክብር ድሆችን በነገር ሁሉ ባለጠጋ ማድረግ ነው፡፡
ለክርስቶስ መመስከሬ በእናንተ ዘንድ እንደ ጸና፥ በነገር ሁሉ በቃልም ሁሉ በእውቀትም ሁሉ በእርሱ ባለ ጠጎች እንድትሆኑ ተደርጋችኋልና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፡5-6
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ abiy Wakuma dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ያልታወቁ #የታወቅን #የምንሞት #ሕያዋን #የተቀጣን #አንገደልም  #ኀዘንተኞች #ደስ #ድሆች #ባለጠጎች #የሌለን  #ሁሉየእኛነው #ጭንቀት #የባለጠግነትማታለል #የኑሮሃሳብ #የእለትእንጀራ #የባለግነትምቾት #ዘር #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment