Popular Posts

Thursday, July 12, 2018

የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው

በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል። ወደ ገላትያ ሰዎች 6፡8
የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵሰት፥ መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥ መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላትያ 5፡19-21
ስጋ እንደ መንፈስ ፍሬ የለውም፡፡ ስጋ ያለው ካለ ፍሬ የሆነ ስራ ነው፡፡ የስጋ ስራ ደግሞ ረቂቅ ማንም ሊያውቀው የማይችል አይደለም፡፡ የስጋ ስራ የተገለጠ ነው፡፡ የስጋን ስራ በህይወታችንም ይሁን በሰዎች ህይወት አይተን እናውቀዋለን፡፡ 
ዝሙት
ሚስት ወይም ባል ካልሆነ ሰው ጋር ያለ ልቅ የሆነ ግንኙነት
ርኵሰት፥
በአለም ስርአት አስተሳሰብ አመለካከት መርከስ
መዳራት፥
ፈር የለቀቀ ግንኙነት፡፡ ለስጋ ደስታ ልክ አለማበጀት፡፡ ልቅነት፡፡
ጣዖትን ማምለክ፥
ከእግዚአብሄር ውጭ መፍትሄን መፈለግ፡፡
ምዋርት፥
ሌላው ሰው ላይ ክፉ እንዲደርስበት መፈለግ መስራት ክፋት ለማድረግ እንግዳን ሃይል መፈለግ መጠቀም፡፡
ጥል፥
መብትን በራስ ጉልበት ለማስከበር ሲባል ሰው ላይ የስሜት ወይም የአካል ጉዳት ጉዳት ማድረስ
ክርክር፥
በንግግር ብዛት በሰው ላይ ተፅኖ ማድረግ ፣ ሌላውን ሰው አላግባብ ለመቆጣጠር መሞከር ፣ በእግዚአብሄር አለመታመን በቃል ብዛትና በንግግር ችሎታ ሌላውን ለመቆጣር መሞከር፡፡   
ቅንዓት፥
በሌላው ከፍታ ማግኘትና መከናወን ደስ አለመደሰት፡፡ በሌላው ስኬት መበሳጨት፡፡ የሌላው ከፍታ በሌላው ውድቀት ምክኒያት እንደመጣ መቁጠር፡፡
ቁጣ፥
በከፍታ ድምፅ ፣ በከፍተኛ ስሜት የራስን ፍላጎት ብቻ ለማስፈፀም መሞከር፡፡ ንግግርን ሃሳብ ከማስተላለፍ ያለፈ ፈር ለለቀቀ ሌላውን ለመቆጣጠር ክፉ አላማ መጠቀም፡፡
አድመኛነት፥
ሌሎችን ለራስ የግል አላማ በክፋት ማነሳሳት ማንቀሳቀስ፡፡ ለግል አላማ ሌላውን ማሰባሰብ በሌላው ላይ በክፋት ማስነሳት አብሮ መጣላት፡፡  የሌላውን ተሰሚነት እና ችሎታ ተጠቅሞ የግልን ድብቅ አላማ ማስፈፀም፡፡ የግል ድብቅ አላማን ለማስከበር ቡድን ፈጥሮ ሌላውን ማጥቃት፡፡ 
ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ስራ ሁሉ አሉና። የያዕቆብ መልእክት 3፡16
መለያየት፥
በሰዎች መካከል ክፍፍልን መፍጠር፡፡ ጥላቻን መቀስቀስ አንዱን ሰው ከሌላው ሰው ማለያየት አንድነት እንዳይኖረው ማድረግ፡፡
መናፍቅነት፥
ለእምነት ራስን ሙሉ ለሙሉ አለመስጠት መሰሰት ራስን መለየት አንድነት አለማድረግ ራስን ከሌላው ጋር አለማስተባበር
ምቀኝነት፥
በሌላ ሰው ማግኘት መከናወን ደስተኛ አለመሆን መበሳጨት ሌላው እንዳያድግ እንዳይለወጥ እንቅፋት ማድረግ፡፡
መግደል፥
ጥላቻ እንደእርሱ ያለ እግዚአብሄር የፈጠረውን ሰው እንዳይኖር መፍረድ ትእቢት ማን አለብኝነት፡፡
ስካር፥
እግዚአብሄር ለስው የሚናገርበትን የእግዚአብሄርን ድምፅ የሚሰሙበትን ህሊናን ማደንዘዝ፡፡ እግዚአብሄርን ለመስማት አለመፈለግ፡፡ ከመጠን በላይ መዝናናት
ዘፋኝነት፥   
ስጋን ያለልክ መልቀቅ፡፡ መዝናናትን ተድላን ከእግዚአብሄር ባለይ መውደድ ምንም ምንም ብሎ ነፍስን ማስደሰት፡፡
ሕዝብም ሊበሉ ሊጠጡም ተቀመጡ ሊዘፍኑም ተነሡ ተብሎ እንደ ተጻፈ ከእነርሱ አንዳንዶቹ እንዳደረጉት ጣዖትን የምታመልኩ አትሁኑ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10፡7
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ክብር #ራእይ #ስጋ #ሃሳብ #የዘራውን #ያጭዳል #ዝሙት #ርኵሰት #መዳራት #ጣዖትንማምለክ #ምዋርት #ጥል #ክርክር #ቅንዓት #ቁጣ #አድመኛነት #መለያየት #መናፍቅነት #ምቀኝነት #መግደል #ስካር #ዘፋኝነት #አትሳቱ #አይዘበትበትም #መበስበስ #ሰላም #ህይወት #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ብርሃን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መንገድ #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment