Popular Posts

Saturday, July 7, 2018

ለሚያምን ሁሉ ይቻላል

እግዚአብሄር ሰውን በመልኩና በአምሳሉ ነው የፈጠረው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን ሲፈጥር አልሰሰተም ቁርጥ እርሱን አስመስሎ ነው የፈጠረው፡፡ እንደ አንዳንድ ሰዎች ከሆነ ሰውን በመልኩና በአምሳሉ መፍጠሩ ትክክል አልሰራም፡፡ በግልፅ ባይሆንም ሰው በመልኩና በአምሳሉ መፈጠሩን ባገኙት አጋጣሚ ይቃወማሉ፡፡ እነርሱ ቢሆኑ እንደማያደርጉት እርግጥ ነው፡፡
እንዲሁም ለሚያምን ሁሉ ይቻላል የሚለው አባባል የሚያስደነግጣቸው ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ነግር ግን ምንም ማድርግ አይቻልም፡፡
ሰው ለእግዚአብሄር ሁሉ ይቻላል ሲባል ይሻለዋል፡፡ ለሚያምን ሁሉ ይቻለዋል ሲባል ያስፈራዋል፡፡
ነግር ግን እውነቱ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል የሚያስብና የሚያስላስል ሰው እንደ እግዚአብሄር ያስባል ይባላል፡፡ እውነት ነው
እምነት የሚመጣው የእግዚአብሄርን ቃል ከመስማት ነው፡፡
ስለአለበት ሁኔታ የእግዚአብሄርን ቃል የሚሰማ ሰው ሁሉ እምነት ከእግዚአብሄር ቃል ይመጣለታል፡፡
ለሚያምን ሰው ቃሉ ይቻላል የሚለው ነገር ሁሉ ይቻለዋል፡፡
ለእግዚአብሄ የሚሳነው ነገር እንደሌለ ሁሉ ለሚያምን ሰው የሚሳነው ነገር አይኖርም፡፡
ለሚያም ሁሉ ይቻለዋል፡፡  
ኢየሱስም፦ ቢቻልህ ትላለህ፤ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል አለው። የማርቆስ ወንጌል 9፡23
ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ እምነት ቢኖራችሁ ባትጠራጠሩም፥ በበለሲቱ እንደ ሆነባት ብቻ አታደርጉም፤ ነገር ግን ይህን ተራራ እንኳ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ብትሉት ይሆናል፤ የማቴዎስ ወንጌል 21፡21
ለሚያምን ሁሉ ይቻላል !
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #መናገር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ቃል #ማሰላሰል #ማድረግ #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment