Popular Posts

Saturday, July 21, 2018

ከዛሬ ተግዳሮት ባሻገር

ይብዛም ይነስም ችግሮች ወደህይወታችን በየጊዜው ይመጣሉ፡፡ ችግሮቹ ሲከሰቱ ችግሮችን መፍታት ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ችግሮች ሲከሰቱ ችግሮችን ካልፈታናቸው ችግሮቹ የእግዚአብሄርን አላማ ከማድረግ ሊያደናቅፉን ይችላሉ፡፡
ችግሮች ሲመጡ መፍታት መልካም ሆኖ ሆኖ ሳለ ችግሮችን ከመፍታት የተሻለ መንገድ ደግሞ አለ፡፡
በህይወታችን አላማ ያስፈልገናል፡፡ እግዚአብሄር በምድር ላይ እንድንሰራ ያዘጋጀውን ስራ በትክክል ማወቅ አለብን፡፡ እግዚአብሄ በህይወታችን ያስቀመጠውን አላማ በትጋት መከተል አለብን፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ያስቀመጠው አላማ ላይ በትጋት መስራት ይጠበቅብናል፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን ያስቀመጠውን አላማ ለመፈፀም ስንንቀሳቀስ ከጉዞዋችን ሊያግደን የሚመጣ ችግርን እና ፈተናን ማለፍ ሃላፊታችን ነው፡፡
በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤ በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1፡9-10
ካልሆነ ግን ችግሮች ይመጣሉ እንፈታዋለን፡፡ የህይወት አላማ ከሌለን ለተወሰነ ጊዜ ደግሞ ተዝናንተን እንኖርና ደግሞ ሌሎች ችግሮች ይመጣሉ፡፡ በዚህ ሁኔታ ችግሮችን እየፈታን ችግሮቹ የሚጠብቁብንን ነገሮች እያደረግን ህይወታችንን እንገፋለን እንጂ እግዚአብሄር በህይወታችን ባለው አላማ እንደሚገባን ወደፊት መሄድ አንችልም፡፡ በየጊዜው የሚመጡትን ችግሮች በመፍታታችን ብቻ ከረካን እግዚአብሄር በህይወታችን ያቀደውን አላማ ከግብ ለማድረስ ይሳነናል፡፡
በየጊዜው መልካቸውን እየለዋወጡ የሚመጡትን ችግሮችን ብቻ እየፈታን የምንኖር ከሆንን ትልቁን የእግዚአብሄርን አላማ ምስል ማየት ያቅተናል፡፡ በየጊዜው የሚመጡትን ችግሮች ብቻ በመፍታት ላይ ከተሰማራን ዋናውን የእግዚአብሄርን አላማ ማየት ይሳነናል፡፡ በየጊዜው የሚመጡትን ችግሮች እየፈታን ከኖርን ሰይጣን የተለያየ የቤት ስራ እየሰጠን ባተሌ ያደርገናል፡፡ በየጊዜው የሚመጡት ችግሮች ላይ ብቻ ካተኮርን ስለነገ ማሰብ ያቅተናል፡፡ በየጊዜው የሚመጡት ችግሮች ላይ ባቻ ካተኮርን እግዚአብሄር በህይወታችን ስላለው ዋናው አላማ ማሰብና ማቀድ ያቅተናል፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ትንቢተ ኤርምያስ 29፡11
በህይወታችን የእግዚአብሄር አላማ ያስፈልገናል፡፡ በህይወታችን ያለውን የእግዚአብሄርን አላማ በትጋት መከተል ይገባናል፡፡ የእግዚአብሄርን አላማ ለመከተል ስንሄድ የሚቋቋመን ነገር ብቻ ነው ችግር ሊሆንብን የሚገባው፡፡ የእግዚአብሄርን አላማ ከመከተል የሚቋቋመን ችግር መፍታት የአላማችን መፈፀም አካል ሰለሆነ እግዚአብሄር በዚህ ይከብራል፡፡
ራእይ ባይኖር ሕዝብ መረን ይሆናል፤ ሕግን የሚጠብቅ ግን የተመሰገነ ነው። መጽሐፈ ምሳሌ 29፡18
የሰይጣን አላማ ህይወታችንን በጥቃቅን ነገር ባተሌ ማድረግና ከአግዚአብሄር አላማ ማደናቀፍ ነው፡፡ በህይወታችን የእግዚአብሄር አላማ በትክክል መረዳት ከሌለንና እግዚአብሄር ለምን የተለየ አላማ እንደፈጠረን ካልተረዳን ሰይጣን የቤት ስራ እየሰጠን ህይወታችንን ከንቱ ያደርጋል፡፡ ወደዚህ ምድር ለምን የተለየ አላማ እንደመጣን ካልተረዳን ችግሮችን በመፍታታችን ብቻ ደስ እያለን ዋናውን የእግዚአብሄርን አላማ ሳናከናውን ጊዜያችን ያልፋል፡፡
ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። የዮሐንስ ወንጌል 10፡10
ስለዚሀ በተነሳሽነት መንፈስ የእግዚአብሄርን ልዩ አላማ መፈለግ አለብን፡፡ በተነሳኽሽነት መንፈስ ያንን አላማ ለመፈፀም እቀድ ማውጣት አለብን፡፡ በተነሳሽነት መንፈስ ያንን አላማ ለማስፈፀም የህይወት እቅዳችንን በትጋት መከተል አለብን፡፡
የእግዚአብሄርን አላማ በትጋት ስንከተል ችግሮች የሚሆኑት አታልፍም ብለው በፊታችን የሚቆሙ ከአለማችን ሊያደናቅፉ የሚመጡ እንቅፋቶች ብቻ ይሆናሉ፡፡ የእግዚአብሄርን አላማ በመፈፀም ላይ ከተጋን ሰይጣን ሊመራንና በየጊዜው በሚሰጠን የቤት ስራ ላይ ባተሌ ሆነን ዋናውን የህይወታችን አላማ አንዘነጋም፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #እይታ #አላማ #ተስፋ #ፍፃሜ #ችግር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ተሰፋ #ፍፃሜ #የእግዚአብሄርሃሳብ #የእግዚአብሄርእቅድ #የእግዚአብሄርፈቃድ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment