Popular Posts

Saturday, July 28, 2018

ትእቢት ለምን

የእግዚአብሄር ቃል ስለ ትእቢት አስከፊነት ብዙ አስፈሪ ነገሮችን ይናገራል፡፡ እግዚአብሄር ትዕቢተኞችንም ከሩቅ እንደሚያውቅ መፅሃፍ ቅዱስ ይናገራል፡፡
እግዚአብሔር ከፍ ያለ ነውና፥ ወደ ችግረኞችም ይመለከታልና፤ ትዕቢተኞችንም ከሩቅ ያውቃል። መዝሙረ ዳዊት 138፡6
እግዚአብሄር ስለትእቢት ውጤት የተረጋገጠና እርሱም ውድቀት እንደሆነ ያስተምራል፡፡
እገዚአብሄር ብዙ አላዋቂ ሰዎችን ያስተምራል ይለውጣል፡፡ እግዚአብሄር የተለያየ ችግር ላለባቸው ሰዎች እነርሱን የሚያነሳበት መፍትሄ አለው፡፡ እግዚአብሄ ግን ለትእቢተኛ ማድርግ የሚችለው አንድ ነገር መቃወም ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር ግን ለምንድነው ግን እግዚአብሄር ትእቢኛን እንደዚህ የሚቃወመው ብለን መጠየቅ ብልህነት ነው፡፡
1.      ትእቢተኝነት ሰይጣንን መከተል ነው
ሰይጣን ከእግዚአብሄር ዘንድ የተጣለው በትእቢቱ ነው፡፡ ትእቢተኝነት ሰይጣንን ማድነቅ ነው፡፡ ትእቢት ሰይጣንን እንደ ምሳሌ መከተል ነው፡፡ ሰይጣን እግዚአብሄር የሰጠውን ስልጣን በመናቅና አንደኛ ለመሆን በመመኘት የእግዚአብሄርን ስልጣን በመፈለጉ ከሰማይ ተጣለ፡፡
አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፥ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! አሕዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ፥ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቈረጥህ! አንተን በልብህ፦ ወደ ሰምይ ዐርጋለሁ፥ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፥ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ፤ ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ። ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጕድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ። ትንቢተ ኢሳይያስ 14፡12-15
እግዚአብሄር ትሁት ነው፡፡ ትእቢተኝነት የእግዚአብሄርን ትህትና ሳይሆን የሰይጣንን ትእቢት መከተል ነው፡፡
መኖሪያቸውንም የተዉትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁትን መላእክት በዘላለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ቀን ፍርድ ድረስ ጠብቆአቸዋል። የይሁዳ መልእክት 1፡6
2.     ትእቢተኝነት የተፈጠሩበትን አላማ መሳት ነው
እኛ ስንፈጠር ለእግዚአብሄር እየተገዛንና እያመለክነው በትህትና እንድንኖር ነው፡፡ ሰው ግን የተፈጠረበትን አላማ ሲስት እግዚአብሄር ከመቃወም ውጭ ከሰው ጋር ምንም ግንኙነት ማድረግ አይፈልግም፡፡ ሰው ትህትናውን ሲጥል እግዚአብሄር ሊጠቀምበትም ይቅርና አብሮት ምንም ነገርን ሊያደርግ አይችልም፡፡
እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤ ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና። ኦሪት ዘፍጥረት 2፡16-17
ሰው ሆይ፥ መልካሙን ነግሮሃል፤ እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ፥ ምሕረትንም ትወድድ ዘንድ፥ ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሄድ ዘንድ አይደለምን? ትንቢተ ሚክያስ 6፡8
3.     ትእቢት መልከ ጥፉነት ትህትና ውበት ነው
እግዚአብሄር የፈጠረው ሰው ሁሉ ውብ ነው፡፡ እግዚአብሄር ውብና ድንቅ ተደርጎ ያልተፈጠረ ሰው የለም፡፡ ነገር ግን ሰው ሰይጣንን ተከትሎ ውበቱን ሲያጣው አስቀያሚ ይሆናል፡፡ ሰው ትእቢተኛ ሲሆን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረውን የልቡን ውበት ያጣዋል፡፡
ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3፡4
4.     ትእቢተኝነት በራስ ሃይል መተማመን ነው
ሰው በጉልበቱ ካልታመነ ትሁት ይሆናል፡፡ ሰው ግን በራሱ ጉልበት ከተማመነ ትእቢተኛ ይሆናል፡፡
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው፦ ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ትንቢተ ኤርምያስ 9፡23-14
5.     ትእቢተኝነት ለእግዚአብሄር እምላክነት እውቅና አለመስጠት ነው
ትእቢተኝነት በራስ ላይ ራስ ጌታ መሆን ነው፡፡ ሰው የሚሳካለት እግዚአብርን አምላክነት እውቅና ሲሰጥ ብቻ ነው፡፡
የማይታየው ባሕርይ እርሱም የዘላለም ኃይሉ ደግሞም አምላክነቱ ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ ከተሠሩት ታውቆ ግልጥ ሆኖ ይታያልና፤ ስለዚህም እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ስላላከበሩትና ስላላመሰገኑት የሚያመካኙት አጡ፤ ወደ ሮሜ ሰዎች 1፡20-21
6.     ትእቢተኝነት እግዚአብሄርን አላዋቂ ራስን አዋቂ ማድረግ ነው፡፡
ትእቢት ከእግዚአብሄር በላይ የአዋቂነት ስሜት ነው፡፡ ካለአዋቂነት ስሜት ሰው ትእቢተኛ ሊሆን አይችልም፡ 
አትታበዩ፥ በኩራትም አትናገሩ፤ እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፥ እግዚአብሔርም ሥራውን የሚመዝን ነውና፥ ከአፋችሁ የኵራት ነገር አይውጣ። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 2፡3
ለጣዖት ስለ ተሠዋ ሥጋም፥ ሁላችን እውቀት እንዳለን እናውቃለን። እውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል። 1 ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 8፡1
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ትህትና #መዋረድ #ባህሪ #ዝቅታ #ትዕቢት #ትምክህት #መመካት #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment