Popular Posts

Monday, July 9, 2018

በእግዚአብሔር እንጂ በሁኔታ አንታመንም

ብዙ ሰዎች ሁኔታዎች እየጨለሙ ሲሄዱ እምነታቸው የሚጠፋ ይመስላቸዋል፡፡ ነገር ግን እምነት ከሁኔታ ጋር አይገናኝም፡፡ እምነት የሚመጣው ከእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ እምነት የሚወሰንው በእግዚአብሄር ፈቃድ እንጂ በሁኔታ አይደለም፡፡ እምነት የሚሄደው ከእግዚአብሄር ቃል ሃሳብ እንጂ ከሁኔታ ጋር አይደለም፡፡
ሁኔታዎች እንዳመንነው ሳይሆነ ካመነንው ከእግዚአብሄር ቃል የተቃረነ ሲመስል እምነታችን ከመጥፋት ግን እየጠራ ይሄዳል እንጂ አይጠፋም፡፡ ሁኔታዎች ሁሉ ካመንነው ተቃራኒውን ሲናገሩ እምነታችን ሲፈተን እየጠራ ይሄዳል፡፡
በዚህም እጅግ ደስ ይላችኋል፥ ነገር ግን በእሳት ምንም ቢፈተን ከሚጠፋው ወርቅ ይልቅ አብልጦ የሚከብር የተፈተነ እምነታችሁ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ፥ ለምስጋናና ለክብር ለውዳሴም ይገኝ ዘንድ አሁን ለጥቂት ጊዜ ቢያስፈልግ በልዩ ልዩ ፈተና አዝናችኋል። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1፡6-7
ብዙ ጊዜ ፀሎታችን ወዲያው ሲመለስ እምነታችን አያደገ ይመስለናል፡፡ የፀሎታችን መልሰ የዘገየ ሲመስለን ደግሞ እምነታቸን እየደከመ ይመስለናል፡፡ ሁኔታዎች እንደፈለግናቸው ሲሄዱ እምነታእን የሚያድግ ሁኔታዎች እንደፈለግናቸው ካለሄዱ እምነታችን የሚቀጭጭ ይመስለናል፡፡ ፀሎታችን ያልተመለሰ ሲመስለን እምነታችን ውስጥ ወስጡን እምነታችን ያድጋል፡፡ ሁኔታዎች ከእግዚአብሄር ቃል ተቃራኒ እምነታችን እየጠራ ይሄዳል፡፡  
ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማም አሕዛብን ሲሸፍን የእምነታችን ብርሃን እየጨመረ ይደምቃል፡፡ ስለዚህ ፀሎታችን ያልተመለሰ ሲመስለን እምነታችን ግን እየጨመረ እየደመቀ ይበራል፡፡
ብርሃንሽ መጥቶአልና፥ የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻልና ተነሺ፥ አብሪ። እነሆ፥ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማም አሕዛብን ይሸፍናል፤ ነገር ግን በአንቺ ላይ እግዚአብሔር ይወጣል ክብሩም በአንቺ ላይ ይታያል፤ አሕዛብም ወደ ብርሃንሽ ነገሥታትም ወደ መውጫሽ ጸዳል ይመጣሉ። ትንቢተ ኢሳይያስ 60፡1-3
እንዲያውም ሁኔታዎች ከእግዚአብሄር ቃል በተቃራኒ እንደመሄድ እምነትን የሚያጠራውና ይበልጥ እግዚአብሄር ላይ እንድንደገፍ የሚያደርግ ሌላ ነገር የለም፡፡ እንደ ሁኔታዎች አለመከናወን እምነትን የሚያጠራው ነገር የለም፡፡ እንደ እምነት ፈተና እምነትን የከበረ አድርጎ የሚያጠራው ነገር የለም፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #መፈተን #መጥራት #ጨለማ #ብርሃን #እሳት ##መናገር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ቃል #ማሰላሰል #ማድረግ #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment